Professional Documents
Culture Documents
ኦርቶዶክሳዊ_መምህር፣_ዕውቀቱ_እና_ክሂሎቱ
ኦርቶዶክሳዊ_መምህር፣_ዕውቀቱ_እና_ክሂሎቱ
1/ ከቅርብ እስከ ሩቅ፡- የአንድ ሐዋርያ ተግባር አጠገቡ ካለው ማኅበረሰብ ጀምሮ አይቶት እና
ሰምቶት እስከማያውቀው ሕዝብ ሊደርስ እንደሚችል
ዋና ዋና ተልዕኮዎች
1
ዝርዝር ተልዕኮዎች
አንዳንድ ሊቃውንት አንድ የወንጌል መምህር ሦስት ነገሮች ሊኖሩት ይገባል ይላሉ፡፡ እነዚህም
ለምሳሌ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ በቁስጥንጥንያ ሐጊያ ሶፍያ ቤተ ክርስቲያን በየዕለቱ የሠርክ
ጉባኤ ነበረው፡፡ ትምህርቶቹን ተከታትለው ይጽፉ የነበሩ ደቀ መዛሙርትም ነበሩት፡፡ እርሱም
ትምህርቶቹን አስቀድሞ ይጽፋቸው ነበር፡፡ ባስልዮስ ዘቂሳርያም በቂሳርያ ከተማ በመሠረተው
ገዳም አያሌ ሕዝብ ያስተምር ነበር፡፡ በተለይም ዓምደኞች እየተባሉ ይጠሩ የነበሩ መምህራን
ሕዝቡን ሌሊትና ቀን ያስተምሩት ነበር፡፡ ስምዖን ዘዓምድ ከቆመበት ዓምድ ሳይወርድ ቀንና
ሌሊት ወደ እርሱ ይመጡ የነበሩትን ሁሉ አስተምሯል፡፡
የመጻፍ በሐዋርያውያን አበው እና ከእነርሱ በኋላ በተነሡ የቤተ ክርስቲያን መምህራን ዘንድ
እነዚህን ሦስቱን ነገሮች እናገኛለን፡፡ ዛሬ በየድርሳኖቻቸው እና በሃይማኖተ አበው
የምናገኛቸውን ጽሑፎች እና መጻሕፍት ጽፈዋል፡፡ ትርጓሜያትን አዘጋጅተዋል፡፡ እንዲያውም
2
በሃይማኖተ አበው ላይ የምናገኛቸውን ድርሰቶቻቸውን ስናይ አበው እርስ በርሳቸው
በመልእክት ትምህርት ይለዋወጡ እንደ ነበር፣ጥያቄ ይጠያየቁ እንደነበር እንረዳለን፡፡
የዕውቀት ምንጮች
የዕውቀት መሠረታውያን
3
የጌታችን ትምህርቶች ወደ ኋላ ሄደን ብሉይን ፣ወደፊት ተጉዘን ሐዲስን የምንተረጉመው
የቤተ ክርስቲያን መሠረቷ የሆነው ጌታችን በሰጠን መሠረት ላይ ሆነን ነው፡፡
4. ለሌሎች አርአያ የሚሆን የቅድስና ሕይወትን ሲኖር (H.G. Bishop Moussa, The
Characteristics of Orthodox Teaching. P ,85)
4
የተለያዩ እሴቶችን እንማርበታለን፡፡ የተለያዩ አበው ልዩ ልዩ ጸጋ፣ ተሰጥኦ እና ደረጃ አላቸው፡፡
የልዩ ልዩ አበውን ሕይወት ስናጠና እነዚህን ነገሮች እናገኛለን፡፡ ከአትናቴዎስ ለሃይማኖት
መጽናትን፣ ከእንጦንስ ራስን መግዛትን፣ ከአርሳንዮስ ትኅትናን፣ ከዲዮስቆሮስ ሃይማኖትን
በድፍረት እና በእውነት መመስከርን፣ ከአባ ቢሾይ ጸሎት እና ፍቅርን፣ እንማራለን፡፡
እንዴት እናንባቸው?
5
የነበሩበትን ዘመን፣ ሁኔታ እና ለነማን እንደ ጻፉት መረዳት አለብን፡፡ መጀመርያ የተጻፈበትን
ቋንቋ፤ በዘመናቸው የነበረውን የሃይማኖት እና የሥነ ምግባር ችግር ማጤን አለብን፡፡
• ቅዳሴያት/liturgies/
7
የታሪክ መጻሕፍት/Ecclesiastical history/ የቤተ ክርስቲያንን ታሪክ በተመለከተ የተጻፉ
(Fr.Tadros Yacoub Malaty. An Introduction of Patrology.)
ኢትዮጵያውያን አባቶች
የቤተ ክርስቲያን ትውፊት፡ ሁሉም ነገር በመጽሐፍ አልተጻፈም፤ በቤተ ክርስቲያን ሕይወት
ውስጥ በጸሎቱ፣ በማኅሌቱ፣ በቅዳሴው፣ወዘተ የምናገኛቸው ትምህርቶች እና ሥርዓቶች ለቤተ
ክርስቲያን ርቱዐዊ ጉዞ አስፈላጊ ናቸው፡፡
8
የቤተ ክርስቲያን ጉባኤያት ውሳኔዎችበየዘመናቱ የተነሡ መናፍቃንን፣ በየጊዜው የተፈጠሩ
ችግሮችን፣ በየሁኔታው የገጠሙ ፈተናዎችን ለመፍታት በጉባኤያት ተሰብስበው አበው
የደነገጓቸው ድንጋጌዎች ቤተ ክርስቲያን ከማዕበል ወጥታ ወደ ጸጥታ ወደብ እንድታመራ
ያደረጉ፤ የቤተ ክርስቲያንንም አንድነት ያጸኑ ዋልታዎች ናቸው፡፡
ተጨማሪ ዕውቀቶች
አንድ አስተማሪ ቅዱሳት መጻሕፍትን ስላወቀ ብቻ ሊያስተምር አይችልም፡፡ ዘመኑንም ማወቅ
አለበት፡፡ ዘመኑን ማወቅ ማለት ደግሞ፡
የዘመኑን አስተሳሰብ ማወቅ
የዘመኑን ችግሮች ማወቅ
የዘመኑን ጥያቄዎች ማወቅ
የዘመኑን የአኗኗር ሁኔታ ማወቅ
የዘመኑን ሥርዓተ ማኅበር ማወቅ ማለት ነው፡፡
እነዚሀን ነገሮች ለማወቅ ደግሞ ሚዲያዎችን መከታተል፣ የዘመኑን ወሳኝ መጻሕፍት
ማንበብ እና አካባቢን ማጥናት ያስፈልጋል፡፡ የቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅን ሃብታም እና
ድኻ፣ ጋብቻ፣ ወዘተ መጻሕፍቱን ስናነብ ሊቁ ዘመኑን እንዴት እንደተረዳው እናውቃለን፡፡
9
የግሪክን ፈላስፎች፣ የዘመኑን ዜናዎች፣ የወቅቱን የአኗኗር ባህል በውስጡ ይተነትናቸዋል፡፡
ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ የጻፈውን የሙሴ ሕይወት ስናነብ የግሪክ ፈላስፎችን አመለካከት እንዴት
እንዳፈረሰ እናያለን፡፡
አንድ አስተማሪ ከላይ ያሉትን ምንጮች መጠቀም የሚያስችሉት ሦስት መሣርያዎች አሉ፡፡
እነርሱም
የማንበብ ልምድ
መረጃ የማሰባሰብ ልምድ እና
የቋንቋ ችሎታ ናቸው፡፡
1. የማንበብ ልምድ፡
የማያነብ ሰባኪ ባያስተምር ይመረጣል፡፡ ከሚደርቅ ምንጭ የሚያረካ ውኃ አይገኝምና፡፡
ማንበብ ደግሞ ከመጻሕፍት ብቻ ሳይሆን ራሳቸው ተንቀሳቃሽ መጻሕፍት ከሆኑት ሊቃውንት
መማርም ነው፡፡ ከቀደሙት አበውም ሆነ ከማንደርስበት የዕውቀት ምንጭ መማር የምንችለው
በማንበብ ነው፡፡ ስለዚህም ሰባኪው የማነበብ እና የማጣጣም ልምድ ሊያዳብር ይገባዋል፡፡
ወስኖ፣ ጊዜ እና ገንዘብ መድቦ ማንበብ ልምድ መሆን አለበት፡፡ የምናነባቸው መጻሕፍት እንደ
በያይነቱ ምግብ ከሁሉም አቅጣጫ ቢሆኑ ይመረጣል፡፡ የሕክምና ሰዎች ልዩ ልዩ ዓይነት
ምግብ የሚመገብ ሰው የተለያዩ ቫይታሚኖች፣ ማዐድኖች እና ገንቢ ነገሮች የማግኘት ዕድሉ
ይሰፋል እንደሚሉት ሁሉ ልዩ ልዩ ዓይነት መጻሕፍትን ማንበብም እንደዚሁ ነው፡፡
2. የማሰባሰብ ልምድ፡
የቤተ ክርስቲያን መጻሕፍት በቀላሉ አይገኙም፡፡ በየገዳማቱ እና በየሊቃውንቱ፤ በየቤተ
መጻሕፍቱ እና በየሙዝየሙ ተበትነዋል፡፡ እነዚሀን ለማገኘት ትእግሥት እና ጥረት
ያስፈልጋል፡፡ መረጃዎችን በኮፒ፣ በድምጽ፣ በማስታወሻ፣ በኣካል እና በአእምሮ የማሰባሰብ
ልምድ ያስፈልጋል፡፡
3. የቋንቋ ችሎታ፡
ግእዝን፣ ዐረብኛን፣ ዕብራይስጥን እና ግሪክን የመሳሰሉ ቋንቋዎች የጥንት ጽሑፎችን
ለመመርመር፤ እንግሊዝኛ ደግሞ በዘመኑ የተጻፉትንም ሆነ የተተረጎሙትን ለማግኘት
አስፈላጊዎች ናቸው፡፡ ዐቅማችን የፈቀደውን ያህል ብናውቃቸው በሩ ወለል ብሎ
ይከፈትልናል፡፡
የማስተማር ዓላማ
10
ኦርቶዶክሳዊ የማስተማር ዐላማው ማስደነቅ፣ ማስደመም፣ ማዝናናት፣ ማሳወቅ፣
ማስጨብጨብ፣ ወዘተ አይደለም፡፡ ማዳን ነው፡፡ (Tadros The Syrian, Orthodox
Teaching. P 35) ሰዎች እግዚአብሔርን ዐውቀው፣ በክርስትና ሕይወት ኖረው፣ መንግሥተ
ሰማያትን እንዲወርሱ ማድረግ ነው፡፡ ሐዋርያዊው ሄሬኔዎስ በጻፈው «መድፍነ መናፍቃን»
በተሰኘው መጽሐፉ መግቢያ ላይ ማርቅያኖስ የተባለውን ልጁን ሲመክረው «ይህንን
የምጽፍልህ ከጥቂቱ ነገር ብዙ ዐውቀህ፣ የእውነትንም ልዩ ልዩ ክፍሎች ተረድተህ፣
የእግዚአብሔር የሆኑትን ነገሮችም ተገንዝበህ፣ የመዳንን ፍሬ እንድታፈራ ነው» ብሏል፡፡ ለዚህ
ደግሞ ማሳመን፣ ማሳተፍ እና ማስቀጠል ወሳኞቹ ናቸው፡፡ (Irnaeus, On The apostolic
preaching. P 29)
ማሳመን፡ ማለት አንድን ሰው በበቂ ኦርቶዶክሳዊ ዕውቀት ማስታጠቅ ነው፡፡
እንዳይናወጽ እና እንዳይወድቅ አድርጎ መትከል ነው፡፡ ነገ መምህሩ እንኳን ባይኖር
ተማሪው በራሱ ሊኖር እንዲችል አድርጎ መገንባት ነው፡፡
ማሳተፍ ደግሞ የምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን ተሳታፊ እንዲሆን ማስቻል ነው፡፡
ማስቀጠል ደግሞ እየጾመ፣ እየጸለየ፣ አሥራት እያወጣ፣ ሰንበቴ እየጠጣ፣ እየተማረ፣
እያስተማረ፣ እየጻፈ፣ እየቀደሰ፣ እያስቀደሰ፣ ወዘተ በአገልግሎት እንዲቀጥል ማድረግ
ነው፡፡
በዚህ ጉዞ ውስጥ ሰባኪው ምእመናን በሦስት ጉዳዮች ላይ ያላቸውን ጽናት መለካት አለበት
11
ትምህርቶችን፣ ውይይቶችን እና የልምድ ልውውጦችን ማካተት አለባቸው፡፡ ይህን የመሰሉ
መድረኮች በሀገር አቀፍም ሆነ በአካባቢ ደረጃ ሊመሠረቱ ይችላሉ፡፡
2. ተተኪዎችን ማፍራት
ፍላጎት እና ተነሣሽነት ያላቸውን ማሳወቅ እንጂ የሚያውቁትን ፍላጎት እንዲኖራቸው ማድረግ
ከባድ ነው፡፡ በመሆኑም ጥረት፣ ትጋት እና ፍላጎት ያላቸውን መርጦ በግል፣ በቡድን እና
በማኅበር በማሠልጠን ማሠማራት ያስፈልጋል፡፡ አሁን እንደምናደርገው ሲንቀሳቀሱ
የማይታዩትን ለማንቀሳቀስ ከመሞከር፤ የሚንቀሳቀሱትን የሰሉ የበቁ እንዲሆኑ ማድረግ
ይሻላል፡፡
3. ቴክኖሎጂዎችን መጠቀም
ቪዲዮ፣ መቅረጸ ድምፅ፣ ኮምፒውተር ወዘተ የመሳሰሉትን መሣርያዎችን በበቂ ሁኔታ
መጠቀም ያስፈልጋል፡፡ በተለየም ሰባክያን የኢንተርኔትን አጠቃቀም አውቀው ብሎ ጎችን
በመክፈት፣ ዌብሳይቶችን በማዘጋጀት፣ የኢሜይል ትምህርቶችን በመላክ ወዘተ እንዲሳተፉ
መደረግ አለበት፡፡
4. መንፈሳዊ ድፍረት እና ንቃት
ዛሬ ዛሬ መድረኮቻችን ዕውቀት እና ሕይወት በሌላቸው ሰባክያን እየተሞሉ ይመስላል፡፡
እነዚህ ሰባክያን ያላቸው አንድ ነገር ቢኖር ድቅድቅ ድፍረት ነው፡፡ ሌሎች በትኅትና ዝም ሲሉ
እነርሱ በድፍረት ያልሆኑትን ነን ብለው ወጡ፡፡ ስለዚህም ያልተማሩትንም፣ የማያምኑበትንም
ያስተምራሉ፡፡ አሁን ከእውነተኞቹ መምህራን መንፈሳዊ ድፍረት እና አካላዊ እና ሥነ ልቡናዊ
ንቃት ያስፈልጋል፡፡ ራሳችሁን በዕውቀት እና በአተያይ አዘምኑ፡፡
የምታውቁትን ሁሉ «እናውቃለን፤ ግን አይጠቅምም ብለን ተውነው» ለማለት ማቻል
አለባችሁ፡፡
የትምህርት ደረጃዎቻችንንም እናሻሽል፡፡ ወደፊት ከአብነት ትምህርት ቤት የሚመጡት
እያነሡ፤ ከዘመናዊ ትምህርት ቤቶች የሚመጡት እየበዙ ነው የሚሄዱት፡፡ ስለሆነም
አብረናቸው ማደግ ይኖርብናል፡፡ ካልሆነም በማንበብ እና በመከታተል ራሳችንን ማብቃት
አለብን፡፡
5. በመዋቅር መሥራት ነገር ግን ያለ መዋቅር ማሰብ
12
ሥራን በአደረጃጀት፣ በመዋቅር እና በተቋማዊ መንገድ መሥራት መልካም ነው፡፡ ሃሳብን ግን
በመዋቅር ማሰብ አስቸጋሪ ነው፡፡ መዋቅሮች ይረዱናል፤ ያግዙናል እንጂ አይተኩንም፡፡
ስለሆነም ለማንበብም፣ ለመጻፍም፣ ለማስተማርም፣ ለመማርም፣ ለማደግም፣ ለመሻሻልም፣
ወንጌልን ለማስፋፋትም፣ ለማሠልጠንም መዋቅርን እና መዋቅርን ብቻ መጠበቅ የለብንም፡፡
አንዳንዶቻችን በኮሚቴ፣ በማኅበር፣ በቡድን፣ በጽዋ ካልተሰበሰብን ሥራ መሥራት የምንችል
አይመስለንም፡፡ እነዚህ ሁሉ ለሥራ መልካም ሊሆኑ ይችላሉ ለማሰብ ግን መሰብሰብ
አያስፈልግም፤ መጸለይ እና መጨነቅ እንጂ፡፡ ከመዋቀራችን በፊት ሰው ነበርን፡፡ ስለሆነም
መጀመርያ የሰውነታችንን ሥራ እንሥራ፡፡ በጀት ፈልገን፣ ሰው አስተባብረን ለመሥራት
እንሞክር እንጂ ሁሉን በዕቅድ እና በበጀት፣ በመመርያ እና በስብሰባ አናድርገው፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
13