You are on page 1of 4

ምኩራብ

ምኩራብ ማለት ምን ማለት ነው

 ምኩራብ» ማለትም ቀጥተኛ ፍችው ኮረብታ፣ ተራራ የሚያኸል ታላቅ ሕንጻ ማለት ነው፡፡

 ምኩራብ ማለት ሰቀላ መሰል አዳራሽ ማለት ነው።

 ምኩራብ ማለት ለአምልኮትና ለትምህርት ለህብረተሰቡ


አገልግሎት የሚሰጥ የአይሁድ ቤተ ጸሎት ነው።
 ያለንበት የዓቢይ ጾም ሳምንት በማኅሌታይ ያሬድ ስያሜ፣ “ምኩራብ” ተብሎአል፤ ምኩራብ አይሁድ በምርኮ
ወደ ባቢሎን በተወሰዱ ወራት፣ ቅዱሳት መጻሕፍትን ለማንበብና የሕጉን ቃሎች ለማሰብ፣ በየጥቂት አባወራ
በመሰባሰብ የጀመሩት ነው። ወደ አገራቸው ሲመለሱም ይኸንኑ በመቀጠል፣ ከዋናውና መሥዋዕት
ከሚቀርብበት መቅደስ ባሻገር፣ በየመንደራቸው አቅራቢያ ምኩራብ በመሥራት፣ ቅዱሳት መጻሕፍትን
ማጥናትና ማንበብን በዚያ ጀመሩ። እንግዲህ ማኅሌታይ ያሬድ፣ ምኩራብን ለዓቢይ ጾም ሦስተኛው ሳምንት
ሲሰይም፣ በሳምንቱ ውስጥ ከሚነበቡት የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች ደግሞ፣ ዮሐ. 2፥12-22 ን በመመደብ ነው።
ክፍሉም በቀጥታ በኢየሩሳሌም ከነበረው ቤተ መቅደስ ጋር በማያያዝ፣ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተናገረው ስለ
መኾኑ የታመነ ነው።

 ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በቦታው ይገኝ እንደነበር ወንጌል “በሰንበት ወደ ምኵራብ ገብቶ አስተማረ”
(ማር 1፡21) ይላል፡፡

 ጌታ በመዋዕለ ስብከቱ በእስራኤል ሀገር ብዙ ምኩራቦች


ስለነበሩ እየገባ ወንጌልን አስተምሮባቸዋል። በዚህም “ቦአ
ኢየሱስ ምኩራበ አይሁድ ወመሀረ ቃለ ሃይማኖት” እንዲል
ቅዱስ ያሬድ ኢየሱስ ወደ አይሁድ ምኩራብ ገብቶ
የሃይማኖት ቃልን አስተማረ። ከሚለው የቅዱስ ያሬድ ዜማ
ሥያሜውን አግኝቷል።
 በምኩራብ ጸሎትና ትምህርት ይፈጸምበታል። መሥዋዕት
ግን አይከናወንም። መሥዋዕት ግን በታላቁ ቤተ መቅደስ
በኢየሩሳሌም ብቻ ይፈጸም ነበር። በዚህ ሳምንት
የሚነገረው ታሪክ ጌታ ቤተ መቅደሱን የገበያ ማዕከል
አድርገው ሸቀጥ ዘርግተው በጉን ላሙን ርግቡን እየሸጡ
አገኛቸው። በዚህ ተቆጥቶ በጉን ላሙን ርግቡን ከምኩራብ
አስወጥቶ ሸቀጣቸውንና መደርደሪያቸውን እንዲሁም
ወርቅና ብራቸውን በነፋስ በተነባቸው ይላል።

 በዚህ ሁኔታ ከቤተ መቅደስ አስወጥቶ "ቤቴ የጸሎት ቤት


ትባላለች እናንተ ግን የሽፍቶችና የወንበዴዎች ዋሻ
አደረጋችኋት" በማለት ወቅሷቸዋል። “አሰስሉ ወአውፅኡ
ዘንተ እምዝየ ወኢትረስዩ ቤተ አቡየ ቤተ ምሥያጥ” እንዲል
ዮሐ. 2፥16፤ ማቴ. 21፥13። ይህን ተአምር በማሳየት ቤተ ጸሎት
የተቀደሰ ከገበያ የተለየ መሆኑን አስተምሮበታል።
በሰንበተ ምኩራብ ጌታ ወደ ቤተ መቅደስ ገብቶ ለዋጮችን
ማስወጣቱ ወርቅና ብሩን በነፋስ መበተኑ ላሞችን በጎችን
በጅራፍ መግረፉ ቤተ መቅደሱን ማንጻቱ ወዘተ ይነገራል።
የዚህም በዓል ታሪክ ዝርዝር ሁኔታው ማቴዎስ 21፥12-13 ላይ
(

ተጠቅሷል፡፡)
ከዚህ ምእመናን ወደ ቤተ ለጸሎት ዘወትር ስለመገኘት እንድናውቅና እንድናስብ ይገባ ዘንድ ከጾሙ ሳምንታት ውስጥ
አንዱን ምኵራብ በሚል ስያሜ ተሰይሞ እንድናስበው ተደረገ (ማቴ.21፥13)፡፡ ስለዚህ ምዕመናን በዚህ የጸሎት ስፍራ
በቤተ ክርስቲያናችን ዘወትር እየተገኘን እንድንጸልይ፣ እንድንማርና ሕይወታችንን በዚያ እንድንመሠረት የእግዚአብሔር
ቃል “በእግዚአብሔር ቤት በመቅደሱ ውስጥ እንገናኝ” (ነህምያ 6፡10) ይለናል፡፡

ምኩራብ - ሦስተኛው ቤተ መቅደስ

ጌታ ኢየሱስ ግን “ይህን ቤተ መቅደስ አፍርሱት፥ በሦስት ቀንም አነሣዋለሁ” ብሎ፣ “ስለ ሰውነቱ ቤተ መቅደስ”
ተናገረ። ለአይሁድ ይህ የጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ንግግር አልተዋጠላቸውም፤ አልተቀበሉትምም። እነርሱ የሚያወሩለት
መቅደስና ጌታ ኢየሱስ የሚያወራው መቅደስ ፈጽመው አይገናኙም ነበር። እነርሱ ስለሚፈርሰውና ከድንጋይ ስለ
ተሠራው ቤተ መቅደስ ሲያወሩ፣ እርሱ ግን ስለ ሕያውና ፈጽሞ ስለማይሞተው ሕያው ቤተ መቅደስነቱ ተናገራቸው።
ይህን ለማስተዋል የቤተ መቅደሶቹን ይዘት ማየቱ በጥቂቱ ይጠቅመናል።

ፊተኛው መቅደስ

ፊተኛው መቅደስ የተሰጠው ከእግዚአብሔር በሰሎሞን አማካይነት ነው። ያ መቅደስ ግርማውና ክብሩ እጅግ
የሚያስደንቅ ነበር፤ ሰሎሞን አባቱ ዳዊት ባከማቸው ሃብት፣ መቅደሱን የሠራው እጅግ አንቆጥቁጦ፤ አስውቦ ነበር።
እግዚአብሔር ራሱ በዚህ መቅደስ ተገኝቶ ሰሎሞንን በተደጋጋሚ በጨለማ ውስጥ ኾኖ ተናግሮት ነበር። ይህ መቅደስ
ለአይሁድ ብቻ ያይደለ፣ ከአይሁድ ውጭና የኪዳኑ አካል ያልኾነም ሰው መጥቶ በዚያ ቢጸልይ እግዚአብሔር
እንደሚሰማው ቃል የገባበት መቅደስ ነበር።

የመሰጠቱ ዋነኛ ዓላማም፣ እግዚአብሔር አምላክ ክብሩን በዚያ መቅደስ ውስጥ በመግለጥ፣ በሕዝቡ መካከል ለመኖር
ነበር። ሥፍራው የያህዌ ዋነኛ መታወቂያ፤ የአምልኮ ማዕከል፤ የእግዚአብሔር መገለጥ የሚታይበትም ቅዱስ ስፍራ
ነበር። በእርግጥ መቅደሱ የአይሁድ ብቸኛ ተስፋና የአምልኮአቸው ማዕከል ነበር፤ ነገር ግን ኀጢአትን ስለ ሠሩ እጅግ
ውብና ማራኪው ቤተ መቅደስ በናቡከደነጾር ፈርሶ ፍጹም ምድረ በዳ ኾነ።

ኹለተኛው ቤተ መቅደስ

ፊተኛው ቤተ መቅደስ ከፈረሰና እስራኤል ለሰባ ዓመታት ያህል በባቢሎን ምርኮ ከተገዙ በኋላ፣ በእነ ዘሩባቤል መሪነት
ኹለተኛው ቤተ መቅደስ ተገነባ። ምንም እንኳ ግንባታው እጅግ የተለያየ ቢሆንም፣ የኹለተኛው ቤተ መቅደስ ዓላማም
ከፊተኛው ቤተ መቅደስ የተለየ አይደለም። ከዚህም ባለፈ ታላቁ ሄሮድስ በአይሁድ ዘንድ ድጋፍና ተወዳጅነት ለማግኘት
ሲል፣ መቅደሱን ለአርባ ስድስት ዓመታት ያህል በሚማርክ መልኩ አድሶትና አስፋፍቶት ነበር። ነገር ግን ይህም መቅደስ
በ 70 ዓ.ም እስከ ዛሬ ድረስ ዳግም መሠራት እስከማይችል ድረስ ፈጽሞ ፈረሰ፤ ፈራረሰ፤ ወደመ።
እግዚአብሔር አንድን መቅደስ ለእስራኤል የሰጣቸው፣ ክብሩንና ራሱን ለእነርሱ ሊገልጥና ለዘወትርም በዚያ
እንደሚገኝ ኪዳን በመግባት ነበር።

ሦስተኛው ቤተ መቅደስ

You might also like