You are on page 1of 15

የሴቶች ሚና


ቤተክርስቲያን
መግቢያ
በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አስተምህሮ

የክርስቲያኖችን አንድነት በሦስት “ፆታ ምዕመናን” ይከፍላቸዋል።
እነርሱም ወንዶች፣ ሴቶችና ካህናት ናቸው።
እግዚአብሔር በቅዱሳት መጻሕፍት እንደተናገረን በመንፈሳዊ
ህይወት የሁሉም ፆታ ምዕመናን ዓላማ መስዋዕትነትና ከራስ በላይ
ለሌሎች መኖር ነው።
ወንዶች የቤተሰብ ራስ (ተጠሪ) መባላቸው እንደ ክርስቶስ
ራሳቸውን ስለቤተሰባቸው ቤዛ እስከማድረግ የሚገለጥ ነው።
ሴቶች የሕይወት ምንጭ (እናት) በመሆናቸው በብዙ መከራ
እየተፈተኑ የቤተክርስቲያንን ሕይወት ያስቀጥላሉ።
ካህናትም ክህነታቸው “እናንተም እንዲሁ አድርጉ” ብሎ አብነት
እንደሆናቸው ጌታ ዝቅ ብለው ምዕመናንን እንዲያገለግሉ ነው።
የሴትነት (የእናትነት) አገልግሎት
ክብር

“ ቅድስት ሥላሴ ” ብለን በእናት አንቀፅ
መጥራታችን
“ እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ” ሰው ሁሉ
እናታችን ጽዮን ይላል (መዝ 86:5)” ተብሎ በትንቢት
የተነገረላት፣ “እነኋት እናትህ (ዮሐ 19:38)” ብሎ
በአካል የሰጠን እናታችን ናት።
“ እናት ቤተክርስቲያን ”
የሴቶች አገልግሎት በብሉይ ኪዳን


እናታችን ሔዋን (ዘፍ 3:20)

እናታችን ሣራ ደግሞ የእስራኤል ዘሥጋ እናት (ዘፍ 17:16)
 ያዕቆብ በረከትን እንዲያገኝ ያደረገችው ርብቃ
 የዮሴፍ እናት ራሄል
 ሙሴን በፈርኦን ቤት በጥበብ ያሳደገችው የሙሴ እናት (ዮካቤድ) (ዘፀ 1:28
 ሕዝበ እስራኤል ባህረ ኤርትራን ከተሻገሩ በኋላ ከበሮን ይዛ ምስጋናውን ስትመራ የነበረችው
የሙሴ እኅት ማርያምም ሴቶች በዝማሬ እና በምስጋና ዘርፍ ለሚያበረክቱት ድርሻ አብነት ሆናለች
(ዘጸ 15:20)
 የእስራኤልን ሰላዮች ተቀብላ ያተረፈቻቸው በኢያሪኮ ትኖር የነበረችውና በኋላም በዳዊትና
በክርስቶስ የዘር ሀረግ ለመቆጠር የበቃችው ረዓብ ሌላዋ ታላቅ ሴት ነበረች።
 እግዚአብሔር በገለጠላት ጥበብ የጠላትን መሪ ድል ያደረገችው ዮዲት (መጽሐፈ ዮዲት 1)፣
በድንቅ እምነቷ እግዚአብሔር ከሐሰት ፍርድ ያዳናት ሶስና (መጽሐፈ ሶስና 1)
የቀጠለ…
 ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመዋዕለ ስብከቱ ስለ ተአምራት ሲያስተምር “


ንግሥተ ዓዜብ በፍርድ ቀን ከዚህ ትውልድ ጋር ተነሥታ ትፈርድበታለች፤ የሰሎሞንን ጥበብ
ለመስማት ከምድር ዳር መጥታለችና፥ እነሆም፥ ከሰሎሞን የሚበልጥ ከዚህ አለ (ማቴ 12:42)”
በማለት የተናገረላት ንግሥተ ዓዜብ
 ለእስራኤል ድኅነት ምክንያት የሆነች ታላቅ ሴት አስቴር (አስቴር 4:14)።
 አቢጊያ ከባልዋ ከናባል ይልቅ ባለታላቅ አእምሮ ስለነበረች ከዳዊት ጦር የታዘዘውን የሞት ቅጣት
በጥበብ መመለስ ችላለች (1ኛ ሳሙ 25:3)።
 ጌታችንን በመቅደስ ያመሰገነችው (በሉቃ 2:36-38) ነቢይት ሐና ሴቶች ነቢያት ሆነው (በፆም
በጸሎት ተወስነው መጻዕያትን እየተናገሩ፣ የእግዚአብሔርን ድንቅ ስራ እየመሰከሩ) ሲያገለግሉ
እንደነበር ጥሩ ማሳያ ናት።
 በእስራኤል የፍርድ ወንበር ተቀምጣ ትፈርድ የነበረችው ዲቦራም (መሳፍ 4:4-5) ሴቶች በኃላፊነት
ደረጃ ተቀምጠው ለሕዝብና ለቤተክርስቲያን የሚጠቅም ሥራን መሥራት እንደሚችሉ ጥሩ ምሳሌ
ናት።
 የእምነቷ ጽናት በልዩ ሁኔታ የተመሰከረላትና ከክርስቶስ የትውልድ ሀረግ የተቆጠረችው ሞአባዊቷ
ሩት እንዲሁ ልዩ ምሳሌያችን ሆና ትኖራለች።
የሴቶች አገልግሎት በዘመነ ሥጋዌ
 ቅድስት ድንግል ማርያም ከሴቶች ሁሉ የተለየች ናት (ሉቃ 1:26-30)

 ቅድስት ኤልሳቤጥም (ሉቃ 1:39-44)
 ሰሎሜ
 ሳምራዊቷ ሴት (ቅድስት ፎቲና) (ዮሐ 4:4-26)።
 36 ቅዱሳት አንስት (ዮሐ 10:38):።
 ያላትን አንዲት ዲናር ሰጥታ ጌታችን እምነቷን ያደነቀላት ሴት፣
 የልብሱን ጫፍ ብነካ እድናላሁ ብላ በማመን ልብሱን ነክታ የዳነችው ደም
ይፈሳት የነበረችው ሴት (ዮስቃና)
 ማርያም እንተ ዕፍረት
 ጌታችን መስቀል ተሸክሞ በጎልጎታ መከራን ሲቀበል አይሁድን ሳትፈራ ላቡን
እንዲጠርግበት መጎናጸፊያዋን የሰጠችው ቅድስት ቬሮኒካ
 ማርያም መግደላዊት (ማቴ 28:1)
የሴቶች አገልግሎት በዘመነ
ሐዋርያት
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ (
ሮሜ 16:1-7) የጻፈላቸው ፌቤንና፣
ጵርስቅላና አቂላ ሌሎችም ቅዱሳት ሴቶች
ወንጌላዊው ዮሐንስም (2ኛ ዮሐ 1:1) “በእኛ ስለሚኖርና ከእኛ ጋር
ለዘላለም ስለሚሆን እውነት፥ እኔ ሽማግሌው በእውነት
ለምወዳቸውና እኔ ብቻ ሳልሆን እውነትን የሚያውቁ ሁሉ ደግሞ
ለሚወዱአቸው ለተመረጠች እመቤት ና ለልጆችዋ፤ ከእግዚአብሔር
አብና ከአብ ልጅ ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ምሕረት ሰላምም
በእውነትና በፍቅር ከእኛ ጋር ይሆናሉ።” በማለት ያገለግሉ ከነበሩ
ቅዱሳት ሴቶች መካከል ለነበረችው ሮምና ን “እመቤቴ”
የሴቶች አገልግሎት በዘመነ
ሰማዕታት
 
ሰማዕታት ታሪካቸውን በደም የጻፉ ቅዱሳት አንስት
ቅድስት አርሴማ (ስንክሳር መስከረም 29)
ከ50 ቅዱሳት አንስት ጋር በንጉሥ ዑልያኖስ ሰማዕትነትን የተቀበለችው
ቅድስት ሶፊያ
በንጉሥ ዴሲየስ ዘመን ሰማዕትነትን የተቀበለችው ቅድስት አንስጣስያ፣
ገድላቸው ሲዘከር የሚኖረው ቅድስት ባርባራ ፣ ቅድስት ዮልያና እና
ቅድስት ዮስቲና፣
በጽኑ ተጋድሎ ክብርን ያገኘች ቅድስት ዕንባ መሪና (ስንክሳር ነሐሴ 25)፣
ገዳማዊ ሕይወትን ለእናቶች ያስተማረች ሰማዕቷ ዴምያና፣
ከልጇ ጋር ሰማዕትነትን የተቀበለችው ቅድስት እየሉጣ ና (ስንከሳር
ሐምሌ 19) ሌሎችም
…የቀጠለ

ለ25 ዓመታት በገዳም የተጋደለችው ቅድስት ማርታ ተሐራሚት (ስንክሳር ሰኔ 3)፣
በዘመነ ሰማዕታት ልጇን በደም ያጠመቀችው ቅድስት ሣራ ፣
የጌታችን ቅዱስ መስቀል ከ300 ዓመታት በላይ ከተቀበረበት እንዲወጣ ያደረገችው
ንግሥት ኢሌኒ የክርስትና ታሪክ ፈርጦች ናቸው።
 የቤተክርስቲያን ወርቃማ ዘመን በሚባለው
በ4ኛው መቶ ከፍለ ዘመን የነበሩት የቅዱስ አውግስቲን እናት ቅድስት ሞኒካ፣
የቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ እኅት ቅድስት ማክሪና
የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ረዳት የነበረችው ቅድስት ኦሊምፒያ
ከዚህም ባሻገር ታላላቅ ቅዱሳንን ያስገኙልን እንደ
 ቅድስት እግዚእ ኃረያ
 ቅድስት አቅሌስያ
የቀጠለ….

 ጻድቋ ክርስቶስ ሠምራ (ስንክሳር ነሐሴ24)፣
 ከ36ቱ ቅዱሳት አንስት በመዐርግ የተስተካከለችውና ከላሊበላ ውቅር አብያተ
ክርስቲያናት አንዱን ያነፀችው ቅድስት መስቀል ክብራ (ስንክሳር ሐምሌ 28)፣
 በቅድስናና በንጽሕና ኖራ ሰማዕትነትን የተቀበለችው ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ
(እመ ምዑዝ) (ስንክሳር የካቲት 29)፣
 ካቶሊካውያን ቅኝ ገዥዎች በሀገራችን ኢትዮጵያ ኦርቶዶክሳውያንን አስገድደው
እምነት በማስለወጥ ላይ በነበሩበት ዘመን በቅድስናና በጥብዓት ሰማዕትነትን
የተቀበለችው ቅድስት ወለተ ጴጥሮስ (ስንክሳር ህዳር 17)
 ጸዋሬ ክርስቶስ የሆነችው ኢትዮጵያዊቷ ቅድስት ፀበለ ማርያም
የሴቶች አገልግሎት በዘመነ
ሊቃውንት

 በቅኔው ዘርፍም ድንቅ ታሪክን ያስመዘገበችው እማሆይ ሃይመት፣
 ሴቶች በመንፈሳዊው ዕውቀትና በማስተማሩም ሥራ ታላቅ ድርሻ ማበርከት እንደሚችሉ
አርአያዎች በዘመናችንም ያሉት
 መምህርት ጥዕምተ ዜማ፣
 መምህርት ሶስና በላይ ፣
 መምህርት ሕይወት ፀሐይ ናቸው።
 ያሳዩት አርአያነት ሴቶች ከባድ በሚባለው የቅኔ ዘርፍ ሳይቀር በማስተማር ጉልህ ድርሻ
ሊኖራቸው እንደሚችል ማረጋገጫዎቻችን
 እማሆይ ገላነሽ ፣
 ቀጥሎም የመጡት ሴት የቅኔ መምህራን
 እማሆይ ኅሪትና
 እማሆይ ወለተ ሕይወት ናቸው።
 ብዙ ቅዱሳት መጻሕፍትን ለቤተክርስቲያን ያበረከቱት እቴጌ እሌኒ

ቅድስት ፀበለ ማርያም




You might also like