Professional Documents
Culture Documents
Teaching Plan
Teaching Plan
በዚህ ክፍል የመምህሩ እና የተማሪዎች ተግባራት በዝርዝር ይገለጻሉ እኚህ ተግባራት በአራት ንዑሳን ክፍሎች የተከፈሉ
ናቸው እነሱም
1. መግቢያ፤
2.አቀራረብ
የዕለቱ ትምህርት የሚቀርብበት ዋናው ክፍል ሲሆን በዚህ ክፍል ውስጥ መምህራን የሚጠቀሟቸው መርጃ መሳሪያዎች
(ሚዲያዎች) ከመማር ማስተማር ዘዴዎች ጋር በተያያዘ መል የሚተገበሩ ረግባራት (የመምህር እና የተማሪዎች)
በዝርዝር በቅደም ተከተል የሚገለጽበት ይሆናል፡፡
3. ማጠናከሪያ
በዚህ ክፍል ተማሪዎች የተማሩትን ትምህርት ይበልጥ በአእምሮዋቸው ውስጥ ሰርጾ እንዲቀር የሚያስችሉ ተግባራት
ይከናወናሉ እነዚህም ተግባራት በዕቅዱ ውስጥ በዝርዝር ይቀመጣሉ የዕለቱ ትምህርት በአጭሩ እንዴት
እንደሚከለስላቸው ይታቀድበታል
4. ግምገማ ይህ ክፍል ተማሪዎች የተማሩትን ትምርት እንዴት አድርገው እንደተቀበሉት በሚፈለገው መጠን
ትምህርቱን እንደተረዱት እና እንዴት እንደተገበሩት እና እንደሚተገብሩት የሚመዘንበት ክፍል ሲሆን ይህ ክፍ
በስተመጨረሻ ብቻ ሳይሆን መጀመሪያ መሃልም ላይ ሊሆን እና በአጠቃላይ ትምህርቱ እንዲያመጣ የሚፈለገውን
ውጤት ማምጣት አለማምጣቱን የምንለካበት ክፍል ነው፡፡
ዕለታዊ የትምህርት እቅድ አግድም ቅጽ
1. የመምህሩ ስም
2. የትምህርቱ ዓይነት
3.ትምህርቱ የሚሰጥበት ዕለት እና ቀን
4.የዕለቱ ትምህርት ርዕስ
5.ክፍለጊዜው
6.ለክፍለ ጊዜው የተሰጠው ደቂቃ
7.የትምህርቱ ዝርዝር ዓላማ
የጊዜ የትምህርቱ ዋና ዋና የመማር ማስተማር ሂደት መርጃ መሳሪያ ምዘና እና ምርመራ
ድልድል(ደቂቃ) ይዘቶች ግምገማ
መግቢያ መግቢያ
አቀራረብ አቀራረብ
ማጠናከሪያ ማጠናከሪያ
ግምገማ ግምገማ
የመማር ማስተማር እቅድ ለትላንቱም ለዛሬውም እንዲሁም ለነገውም የሚጠቅም ለመማር ማስተማር
ሂደት ወሳኝ ጉዳይ በመሆኑ ሁሉም መምህራን ይህንን ተገንዝበው ማስተማሪያ እቅድ አዘጋጅተው
ለእያንዳንዱ የሚመለከተው ክፍል እሱን አቅርበው እንዲያስተምሩ ይመከራል ምክንያቱም
የማስተማሪያ እቅድ የሚከተሉት ወሳኝ ጥቅሞችን ይሰጣል እና
ለሰንበት ትምህርት ቤቱ
1. መምህሩ ምን እንደሚያስተምር
2. ማንን እንደሚያስተምር
3. ለምን እንደሚያስተምር
4. በምን እንደሚያስተምር
5.ምን እንዳስተማረ እና ምን እንደቀረው
6. የቱ ጋር እንዳለ
7. መፍጠን መዘግየቱን ለመከታተል
8. ከዓላማው አንጻር አዛምዶ ትምህርቶቹን እያስተማረ እንደሆነ እንዲያውቅ ይረዳዋል
9. ለቁጥጥር እና ለክትትል ለግምገማም ያግዘዋል
10. መርሐግብሩን እንዲሁም ለትምህርቱ የተሰጠውን ሰዓት እንዲገመግም እና ማሻሻያ እንዲያደርግ
ለመምህሩ
1. ትምህርቱን መቼ ጀምሮ መቼ እንደሚጨርስ ያሳውቀዋል
2. በየጊዜው ምን ላይ ነበር ያቆምነው ከማለት ያድነዋል
3. ምን ለምን እንደሚያስተምር ያሳውቀዋል
4. ከዓላማ አንጻር ትምህርቱን እንዲያስተምር ያግዘዋል
5.የትምህርት መቆራረጥ እና መደጋገም እንዳይኖር ይረዳዋል
ወስብሐት ለእግዚአብሔር