Professional Documents
Culture Documents
2009 .
2009 .
ክፍል 1
የ 2008 ዓ.ም የወረዳው አጠቃላይ ትምህርት ዋና ዋና እቅዶች አፈፃፀም የሁኔታ ግምገማ
የአጠቃላይ የትምህርት ጥራት ፓኬጅ :-
በትምህርት ዘመኑ በወረዳው የአጠቃላይ ትምህርት ጥራትን በማሻሻልና የምዕተ ዓመቱን ግብ በውጤታማነት በመፈፀም የብቁ ዜጋ
ማፍራት ተልዕኮን የማሳካት ወሳኝ ግብ ዕውን ለማድረግ የልማትና የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታችን ለማፋጠን ዓመታዊ እቅድ ተዘጋጅቶ ነበር
፡፡ ይህም እቅድ የአጠቃላይ ትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ፣ የትምህርት ሽፋንን ለማሳድግ በሀገር አቀፍ ደረጃ የተዘጋጁትን መርሃ-ግብሮች
መነሻ በማድረግ ከወረዳችን ተጨባጭ ሁኔታ ጋር ተገናዝቦ በዋና ዋና ግቦችና ተግባራት ታቅዷል::
የአጠቃላይ ትምህርት ጥራት ማረጋገጫ ፓኬጅ አፈፃፀም ቁልፍ ተግባራት (70%) የወረዳውን አጠቃላይ የትምህርት ጥራት ማስጠበቅ
ተግባር ከክልል ት/ቢሮ መነሻ በማድረግ በውስጡ የተካተቱትን
ሲደረግ ቆይቷል፡፡
በዚህ መሰረትም የተለያዩ የአጭርና ረጅም ጊዜ የአቅም ግንባታ ስልጠና በመስጠት በትምህርት ቤት ውስጥ ያሉ ልዩ ልዩ አደረጃጀቶችን
ማጠናከርና ምርጥ ተሞክሮዎችን በመቀመርና በማስተላለፍ እንዲሁም ከወረዳው ትም/ጽ/ቤት እስከ ት/ቤት ድረስ የትምህርት አመራሩን
የማብቃትና ውጤታማ የሆነ የአሰራርና አደረጃጀት ስርዓቱን ለማጠናከር የሚያስችል ተግባራት ታቅደው ተተግብረዋል፡፡
የወረዳው ትም/ቤቶች በሙሉ በአግባቡ ተመርጠው በቋሚነት በተመደቡ ር/መምህራንና ሱፐርቫይዘሮች እንዲመሩ በማድረግና
ተከታታይ ስልጠና በመስጠት ለትምህርት ተቋማት ባለቤት እንዲኖራቸው ተደርጓል ፡፡ይኸውም ካሉት 81 የመንግስት አንደኛ ደረጃ
ት/ቤቶችና አንድ የግል ት/ቤት እንዲሁም 2 2 ኛ ደ/ት/ቤቶች በጥቅሉ 76 ት/ቤቶች በቋሚ ር/መምህር የሚመሩ ሲሆን እነዚህ 83 ት/ቤቶች
በ 20 ጉድኝት ማዕከላት የተመደቡ ሲሆን 15 ቱ ጉድኝቶች ሱፐርቫይዘር እንዲኖራቸው ተደርጓል፡፡
በአጠቃላይ ከወረዳ ትምህርት ሴክተር አደረጃጀትና አመራሩ ከጽ/ቤት እስከ ት/ቤት ድረስ የአጠቃላይ ትምህርት ጥራት ማረጋገጫ
ፓኬጅ መርሃ-ግብሮችን ለመምራት በሚያስችል መልኩ የተደራጀ ቢሆንም በቀጣይነት ተልዕኮውን በውጤታማነት መምራት የሚችሉ
ት/ቤቶች የብቁ ዜጋ ማፍራት ተልዕኳቸውን እንዲወጡ በስነ- ምግባራቸው፣በሙያቸው፣በአመራር ብቃታቸው ፣በስራ ተነሳሽነታቸው
የትምህርት ሀብትን በአግባቡ ስራ ላይ ማዋል የሚችሉት የት/ቤት ጠንካራ አሰራር ሲኖር በመሆኑ አጫጭር ስልጠናዎችን መስጠት
ይጠበቃል፡፡
በሁሉም ትምህርት ቤቶች በበጀት ዓመቱ ተማሪዎች ያለባቸውን የአቅም ችግር በመለየት እንዲበቁ ለማድረግ
ሰፊ ስራዎች ሲሰሩ የቆየ ሲሆን
-በተፈጠረው የወረዳ የጸጥታ ችግር በትምህርት ቤት ውስጥ ሰላማዊ የመማር ማስተማር ችግር መኖርና ይህን
ምክንያት በማድረግ ተማሪዎች በተደጋጋሚ ት/ቤት አለመገኘት
-የትምህርት ክፍለ-ጊዜ በምክንያትና ያለበቂ ምክንያት መባከንና የባከኑትንም በአግባቡ ተይዘው አለመካካሳቸው
-የተማሪ ውጤት ማሻሻል ማለት የቁጥር እድገት ብቻ አድርጎ ማየትና ተማሪዎችን ሁለንታናዊ
እውቀት፣አመለካከት፣ክህሎትና የባህሪ ለውጥ ማምጣት መሆኑን አለመረዳት
ስለሆነም በሚቀጥለው ዓመት በዚህ መርሀ-ግብር ዙሪያ ውጤታማ ስራ በመስራት በተማሪዎች ላይ ተጨባጭ ለውጥ
ለማምጣት ሁሉም የትምህርት ቁልፍ ባለድርሻ አካላት ርብርብ ማድረግ ይገባቸዋል፡፡
- በወረዳችን የትምህርት ቤት ግቢዎችን ማራኪ የማድረግ ተግባራዊነት በጣም አናሳ መሆኑ ይታዎቃል፡፡ ስለሆነም በዚህ ተግባር ከፍተኛ
ስራ መስራት ይጠበቃል፡፡
-ወሳኝ የሆኑ የትምህርት ቤት የውስጥ ድርጅት የማሟላት፣ቤተ-መጽሀፍት /ፈርኒቸር ፣መጻህፍት፣የትምህርት መርጃ መሳሪያ፣ልዩ ልዩ
አገልግሎት ወዘተ/
-ወላጆችን በትምህርት ጥራት ላይ እንዲመክሩ በማድረግ
-ለተማሪዎች ድጋፍ ስርዓት ዘርግቶ ማስተማር በተለይ ማንበብና መፃፍ የማይችሉ ከ 2-5 ኛ ክፍል ተማሪዎችን ለይቶ በማስተማርማብቃት፣
- የመማሪያ መፅሃፍትን በመገምገም ረገድ ጥሩ ጅምሮች መታየት ቢጀምሩም ቀጣይነት እንዲኖራቸው በቁርጠኝነት መነሳት
ይኖርብናል፡፡
3. የመምህራን ልማት መርሃ-ግብር
መምህራንና የትምህርት ባለሙያዎች ተገቢውን አካዳሚካዊ እውቀት ሙያዊ ስነ- ምግባርና አዎንታዊ አመለካከት በተከታታይ የሙያ
ማሻሻያ መርሃ-ግብር እንዲያጎለብቱ በማድረግ የተማሪዎችን ውጤት ለማሻሻልና የትምህርት ጥራትን ለማጎልበት የስራ ላይ ስልጠና
አስፈላጊነቱ የጎላ ነው፡፡ በመሆኑም በወረዳው ያሉ መምህራን
አግኝተው ለዞን ተልከው ሢያልፉ ምዘናውን ለማለፍ በመጠባበቅ ላይ ይገኛሉ፡፡ በተጨማሪም በ 2008 ዓ.ም የዕጩ
መምህርነት ምልመላ ወ 54 ሴ 65 ድ 119 ዕጩ መምህራን በውጤታቸው ተመልምለው
ፈተና ጭልጋ ወረዳ እንዲወስዱ ተደርጎ ከወረዳችን በክልል ደረጃ በተደረገው
ማጣርያ በጥቅሉ ወ 31 ሴ 25 ድ 56 ብልጫ በማግኘት አልፈው በዝርዝር ሲታይ
በአዲሱ ሞዳሊቲ ዲፕሎማ ወ 30 ሴ 18 ድ 48 በልዩ ፍላጎት ዲሎማ ወ-1 ሴ- ድ
1፣ቅ/መደበኛ ዲፕሎማ ወ - ሴ 1 ድ 1፣ቅ/መደበኛ ሰርትፍኬት ወ - ሴ 6 ድ 6 ዕጩ
መምህራን ወደ ጎንደር፣እንጂባራና ወልዲያ ኮሌጆች መገጣጠሚያ ደብዳቤ ተሰጥተው
ሲላኩ በተለያዬ ደረጃ ለፈተና ቀርበው ላላለፉ ዕጩዎች ደግሞ የት /ርት ማስረጃቸው
በወቅቱ እንዲመለስ ተደርጓል፡፡
የአፍ መፍቻ ቋንቋ ስልጠና በአንደኛዉ ዙር ወ-26 ሴ-23 ድ-49 መ/ራን እና በሁለተኛዉ ዙር ወ-27 ሴ-23 ድ-50 መ/ራን
ስልጠና ወስደዋል::
በዞን ደረጃ ለ 10 ቀን ር/መ/ር 1 ኛ ደረጃ ወ-79 ሴ-1 ድ-80፣ 2 ኛ ደረጃ ወ-2 ሴ- ድ-2 በድምሩ ወ-81 ሴ-2 ድ-83 እና
ር/መ/ር ወ-2 ሴ- ድ-2፣ ሱ/ር 1 ኛ ደረጃ ወ-13 ሴ-0 ድ-13 እና 2 ኛ ደረጃ ወ-2 ሴ-0 ድ 2 በድምሩ ወ-15 ሴ-0 ድ 15 ስልጠና
ወስደዋል፡፡
በሌላ በኩል ወ-19 ሴ-23 ድ-42 መ/ራን በወረዳ ደረጃ በአሳታፊ የመማር ማስተማር ስነ ዘዴ ላይ ስልጠና ተሰጥቷል፣
በህፃናት አድን ድርጅትና በት/ት ቢሮ ትብብር "የ 1 ኛ ደረጃ ት/ት የንባብ አሰጣጥ
ደረጃ ማሻሻል" በሚል ርዕስ ስልጠና ተዘጋጅቶ ለ 2 ቀን ወ 8 ሴ 18 ድ 26 መ/ራን
ሲሰለጥኑ በልዩ ፍላጎት ት/ት ስልጠና 3 ሴት መ/ራን በደብረ ብርሃን ት/ት ኮሌጅ
ስልጠናውን አጠናቀው ተመልሰዋል::
በ 47 የ 1 ኛ ደረጃ ት/ቤቶች በተከታታይ ምዘና ፅንሰ ሃሳብ፣ የተሙማ ፅንሰ ሀሳብና አተገባበር ላይ ስልጠና ተሰጥቷል።
በ 4 ጉድኝት ማዕከል በ SIP/በት/ቤት ማሻሻል ምንነት ላይ ስልጠና ተሰጥቷል።
በ 2 ቱም ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች ላይ በተሙማ ፅንሰ ሀሳብና አተገባበር እና በተከታታይ ምዘና አያያዝና አተገባበር ፣ በኮኪት 2 ኛ
ደረጃ ት/ቤት የዕቅድ አዘገጃጀትና አጠቃቀም እና በሽንፋ 2 ኛ ደረጃ በአሳታፊ የመማር ማስተማር ስነ ዘዴ እንዲሁም በት/ቤት
ማሻሻል ዙሪያ ስልጠና ተሰጥቷል።
በጎንደር ዩንቨርሲቲ ድጋፍ ወ-4 ሴ- ድ-4 የ 2 ኛ ደረጃ መ/ራን በአሳታፊ መማር ማስረተማር፣ በተግባራዊ ጥናትና ምርምር፣
በተከታታይ ምዘና እና ተሙማ ዙሪያ የ 5 ቀን ስልጠና ተሰጥቷል።
በተማሪዎች ስነ-ምግባርና ደንብ ስልጠና የተሰጠ ሲሆን ተሳታፊ ተማሪ ወ 320 ሴ 567 ድ 1083 (3 ት/ቤት)
በሁሉም ት/ቤት ስቁጠባ ባህል ዙሪያ ለማህበረሰቡ ስልጠና ይሰጣል ፡፡ በመሆኑም በተሰጠው ግንዛቤ መሰረት በ 7 ተቋማት
ተማሪዎች 16647 ብር የመቆጠቢ ደብተር በመክፈት ማስቆብ ተችሏል
በት/ቤቱ የሰላም ኮሚቴ በማቋቋም የሚያጋጥሙ ችግሮችን እርስ በእርሳቸው እንደረዳዱ ተደርገዋል ፡፡
የመፅሀፍ እጥረት ለመቅረፍ 40 አጋዥ መፅሀፍ በመግዛት ተችሏል፡፡ ከዚህ በጠጨማሪ ከት/ቤት ት/ቤት ከጉድኝት
በ 18 ት/ቤቶች የፀረ-ኤድስ ቀን በደማቅ የተከበረ ሲሆን ተሳታፊ ወላጅ ወ 511 ሴ 475 ድ 986 መ/ር ወ 102 ሴ
77 ድ 197 ተማሪ ወ 3038 ሴ 3093 ድ 6131
በስነ-ምግብ ዙሪያ ለ 1 ሰዓት ባለሙያ በመጋበዝ ከዲዋርሚንግ ክትባት ጋር በማያያዝ ለ ወ 62 ለሴ 32 ድ 94 መ/ራን
ስልጠና ተሰጥቷል ፡፡
በህፃናት ደህንነትና እንክብካቤ በወረዳ ደረጃ የሠለጠኑ መ/ራን በት/ቤት ደረጃ ስልጠና የሰጡ ሲሆን መ/ር ወ ሴ 6 ድ 10 ተማሪ
ወ 190 ሴ 257 ድ 447
አለም አቀፍ የህፃናት ቀን በ 16 ት/ቤት የተከበረ ሲሆን መ/ር ወ 66 ሴ 79 ድ 145 ተማሪ ወ 2229 ሴ 2484 ድ 4713 ወላጅ
ወ 841 ሴ 237 ድ 1078 ጠ/ድ ወ 3136 ሴ 2800 ድ 5936
የንባብ ክበብ መቋቋሙ ለተማሪዎች ውጤት ወሳኝ መሆኑ ይታወቃል ፡፡ በመሆኑም በየካቲት ወር ቸክሊስት አውርደን እስካሁን
በ 16 ት/ቤቶች ክበቡን በመመሪያው መሰርት በማቋቋም ወደ ተግባር ተገብተው በቁጥር አዘል የላኩልን ተማሪ ወ 289 ሴ 318
ድ 607 መ/ር ወ 17 ሴ 10 ድ 27 የክበቡ ተጠሪ ወ 8 ሴ 2 ድ 10 ናቸው ፡፡
ከሳይንስ እና ቴክኖሎጅ ፈጠራ አኳያ በአካባቢው ቁሳቁስ በመታገስ የሙቀት መለኪያ ( ቴርሞሜትር መስራት ተችሏል ፡፡(ጉባይ
ት/ቤት)
ስለሆነም በወረዳችን በሁሉም ት/ቤት በሚሞሪ በተቀረፀ ት/ት በሬድዮ ይሰጣል፡፡ የተበላሸ ሚሞሪ ላጋጠማቸው
ት/ቤቶችም እንደገና እንዲቀረፅ ተደርጓል :: ከዚህ ሌላ ለ 8 ሙሉ ሳይክል ት/ቤቶች ኮምፒውተር በወረዳው አልማ
ድጋፍ እንዲሰጣቸው ተደርጓል ፡፡
51.73% ደርሷል፡፡በሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች ወ 617 ሴ 668 ድ 1298 ተማሪዎችን ለማስተናገድ ታቅዶ ክንውኑ ወ 569 ሴ 614
ድ 1183 ሲሆን አፈፃፀሙም 91.14% ሆኖ የሴቶች ድርሻ 51.90% ነው፡፡በመማር ላይ ያሉ ወ 569 ሴ 614 ድ 1183 አፈፃፀም 91.14%
ነው፡፡
-ህብረተሰብ አቀፍ ቅድመ-መደበኛ ትምህርት መርሀ-ግብርን በሁሉም የወረዳችን ትምህርት ተቋማት ውስጥ በመክፈትና ከ 4-6 ዓመት እድሜ ክልል ውስጥ
ያሉ 9765 ህፃናትን ለመደበኛ ትምህርት ማዘጋጀት፡፡ በዚህም ህ/ሰብ አቀፍ ቅድመ-መደበኛ ዕቅድወ 4820 ሴ 4945 ድ 9765 ክንውን ወ 1618 ሴ
1613 ድ 3231 አፈፃፀም በ% 33.08 (በ 69 የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤቶ የተፈፀመ)፡፡በአፀደ-ህፃናት ደግሞ ዕቅድ ወ = 739 ሴ = 669 ድ = 1408
ክንውን ወ = 391 ሴ = 366 ድ= 757 አፈፃፀም በ% 53.76 (በ 4 የመንግስት ና በ 1 የግል ት/ቤቶች የተፈፀመ)፡፡
-የጎልማሶች ትምህርትን በሁሉም ቀበሌዎች በማስፋፋት ሁሉንም ጎልማሶች የትምህርት ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በዕቅድ ተይዞ
-ደረጃ 1 ዕቅድ ወ = 15623 ሴ = 7883 ድ= 23506 ክንውን ወ= 1641 ሴ= 1264 ድ= 2905 አፈፃፀም በ% 12.35 %
-ደረጃ 2 ዕቅድ ወ=2535 ሴ= 1084 ድ = 3619 ክንውን ወ = 854 ሴ = 673 ድ = 1527 አፈፃፀም በ% 42.19%
-ጥቅል ደረጃ 1-2 ዕቅድ ወ= 17293 ሴ= 16120 ድ = 33413 ጥቅል ክንውን 1-2 ወ= 1641 ሴ= 6149 ድ= 13870 አፈፃፀም በ% 68.58
ሲሆን ትምህርቱን የሚያስተምሩ ወ= 18 ሴ= 93 ድ= 111 አመቻቾች በወረዳው በጀት ተቀጥረዋል፡፡ ለ 588 ልዩ ፍላጎት
ያላቸው ተማሪዎች በሶስት ትምህርት እንዲሰጥ ለማድረግ በዕቅድ ተይዞ ወ= 27 ሴ= 27 ድ=54 ልዩ ፍላጎት ያላቸው
ተማሪዎች በ 3 ዩኑት ትምህርት እየተሰጠ ነው፡፡
ለዚህ ውጤት መብቃት ዋና ዋና ምክንያቶች
የስራ ሂደቶች ወቅቱን በጠበቀ መልኩ ሂደቱን በሚመለከቱ መረጃዎች አጠናክሮና አፋጣኝ ሪፖርቶችን
አለመላክ እንዲሁም የሚላኩት ሪፖርቶች የሚፈለገውን መረጃ ያሟሉ አለመሆን
በወረዳ የሰላም ችግር ከመኖሩ አንጻር ት/ቤቶች ተረጋግተው ያለማስተማር ችግርና ሳምናታዊ፣ወርሃዊና የሩብ
ዓመት ሪፖርትና ይዘቱን የጠበቀ ሪፖርት አለመላክ
በሰላም እጦት ከወረዳው 30 የሚጠጉ ት/ቤቶች ለተወሰነ ጊዜ መዘጋትና 2 ት/ቤቶች ተ/ቤቶች ተዘግተው
መቅረት፡፡
የተወሰዱ መፍትሄዎች
በደብዳቤ በማሳወቅ ወቅቱን ጠብቀው ማለትም ወሩ በገባ እስከ 20 ኛው ቀን ወርሃዊ ሪፖርት እንዲልኩ
ተደርጓል፡፡
ሙያተኛው ህይወቱን ሰውቶ ት/ቤቶች እንዲረጋጉየመስክ ስምሪት መደረጉና በግብረ-መልስ፣በስልክና በስብሰባ
አጋጣሚዎች ሪፖርታቸውን እንዲያሻሽሉ ጥረት ማድረግ
በመስክ ሙያተኛውና አመራሩ ብዙ ጊዜ ሳይወስዱ እንዲከፈቱ ለሁለቱ ግን የሚቻለው ጥረት ተደርጎ ሳይሳካ
ቀርቷል፡፡
ክፍል 2
ራዕይ፡-
ትምህርትና ስልጠናን በስፋት በማዳረስ ስብዕናው የተሟላ የስራ ባህልን ያሳደገ ብቁ ዜጋ ተፈጥሮ ማየት
ተልዕኮ፡-
የዕቅዱ ዋና ዋና አላማዎች/Aims/
የትምህርት ጥራትን በማስጠበቅ የብቁ ዜጋ ማፍራት ተልዕኮን ማሳካት፣
የትምህርት ሽፋንንና ጥራትን ማሳደግ፣
የትምህርት ፍትሀዊነትን ማረጋገጥ፣
የትምህርት ብቃትን ማሻሻል/ማሳደግ/፣
የዕቅዱ ዝርዝር አላማዎች
-የዘመኑን ዕቅድ ለመፈጸም በመሳሪያነት የምንጠቀመዉ የመሰረታዊ ሥራ ሂደት ለዉጥ ጥናት ዉጤቶችን ነዉ፡፡ በጥናቶች ማስተግበሪያ
ማንዋሎቻችን ደግሞ ግልፅ የሆኑ መርሆችን አስቀምጠናል፡፡ በመሆኑም ዕቅድ ዝግጅቱ፣ትግበራዉ፣ የክትትልና ድጋፍ ሥርዓቱም ሥራ
ሂደት ተኮር መሆን ስላለበት የሚከተሉትን የተወሰኑ መርሆች እንከተላለን ፡፡ ሌሎችንም እንደ ሁኔታዉ መጨመር ይቻላል፡፡
አመራር ሰጭነት፡- ፓኬጁ የአመራሩን የበላይ ሚና በጉልህ አመልክቷል ፡፡ በመሆኑም አመራሩ ድርሻዉን በተገቢዉ መንገድ
ሊወጣ ይገባል፡፡
የግብ ስኬት (Outcome based) ፡-አተኩሮ መንቀሳቀስ የፓኬጁም ሆነ የምዕተ ዓመቱ ግቦች ስኬት የሚለካዉ ብቁ ዜጋ
ማፍራት ላይ ነው፡፡ ግብዓትና ሂደት ለትምህርት ጥራት ወሳኝ ቢሆንም መቋጠሪያው ግን ውጤት ላይ ማጠንጠን ይሆናል፡፡
ደንበኛ ተኮር( customer focused) :- መሆን በትምህርት ሴክተር ዋና ደንበኞች/ ተማሪ፣ መንግስትና ወላጅናቸው፡፡
በመሆኑም ስናቅድ፣ስንተገብር፣ስንገመግም የደንበኛውን ፍላጎት ያማከልን መሆናችንን ማረጋገጥ ይኖርብናል፡፡
ብቃትን ማሳደግ (Empowerment ) :- ፈፃሚ የመወሰን አቅሙን ለማሳደግ ማበረታታትና የኃላፊዎችን ደጋፊነት ሚና
ማጠናከር፣
የመረጃ አጠቃቀምን ማሻሻል (Improve ICT using system)፡- መረጃን በአግባቡና አማክሎ በማደራጀት ለፓኬጁ
አፈፃፀምም ሆነ ለአብይ ተግባራት ትንተና በአግባቡ መጠቀም፣
የመረጃና መገናኛ ቴክኖሎጅ (ICT) አጠናቅሮ መጠቀም ፡- ከከተማ አስከ ት/ቤት በአጠቃላይ ስራችንን ማሳለጫነቱን
በመረጃነት የላቀ ተጠቃሚ መሆናችን እያረጋገጥን መሄድ፣
አሳታፊነት(participatory) ፡- የትምህርት ስራ በባህርይው የብዙ ባለድርሻዎችን ተሳትፎ የሚጠይቅ ከመሆኑ በላይ ፓኬጁም
ይህንኑ የተግባር ግዴታ ስለሚያመለክት ልዩ ትኩረት እንሰጠዋለን፡፡
ችግር ፈችነት ( problem solving) ፡-እቅዶቻችን አቅደን ወደ ተግባር ስንገባ የሚያጋጥሙ ችግሮች በርካታ ናቸው፡፡
ኃላፊዎች በተለይም በየጊዜው ለችግሮች አስቀድመው የመተንበይ እና መፍትሄ ሰጭነት ባህል መላበስ ይኖርብናል፡፡
ግልፀኝነትና ተጠያቂነት(Transparncy & Accountability) ፡- ተልዕኳችን ግልጽ ነው፡፡ ውጤታችንም ተመሳሳይ ሊሆን ይገባል፡፡
ከዚህ በየደረጃው የሚጠበቅበትን ውጤት ያላስመዘገበ ደግሞ ቅድሚያ ለህዝብ ጥቅም ሲባል ተጠያቂ ሊሆን ይገባል፡፡
የማትጋት ስርዓት ( Reward ) :- መልካም አፈፃፀሞች ትኩረት ይሻሉ፡፡ ለእነሱም እንደ ግለሰብም ሆነ ተቋማዊ በሆነ መልኩ
ዘወትር ልንለያቸው፣ልናበረታታቸውና ለሌሎች ልናስተላልፈው የምንችለውን የማትጊያ ስርዓት አቅደን ስንተገብረው
ይሆናል፡፡
የእቅዱ ተፈፃሚነት ወሰን( Scope of the plan)
ከወረዳ ትም/ጽ/ቤት እስከ ት/ቤትና ቀበሌ ድረስ ያሉትን ፈፃሚና አስፈፃሚ አካላትን እንዲሁም ባለድርሻዎች የሚተገብሩትን
ተግባራት ያካትታል፡፡
የትምርት ሴክተር የልማት ሰራዊት በሁሉም የት/ተቋማት በመፍጠር በተቀናጀ እንቅስቃሴ የአጠቃላይ ትምህርት ጥራት ፓኬጁን
በውጤታማነት ማስፈፀም፣
ከመንግስት የሚደብ መደበኛና ካፒታል በጀት /ብሎክ ግራንት/ና ከበጎ አድራጊ ድርጅቶች በሚገኝ በጀት
ከትምህርት ተቋማት የሚገኝ የውስጥ ገቢ
ክፍል 3
የ 2009 ዓ.ም የአጠቃላይ ትምህርት ዕቅድ
ቁልፍ ተግባር:- የተደራጀ የት/ት ልማት ሠራዊት መፍጠር 70%
ግብ 1፡- በ 2009 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የትምህርት ልማት ሰራዊት በመገንባት የአጠቃላይ የትምህርት
ጥራት ማረጋገጫ ፓኬጅን በውጤታማነት በመፈፀም ሁሉም ተማሪዎች በሁሉም የክፍል ደረጃዎችና
የትምህርት አይነቶች 50 እና በላይ ውጤት እንዲያስመዘግቡ ማድረግ፡፡
ተግባር 1፡- በተደራጀ የትምህርት የልማት ሰራዊት የተማሪዎች ውጤት በሁሉም የትምህርት ዓይነት ሁሉም
ተማሪዎች 50℅ እና ከዚያ በላይ ማስመዝገብ፣
ተግባር 2፡- በሂደት ደረጃ የ 1 ለ 5 ዕቅድ ተዘጋጅቶ በሂደቱ አባላት የጋራ በማድረግ ወደ ተግባር ማስገባት፣
ተግባር 3፡-ሁሉም ትምህርት ቤቶች የተደራጀ የትምህርት ልማት ሰራዊትን ያካተተ ዕቅድ አዘጋጅተው ወደ ስራ
እንዲገቡ ማድረግ፣
ተግባር 4፡-በሁሉም ትምህርት ቤቶች የተማሪና የመምህራን የ 1 ለ 5 ና የልማት ቡድን አደረጃጀት ማደራጀት፤፣
ተግባር 5፡- ወመህ እና ቀትስቦ ት/ቤቶችን በባለቤትነት መንፈስ እንዲመሩ ግንዛቤ በመፍጠር፣ በተግባርና በየሃላፊነታቸው
የአቅም ማጎልበቻ አጫጭር ስልጠና በመስጠት በየወሩ እየተገናኙ ት/ቤቶችን እንዲመሩ ማድረግ፡፡
ግብ አንድ ፡-
በት/ቤቶች አጠቃላይ የት/ት ጥራት ማስጠበቂያ ኘሮግራምና የምዕተ ዓመቱን ግብ አቀናጅቶ
ተግባር 1፡- አዲስ ለተቀጠሩ የጉድኝት ሱፐርቫይዘሮች ውጤት ተኮር ውል መስጠትና እነሱም በተዋረድ ለር/መ/ራን
እንዲሰጡና የአፈፃፀም ውጤትንም መሙላት፣
ግብ ሁለት ፡-
ት/ቤቶች በብቁና ለደረጃው በሚመጥኑ፣በአግባቡ በተመረጡና በሰለጠኑ ር/መ/ራንና
ሱፐርቫይዘሮች እንዲሁም በሌሎች ልዩ ልዩ አደረጃጀቶች እንዲመሩ ማድረግ፡፡
ተግባር 1፡- ከ 1-8 ባሉ ት/ቤቶች 63 የክላስተር ዲፕሎማ መምህራን፣10 ር/መ/ራን፣5 ሱፐርቫይዘሮችና ለ 2 ኛ ደረጃ ት/ቤቶች
6 ድገፍ ሰጭ ሰራተኞችን በአዲስ ቅጥር በመፈፀም በወቅቱ እንዲመደብላቸው ማድረግና ት/ቤቶች የተፈለገውን ግብ
እንዲመቱ ማድረግ፣
ተግባር 2፡- የረዥም ጊዜ የስራ ላይ ስልጠና ያልጀመሩትን ር/መ/ራንና ሱፐርቫይዘሮች ከዞን በሚሰጠው ኮታ መሰረት የክረምት
ትምህርት በማስጀመር ለሚመሩት ት/ቤት ደረጃቸውን ብቁ ማድረግ፣
ተግባር 3፡- ሁሉም ሱፐርቫይዘሮችና ር/መ/ራን ከዞን በሚመጣ በወረዳ ደረጃ በሚዘጋጅ የአጭር ጊዜ ልዩ ልዩ ስልጠና እንዲያገኙ
ማድረግ፣
ተግባር 1፡- የዞኑ የመርሱ ልማት ዋና የስራ ሂደት በሚልከው የእጩ ሰልጣኝ መ/ራን ምልመላና መረጣ ኘሮግራም በሚሰጠው
ኮታ መሰረት ማስታወቂያ በማውጣት ጥሪ ተደርጐ በሚዘጋጀው ስታንዳርድ መሰረት በመመዝገብ ለሚመለከታቸው አካላት
መላክ፣
ተግባር 2፡- በኮሌጆች የቃልና የፅሁፍ ፈተና አልፈው የተሰጠውን ክልል አቀፍ መረጣ ላለፉ ሰልጣኞች እንዲገለፁና እንዲሁም
የተመደቡበትን ኮሌጅና የመመዝገቢያ ቀን ለሰልጣኞች በወቅቱ ማሳወቅ፣
ግብ አራት፡-
በወረዳው ከሚገኙ ት/ቤቶች በማስተማር ላይ ከተሰማሩት መ/ራን በት/ት ደረጃ ማሻሻያ ስልጠና ኘሮግራሞች
በማሳተፍ ተገቢውን አካዳሚያዊ እውቀት፣ሙያዊ ስነ-ምግባርና አወንታዊ አመለካት ያላቸው መ/ራንን
ማፍራት፡፡
ተግባር 1፡- በመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤቶች በማስተማር ላይ ያሉ የዲፕሎማ መ/ራን ከዞን ትም/መምሪያ በሚሰጠን ኮታ መሰረት
በመመልመል በዲኘሎማ ደረጃ በሊኔየርና በክላስተር እንዲሁም በዲግሪ ኘሮግራም እንዲከታተሉ ማድረግ፣
ግብ አምስት፡-
መ/ራን በተግባር መሳሪያዎች ቋት የሙያ ማሻሻያ ኘሮግራም ስልጠና ሂደት በማሳተፍ አካዳሚያዊ
እውቀታቸውንና ሙያዊ ስነ-ምግባራቸውን በማሻሻል ሀላፊነታቸውን የሚወጡና በራሳቸው እንዲተማመኑ
ማስቻል፡፡
ተግባር 1፡- በኘሮግራሙ አተገባበር ላይ የነበሩ ችገሮችን በመፍታት መ/ራን የተግባር መሳሪያ ሙያ ማሻሻያ ኘሮግራም
ተግባራት በት/ቤትና በጉድኝት ማዕከላት በአግባቡ ፈፅመው የተማሪዎችን ውጤት የማሻሻል ስራ ተጠናክሮ እንዲቀጥል
ማድረግ፣
ተግባር 2፡- አዲስ ለሚቀጠሩና ለነባር መ/ራን በተመደቡበት ት/ቤት የሙያ ትውውቅ ኮርስና
ተግባር 3፡- አዲስ ለሚከፈቱ ት/ቤቶች ለተግባር መሳሪያዎች ቋት ስልጠና አጋዥ የሚሆኑ የስልጠና ቁሳቁሶችን ለት/ቤቶች
አባዝቶ እንዲዳረሱ ማድረግ፣
ተግባር 4፡- ስልጠናው በአግባቡ እንዲካሔድ ክትትልና ሙያዊ ድጋፍ ተደርጐ ጠንካራና ደካማ
እንዲረጋገጡ ማድረግ፣
ተግባር 6፡- የኘሮግራሙ የሩብ አመት፣የ 6 ወርና ዓመታዊ የመረጃ አያያዝና ሪፖርት
ግብ ስድስት፡-
በወረዳው ውስጥ ያሉ መ/ራን የስልጠና ፍላጐታቸውንና ያሉባቸው የአቅም ክፍተት ተለይቶ ወቅታዊ አጫጭር
ስልጠና በመሰጠት ተጨማሪ አቅም መፍጠር፡፡
ተግባር 1፡- የስልጠና ፍላጐት ከልዩ ልዩ መረጃዎች መ/ራን ካለባቸው የአቅም ክፍተት
ተግባር 3፡- ስልጠናውን ለመስጠት ሞጁሎችን ማዘጋጀትና አጋዥ የሆኑ ግብዓቶችን ማሟላት፣
ተግባር 4፡- ስልጠናው ያመጣውን ለውጥ በመገምገም ደካማና ጠንካራ ጎኖችን በመለየት
ግብ ሰባት፡-
ተግባር 1፡- የመርሱ ዝውውርን ለመስራት ወቅቱን ጠብቆ የዝውውር መሙያ ቅፅ ለት/ቤቶች
ተግባር 2፡- ተሞልቶ የሚመጣውን የዝውውር መረጃ ማጠናከርና ወደ ዞን የሚላከውን በወቅቱ መላክ፣
ተግባር 3፡- ዝውውሩን በወቅቱ፣ግልፅ በሆነ መንገድና አግባብ ያለው ቅሬታ በማያስነሳ ሁኔታ መስራት፣
ተግባር 4፡- የትምህርት ደረጃቸውን የሚያሻሽሉና የቆይታ ጊዜያቸውን አሟልተው የደረጃ እድገት
ተግባር 6፡- መ/ራን፣ር/መ/ራንና ሱፐርቫዘሮች በሚሰጡት አስተያየት መሰረት የተገልጋይ ፍላጎትን እንዲሻሻል ማድረግ፣
ተግባር 7፡- አግባብነት ያለቸውን ቅሬታዎች በመቀበልና በመመርመር አፋጣኝ ምላሽ መስጠት፣
ግብ ስምንት
ተግባር በሁሉም ደረጃ የሚገኙ መለስተኛና በመምህር ደረጃ ያሉ መምህራንን መመዘን፡፡ 1፡-
በሁሉም ደረጃ
ያሉ፣በመለስተኛ ደረጃና በመምህር ደረጃ የሚገኙ መምህራንን መለየት፣
ተግባር 2፡- ለተለዩት መምህራን ምዘና የሚሰጥ መዛኝ መለየትና ለስልጠና መላክ፣
ተግባር 3፡- ለተለዩት የተመዛኝ መምህራን የሚያበቃ የምዘና መሳሪያዎችንና የበጀት ዝግጅት ማከናወን፣
ተግባር 5፡- በስታንዳርዱ መሠረት ምዘናውን ላለፉ መምህራን የሙያ ፈቃድ መስጠት፣የሚጠበቅ ውጤት ተማሪዎች
ብቃታቸው በተረጋገጠ መምህራን ይማራሉ፣መምህራን ለስራቸው ይተጋሉ፣ለሙያቸው ክብር ይሰጣሉ፣
ግብ ዘጠኝ የይዘትና የፔዳጎጅ ምዘና ለወሰዱ ጀማሪ መምህራን የተግባር ምዘና ይሰጣል፡፡
ተግባር 1፡-
የይዘትና የተግባር ምዘና የተመዘኑ መምህራንን የስምሪት መረጃ ማደራጀት፣
ተግባር 2፡- ለተመዛኞች በቂ ሊሆን የሚችል መዛኝ መለየትና ስልጠና እንዲወስዱ ማድረግ፣
ተግባር 3፡- ለተመዛኞች የተዘጋጀውን ሩብሪክስ ለተመዛኞች ቀድሞ ስልጠና እንዲወስዱ ማድረግ፣
ተግባር 6፡- በተቀመጠው ስታንዳርድ መሠረት ውጤት ላመጡ መምህራን የሙያ ፈቃድ እንዲያገኙ ማድረግ፣የሚጠበቅ
ውጤት፡-ተማሪዎች ብቃታቸው በተረጋገጠ መምህራን ይማራሉ፣መምህራን ለስራቸው ይተጋሉ ለሙያቸው ክብር ይሰጣሉ፣
ተግባር 1 ፡- በወረዳው ውስጥ በአጠቃላይ ትምህርት በተለይም በትምህርት ቤት መሻሻል ላይ ባለድርሻ ለሆኑት
አካላት ተካታታይ ስልጠና መስጠት፣
ተግባር 2 ፡- ከወረዳ እስከ ት/ቤት ድረስ አዲስ ተመድበው፣ተቀጥረው ወይም ተዛውረው ለሚመጡ
ር/መ/ራን፣ሱ/ቫይዘሮችንና መምህራን የፅንስ ሀሳብና ተግባር ተኮር ስልጠና መስጠት፣
ግብ አስራ አንድ
ተግባር 1 ፡- ሁሉም የወረዳው ት/ቤቶች በዕቅድ ዘመኑ ያጠናቀቁትን ዓመታዊ የት/ቤት መሻሻል እቅድ
አዘገጃጀት፣አተገባበርንና ውጤት ግምገማ በማድረግ የቀጣዩን የሦስተኛ ዓመት ዕቅድ በአሳታፊነት
አዘጋጅተው ማፅደቅ፣
ተግባር 2 ፡- የት/ቤት ማሻሻያ መርሀ-ግብር ሂደት በመሆኑ የትምህርት ተቋማት ካለፉት አንድ ዓመት የዕቅድ ዝግጅት
ሂደት፣አተገባበር፣ከተገኝው የግብ ስኬት ግምገማ፣ውጤትና ለግምገማው ከተፈጠረው የግንዛቤ ለውጥ
መነሻ በማድረግ የስትራቴጅክ እቅድ ዋና ዋና ግቦችና ተግባራትን ክለሳ ማድረግ፣
2..1 በወረዳና በቀበሌ የተካሄዱትን መድረኮችና በአገር አቀፍ ደረጃ በታቀደው የእድገትና ትራንስፎርሜሽን
ዕቅድ የ 2009 ዓ.ም ዓመታዊ እቅድን መከለስ
2..3 በእቅድ ትውውቅ ላይ የተገኙ ባለድርሻ አካላትን በየደረጃው በቃለ-ጉባኤ አስደግፎ መያዝ
2..4 በእቅድ ትውውቅ በባለድርሻ አካላት የተነሱ ዋናዋና ጉዳዮችንና እቅዱን ለመተግበር የሚያጋጥሙ
ችግሮችና ለችግሮች የተሰጠ መፍትሄ የተፈጠረ መነሳሳትን ቀምሮ መያዝ
ተግባር 3 ፡- የት/ቤት ዓመታዊ የት/ቤት መሻሻል ዕቅድ በአራቱ አብይ ርዕስ ጉዳዮች በአስራ ሁለት ንዑሳን ርዕስ
ጉዳዮችና ሁሉንም ስታንዳርዶች መሰረት በማድረግና የግምገማ ትግበራውንና ሪፖርቱም ይህን አግባብ
የተከተለ ማድረግ፣
3.1 በት/ቤት ማሻሻያ አብይ ርዕስ ጉዳዮችንና ስታንዳርዶችን መምህራን በንቃትና በውጤታማነት ስለመሳተፋቸው
በየወሩ ግምገማ ማካሄድ
ተግባር 4 ፡- ዓመታዊ ዕቅድን ከአዲስ ት/ቤት ማሻሻያ ዕቅድ ግብ ጋር በማያያዝ ማለትም የመምህራንን ግብ
ከተማሪዎች ግብ ጋር ማስተሳሰር፣
ተግባር 7፡- በት/ቤት ደረጃ በየወሩ፣በጉድኝት ደረጃ 3 (በየሩብ አመቱ) በወረዳ ደረጃ 2 ጊዜ በትምህርት ሴሚስተር
መጨረሻ ላይ በትምህርት ቤቱ ማሻሻያ ውጤት ላይ ያለበትን ሁኔታ አጀንዳ አድርጎ መወያየት፣
7.1 በየደረጃው በተቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ መከናወኑን ማረጋገጥና በየጊዜው በግብረ-መልስ ማሳወቅ
ግብ ሁለት
ተግባር 1 ፡- 50/90 የት/ቤት ኮሌጅ ግንኙነት ውስጥ በሆነ መንገድ በት/ቤት ማሻሻያ መርሀ- ግብር እንዲሆን ማድረግ፣
1.1 የት/ቤት ማሻሻያ መርሀ-ግብር በውጤታማነት ለመፈፀም ተገቢውን ክትትልና ድጋፍ ማድረግ
ተግባር 2 ፡- በት/ቤት ውስጥ ያሉ መምህራንና ሰራተኞች በዘመኑ በት/ቤት ማሻሻል ኮሚቴ በአባልነት ይህንም ከአራቱ አብይ
ርዕስ ጉዳዮች በአንደኛ ንቁ ተሳትፎ የማድረግ ተቋማዊ ባህል መፍጠር፣
ተግባር 3 ፡- በወረዳችን ያለፉት ዓመታት የትምህርት ቅበላ የሶስት ዓመት ት/ቤት ማሻሻል የውጤት ጥናት በመስራት
ለማሻሻያ ግብዓትነት መጠቀም፣
ተግባር 4 ፡-የት/ቤት ማሻሻያ ዕቅድ ውጤትን ማደረጃጀትና በተገቢው መንገድ ጥቅም ላይ ማዋል፣
ተግባር 2 ፡- ወላጆች በዓመት ውስጥ በየ 2 ወሩ ለ 5 ጊዜ በመገኘት በት/ቤት ዕቅድ አፈፃፀምና በተማሪዎች ውጤት ላይ
እንዲወያዩና የድርሻቸውን እንዲወጡ ማድረግ፣
ተግባር 3 ፡- ከቀበሌ እስከ ወረዳ ያሉት የህዝብ ም/ቤቶችና የወረዳው አስተዳደር አካላት በዕቅድ ዘመኑ በፓኬጅ አተገባበር
ሪፖርት ቀርቦለት እንዲመክርና የድርሻውን እንዲወጣ ማድረግ፣
ተግባር 3 ፡- ከቀበሌ እስከ ወረዳ ያሉ ህዝባዊ ማህበራትና አደረጃጀቶች በየደረጃው ባሉ ተቋማት በፓኬጅ አተገባበር ሪፖርት
እንዲያመጡና ሚናቸውን እንዲጫወቱ ማድረግ፣
ግብ አስራ አራት በክፍል ውስጥ መማር-ማስተማር ሂደቱን በአዲስ የትምህርት ቤት ማሻሻል ማዕቀፍ
መሰረት እያሻሻሉ በመሄድ የተማሪዎችን ውጤት ማሻሻል፡፡
ተግባር 1 ፡- በወረዳው ውስጥ ያሉት ሁሉም የመጀመሪያ ሳይክል /1-4/ የክፍል ውስጥ አደረጃጀት ከነባር ዘዴ ወጥተው
አዲሱን ተማሪ ተኮር አማራጮች በሙሉ እንዲተገበሩ ማድረግ ፣
1.1 የተማሪ ተኮር የክፍል ውስጥ አደረጃጄቶችን በሁሉም የመጀመሪያ ሳይክል /ከ 1-4/ ት/ቤቶች ተግባራዊ ማድረግ፣
ተግባር 2 ፡- በወረዳው የሚገኙ የአንደኛ ክፍል አዲስ ገቢ ተማሪዎችን በአዲስ የክላስተር ክረምት ባጠናቀቁ መምህራን
እንዲማሩ ማድረግ፣
2፣2 ስልጠና ያጠናቀቁ የክለስተር ሰልጣኝ መምህራንን ከ 1 ኛ ክፍል ጀምሮ ወደላይ መመደብ
ተግባር 3፡- በወረዳው የሚገኙ የ 1 ኛ ክፍል ሴክሽኖች ውስጥ የክላስተር ቋንቋ ስልጠና የወሰዱ መምህራን እንዲመደቡ
በማድረግ በመንፈቅ ዓመቱ መጨረሻ የተማሪዎች የቋንቋ ክህሎት የሚጠብቀው ፕሮፋይል ላይ
እንዲደርስ ማድረግ፣
3.1 በመንፈቅ ዓመቱ መጨረሻ የተማሪዎች የቋንቋ ከህሎት የሚጠበቀው ፕሮፋይል ላይ እንዲደርስ
ከመምህራን ጋር ስምምነት ላይ ማድረስ፣
ተግባር 5 ፡- ተማሪዎች በዓመቱ ውስጥ በሙሉቀን የሚማሩት 1 ,075 ,30 ሰዓት በፈረቃ
የሚማሩበት ደግሞ 820 ሰዓታት ትምህርት ያገኙ መሆኑን ማረጋገጥ በበቂ ምክንያት ለሚቀሩ መምህራን
የተተኪ መምህራንን ስርዓት ዘርግቶ ተግባራዊ ማድርግ፣
5.2 የክፍለ ጊዜ ብክነት እንዳይፈጠር የተተኪ መምህራንን ስርዓት መዘርጋትና ተግባራዊ ማድረግ፣
ተግባር 6፡- በአጠቃላይ በወረዳው ውስጥ የሚገኙ ሙሉ ሳይክል ትምህርት ቤቶች የቤተ-ሙከራ አጠቃቀም በአግባቡ
ተቃኝቶና ተጠንቶ የሳይንስ ትምህርት ቤቶች የቤተ-ሙከራ አጠቃቀም በአግባቡ ተቃኝቶና ተጠንቶ
የሳይንስ ትምህርት በተሸለ መልኩ ለመስጠት የሚያስችል ስልት ቀይሶ ተግባራዊ ማድረግ
6.2 የሳይንስ ቤተ-ሙከራ / በሶስቱም ሳይንሶች / በሁሉም ሙሉ ሳይክል ት/ቤቶች በአግባቡ የሚጠቀሙበትን ስልት ቀይሶ
መንቀሳቀስ፣
ተግባር 7፡- ለመጀመሪያ ደረጃ 2 ኛ ሳይክል የቤተ-ሙከራ ስታንዳርድና አደረጃጀት ማንዋል በአሳታፊነት
አግባብ በማዘጋጀት ተገቢውን ትውውቅ በማድረግ ትምህርት ቤቶችን ማደራጀት፣
ተግባር 8፡- በወረዳው በሁሉም የመጀመሪያ ደረጃ መጀመሪያ ሳይክልና ንባብን የሚያሻሽሉ ስነ- ዘዴዎችን በመጠቀም ሁሉም
ህፃናት እንዲያነቡ ማድረግ፣
8.1 በትምህርት ዘመኑ መጀመሪያ ላይ ማንበብና መፃፍ ባለመቻላቸው ድጋፍ ለማድረግ የተለዩ ተማሪዎችን
መረጃ በአግባቡ መያዝና ለውጡን እየተከታተሉ ሪፖርት ማድረግ
ተግባር 9፡- በሁሉም የትምህርት ደረጃዎች የሳይንስና የሂሳብ ትምህርት አሰጣጥን በማሻሻል የተማሪውን ውጤት
ማሻሻል፣
9.1 የሳይንስና የሂሳብ ትምህርት አሰጣጥን ለማሻሻልና የተማሪዎችን ውጤት ለማሳደግ ከመምህራን ጋር በመወያየትና
ስምምነት በመድረስ እንዲሁም ልዩ ልዩ እቅድ አዘጋጅቶ ተግባራዊ ማድረግ
ተግባር 10፡- የመማር-ማስተማሩን ስራ ለማጠናከር የሚያስችል ጥናታዊ ፅሁፎችንና የፅንስ ሀሳብ ፅሁፎችን
እያንዳንዱን የትምህርት አይነት ሊያጠናከር በሚችል መልኩ ዝግጅት ማድረግና ማጠንከር
1.1 የመማር-ማስተማርን ስራ ለማጠናከር ጥናታዊና የፅንሰ ሀሳብ ፅሁፎችን ማዘጋጀትና ተግባራዊ ማድረግ
1.2 በጥናታዊ ፅሁፎች ውይይት /ሲፖዚየም / በት/ቤት ደረጃ፣በጉድኝትና በወረዳ ደረጃ ማካሄድ
1.3 በተማሪዎች ውጤትና የሳይንስ ሂሳብ ትምህርት ላይ የተገኙ ተጨባጭ ለውጦች
ተግባር 11 ፡- የሳይንስ መምህራን መድረክ በትምህርት ቤትና በወረዳ ደረጃ ማዘጋጄትና እንዲዘጋጁ
በማድረግ ተማሪዎች በሳይንስ ትምህርት ውጤታማ የሚሆኑበትን አግባብ መሞከር፣
ግብ አስራ አምስት
በየደረጃው ለሚገኙ የትምህርት ተቋማት በአዲሱ ክልላዊ ስታንዳርድ ወሳኝ የሆኑ ግብዓቶችን በማሟላት
ምቹና ማራኪ በማድረግ የትምህርት ጥራትን በማስጠበቅ የተማሪዎችን ውጤት ማሻሻል፡፡
ተግባር 1፡- ሁሉም ተቋማት የመማር-ማስተማር ዘዴዎችንና የተማሪዎችን አያያዝ እንዲሁም የትምህርት
ቤቶች አካባቢ ተማሪዎችን የሚማርኩ፣የሚያበረታቱና ከስጋት ነፃ እንዲሆኑ ማድረግ፣
ተግባር 3 ፡- ተጨማሪ ክፍሎችን በመገንባት የተማሪ ክፍል ጥምርታን 1-4 1፡50 ና 5-8 1 ለ 45 ማድረስ፣
ተግባር 6 ፡- ትምህርት ቤቶች ቤተ-ሙከራ (ከ 5—8)፣አይሲቲ ማዕከል(ከ 9—10)ና 4 ከ 5—8 ት/ቤት ፣የመጠጥ ውሀ፣የሁለቱም
ፆታ መፀዳጃ ቤት፣የትም/ማበልፀጊያ ማዕከላት(በሁሉም)፣የስፖርት ሜዳዎች(በሁሉም) 100% ያላቸው እንዲሆኑ ማድረግ
ተግባር 7፡- ሁሉም ተማሪዎች 100% ደረጃቸውን በጠበቁ የተማሪዎች መቀመጫ ወንበርና ዴስክ መቀመጥና መማር
መቻላቸውን ማረጋገጥ፣
ግብ አስራ ስድስት ደረጃቸውን የጠበቁ የትም/ት ተቋማት ግንባታን ጥያቄ ከየቀበሌዎች በቀረበው
መሠረት ተለይቶ አመች ሁኔታ መፍጠር፡፡
ተግባር 1፡- የተፈቀደ በጀት መኖሩን በማረጋገጥ የተገኘውን መረጃ በማጠናከር የግንባታና የግዥ ዕቅድ በማዘጋጀት በዕቅድ ላይ
ውይይት ማድረግ፣
ተግባር 2፡- ከወረዳ እስከ ት/ቤት ድረስ ከውይይቱ በተገኘው ግብዓት ዕቅዱን በማሻሻልና በማፅደቅ የዕቅድ መከታተያ ቸክሊስት
በማዘጋጀት በየ 15 ቀኑ ክትትል ማድረግ፣
ግብ አስራ ሰባት
ሁሉም የተገነቡት የትም/ት ተቋማት በበቂ መጠንና ጥራታቸውን የጠበቁ በስታንዳርዱ መሠረት የክፍል
ተማሪ ጥምርታ እንዲኖር በማድረግ የደንበኞችን እርካታ መጨመር፡፡
ተግባር 1፡- የትም/ት ተቋማትን ለመገንባት የተዘጋጀውን የህንፃ ዲዛይንና የስራ ዝርዝር በባለሙያዎች ቡድን እንዲታይና
እንዲረጋገጥ ክትትል ማድረግ፣
ተግባር 2፡- የተሰጠውን ማረጋገጫ መሠረት በማድረግ በስራ ሂደቱ የበላይነት በማፅደቅ የግዥ ዘዴውን በመለየት ግዥ
እንዲፈፀም የጨረታውን ሰነድና ማስታወቂያ በማዘጋጀት የጨረታ ማስታወቂያ ማውጣት፣የጨረታ ሰነድ አባዝቶ ለመሸጥ
በሰነዱ ለሚቀርቡ ጥያቄዎች ማብራሪያ ለመስጠት ማመቻቸት፣(ከወረዳው ገ/ፕ/ልማት ትብብር ጽ/ቤት ጋር)
ተግባር 3፡- የጨረታ ሰነድ ማዘጋጀትና ማሸግ፣እንዲሁም በወቅቱ በተያዘለት ፕሮግራም ሳጥኑን በመክፈት የተጫራጨቾችን
ዋጋ በንባብ ማሰማትና የጨረታ ማስከበሪያ በመረከብ የጨረታ መክፈቻ ቃለ-ጉባኤ በማዘጋጀት የቴክኒክ ግምገማ
ማከናወን፣የጨረታውን ውጤት ማሳወቅና ሰነድ በማዘጋጀት እንዲፈፀም የውል ማስከበሪያ በመረከብ ስራን የመፈፀም ብቃት
መፍጠር፣(ከወረዳው ገ/ፕ/ልማት ትብብር ጽ/ቤት ጋር)
ተግባር 5፡- የሚገነቡት ተቋማት ስርጭት ፍትሀዊ እንዲሆኑ የተቋማቱ ግንባታ በወቅቱ ተጠናቆ ለተፈለገው የትም/ት መስጫ
አገልግሎት እንዲውል ማድረግ፣
ግብ አስራ ስምንት
በወረዳችን በሚገኙ ሁሉም ት/ቤቶች ደረጃቸውንና ጥራታቸውን የጠበቁ የት/ት መሳሪያዎችን ማቅረብ
ተግባር 1፡- የት/ት መሳሪያዎችን አቅርቦት አስመልክቶ ረቂቅ ስታንዳርድና የመረጃ መሰብሰቢያ
ተግባር 2፡- በተዘጋጀው ረቂቅ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት በማድረግ የተፈጥሮ ሳይንስ፣
ተግባር 3፡- በማንኛውም መንገድ ማለትም በግዥ ወይም በዕርዳታ የሚገኙ የት/ት
ግብ አስራ ዘጠኝ
በወረዳችን ባሉ የት/ት ተቋማት ወቅቱን የጠበቀ የት/ት መሳሪያዎች ጥገናና ዕድሳት ጥያቄ ወቅታዊ
ምላሽ እንዲያገኝ ማድረግ፡፡
ተግባር 1፡- ጉዳት የደረሰባቸውን ህንፃዎች በየአካባቢው የጉዳት መጠናቸው ምን እንደሆነ
ተግባር 2፡- በየት/ት ተቋማቱ የት/ት መሳሪያዎችን ጥገና ፍላጎት በማሰባሰብ በተቋሙ መጠገን
የሚችልና የማይችለውን በመለየት በትም/ት ልማት ሰራዊት /ልማት ቡድን/ በማስጠገን አገልግሎት ላይ እንዲውል ማስቻል፣
እንዲወገዱ ማድረግ፣
ግብ ሀያ
የክፍል፣የጉድኝነትና የወረዳ እንዲሁም የሀገር አቀፍ ፈተናዎች ትንተና ለተማሪዎች ውጤት ማሻሻያነት
በግብዓትነት የመጠቀም የአሰራር ስርዓት ተጠናክሮ ተግባር ላይ እንዲውል ማድረግ፡፡
ተግባር 1፡- በትምህርት ዘመኑ ከመጀመሪያ ደረጃ 1 ኛ ሳይክልና 1 ኛ ደረጃ 2 ኛ ሳይክል እና ከዚያም ዝቅተኛ
የተማሪዎች ውጤት ማሻሻያ በ 10 ጥሬ ማርክ መነሻ ማሻሻል፣
ተግባር 2፡- ሁሉም ት/ቤቶች በ 2009 ዓ.ም የፈተና ውጤታቸው በመተንተን ችግር ያሉባቸው የትምህርት
አይነቶች ልዩ ዕቅድ አዘጋጅቶ መተግበር መምህራን የሚያስተምሩት የትምህርት አይነት ዓመታዊ
የተማሪዎችን ውጤት ማሻሻል ግብ አቅደው እንዲንቀሳቀሱ ማድረግ፣
ተግባር 3፡- ት/ቤቶች በትምህርት መሻሻያ ዕቅዳቸው መሰረት የ 2009 ዓ.ም የተማሪዎች ውጤት ትንተና በመነሳት ዓመታዊ የተማሪዎች ውጤት የማሻሻያ
ግብ ላይ የጋራ ስምምነት ማድረግ፣በግቡ ስኬትና መንስኤዎች ላይ ወርሀዊ ውይይት ማድረግ፣
3.1 የፈተና ውጤቶችን በመተንተንና ችግር ላለባቸው የት/አይነቶች ልዩ እቅድ አዘጋጅቶ ተግባራዊ ማድረግ
3.2 ት/ቤቱ በጣለው የተማሪዎች ውጤት ማሻሻያ ግብ ለተማሪዎችንም ማወያየትና ተማሪዎችም የራሳቸውን ግብ እንዲጥሉ ማድረግ
3.3 ስለውጤቱ መሻሻል ተከታታይነት ያለው ወርሀዊ ውይይት ማካሄድ
ተግባር 4 ፡- የ 4 ኛ፣የ 8 ኛና 10 ኛ ክፍል ውጤት ትንተና በማድረግ ከተገኘው ውጤት አንፃር ለውጤታማነቱ
የእቅድ መነሻ ሀሳብ እንዲሆን ማስቻል፣
4.1 የ 8 ኛ ክፍልና የ 10 ኛ ክፍል የፈተና ውጤት ትንተና በማካሄድ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ማድረግ
ተግባር 5 ፡- የ 4 ኛ ከፍል የንባብ ብቃት መለኪያ በጉድኝት ደረጃ ማዘጋጀትና ፈተና ማካሄድ፣
ተግባር 1፡- ትምህርቱ ከት/ቤቶች ግቢ ውጭ ለህብረተሰቡ የሚሰጥበትን ስልት ቀይሶ ተግባራዊ ማድረግ፣
ትምህርቱን ወደውጭ ለማውጣት የሚያስችል ስልት በመቀየስና ዕቅድ በማዘጋጀት ተግባራዊ ማድረግ
በት/ቤት ደረጃ ተግባራዊ የሆኑና ተግባራዊ ያልሆኑ እሴቶችን ለይቶ መያዝና ተግባራዊ ያልተደረጉ
እሴቶችን ተግባራዊ ማድረግ
ተግባር 3 ፡- ትምህርቱ በሁሉም የወረዳው ት/ቤቶች (ከ 5—10 ኛ) ክፍል ውስጥ በተሻሻለው አዲስ ስርዓተ ትምህርትና
በሰለጠኑ መምህራን መሰጠቱን ማረጋገጥ፣
ተግባር 4 ፡- ከ 1 ኛ-4 ኛ ክፍል ለሚያስተምሩ መምህራን ተገቢና ተከታታይ ስልጠና መስጠት፣ ትምህርቱን የሚያስተምሩ
መምህራን ከአካባቢ ሳይንስ ት/ት በተለይም ደግሞ የስነ-ምግባር እሴቶችንችን ለይተው ምን ያህል
እንሚያስረዱ በየወሩ በክፍልና በሳይክል ደረጃ እንዲወያዩ ማድረግ፣
ግብ ሀያ ሁለት ትምህርቱን በይበልጥ ለማስረፅ ሌሎች ተጓዳኝ ተግባራትን አጠናክሮ ተማሪዎች ላይ በመስራት
የትምህርት አሰጣጥን በማጠንከርና በበቂ ሁኔታ ተግባራዊ ማድረግ፡፡
ተግባር 2፡- የት/ቤቱን ተማሪዎችና መምህራን በእሴቶች አካባቢያዊ አተገባበር ችግር ዙሪያ የተደራጀ ልዩ ልዩ መድረኮችን ፈጥሮ ውይይት
በማድረግ ግንዘቤ መፍጠር፣
ተግባር 3 ፡- ልዩ ልዩ አደረጃጀቶች በመመሪያዉ መሰረት ከየድርሻው በተጨማሪ የጋራ ፎረም በመፍጠር በዓመቱ በአጠቃላይ በት/ቤታቸው
ልዩ ልዩ ጉዳዮች ላይ አራት ጊዜ መክረው ለችግሮች መፍትሄ ማስቀመጥ፣
ተግባር 4፡- የስነ-ምግባር መኮነኖች ክበብ በየት/ቤቱ በመመሪያው መሰረት ተቋቁሞ ውጤታማ ስራ እንዲሰራ ማድረግ፣
ተግባር 5፡- የተማሪዎች ካውንስል ፓርላማ ም/ቤት የምርጫ ሂደቶችን ተከትሎ እንዲመረጡ በማድረግ ተግባራዊ ልምምድ ማድረግ፣
ግብ ሀያ ሶስት
የተጠናከሩ የክፍል ውስጥ የክበባትና የአደረጃጀት ስርዓቶች ተከታታይነት ባለው መልኩ መዘርጋትና ተግባር
ላይ በማዋል የተማሪዎችን ዲሲሰፕሊን ማሻሻል፡፡
ተግባር 1፡- በየሴክሽኑና ት/ቤት ደረጃ አሳታፊ በሆነ መንገድ የተማሪዎች መተዳደሪያ ደንብ በወቅቱ ወጥቶ ተግባራዊ ማድረግ፣
ተግባር 2፡- የልዩ ልዩ የተማሪዎች አደረጃጀቶችን ባረጋገጠ መልኩ የአለቆች ህብረት፣የጎበዝ ተማሪዎች ህብረት፣የተማሪዎች ካውንስል፣የሴት
ተማሪዎች አማካሪ ኮሚቴ ወ.ዘ.ተ በወቅቱ በአግባቡ ማደራጀት፣
ተግባር 3፡- የት/ቤቱ ተማሪዎች ከሀገሪቱ ራዕይ በመነሳት የወደ ፊት ራዕያቸውን እንዲለዩ መዝግቦ በራዕያቸው ላይ የተደራጀ ውይይት
እንዲያደርጉና የባለሙያ ተጨማሪ ማብራሪያ እንዲያገኙ ማድረግ፣
ተግባር 4፡- ልዩ ልዩ በሆኑ ብሔራዊ ዓለም አቀፍ የበዓል ቀናት / የባንዴራ ቀን፤አድዋ ድል፣የሰማዕታት ቀን፣የፀረ-ሙስና ቀን፣የኤች አይቪ
ቀን፣የሴቶች ቀን፣የግንቦት 20፣ የብሔር ብሔረሰቦች ቀን ከእሴቶች ጋር በማያያዝ የት/ቤቱ ተማሪዎችና መምህራን ከልዩ ልዩ
ከግብዓት ጋር በቅንጅት የፓናል ውይይት በማድረግ ትምህርቱን የበለጠ የማስረፅ ስራ መስራት፣
ተግባር 5፡- የፌድራሉና የክልል ህገ-መንግስትና ሌሎች ወሳኝ የሆኑ ድንጋጊዎችንና ተጨማሪ ልዩ ልዩ ፅሑፎችን በት/ቤቶች እንዲሟሉ
በማድረግ እሴቶችን በሚሞሪ፣በበራሪ ፁሑፎች፣ፓስተሮችና ልዩ ልዩ ህትመቶችን ማሰራጨትና እንዲሰርፅ ማድረግ፣
ግብ ሀያ አራት
በትምህርት ቤቶች ውስጥ የሰንደቅ ዓላማና መዝሙር ስነ-ስርዓት በአግባቡ እንዲከበር በማድረግ የተማሪዎችን የሀገር ፍቅር
ስሜት ማጎልበት፡፡
ተግባር 1፡- የሰንደቅ ዓላማ መዝሙርን ለዜጎችም ሆነ ለሀገር ያለውን ትርጉም በስነ- ስርዓት ላይ ከዜጎች ስለሚጠበቅ ስነ-ስርዓት ለተማሪዎች
የማስተዋወቅ ስራ መስራት፣
ተግባር 2፡- ሁሉም የወረዳው ት/ቤቶች ስታንዳርዱን የጠበቁ ሁለቱን ባንዴራዎች እንዲያውለበለቡ ማድረግ፣
ተግባር 4፡- የሰንደቅ ዓላማ ስርዓቱ በሌሎች የመንግስት መስሪያ ቤቶች በተገቢው መንገድ እንዲፈፀም የስነ-ዜጋና ስነ-ምግባር ክበብና ት/ቤቱ
ከየወረዳቸው፣ቀበሌ አፈ-ጉባኤዎች ጋር በማቀናጀት ተግባራዊ ማድረግ፣
ተግባር 5፡- የሰንደቅ ዓላማ ቀንን በልዩ ልዩ ዝግጅቶች በደማቅ ሁኔታ ማክበር፣
ግብ ሀያ አምስት
ተማሪዎች በትምህርት ቤትና ከትምህርት ቤት ውጭ በንድፈ ሀሰብ የቀሰሟቸውን እሴቶች የተላበሱ መሆኑን የሚያረግጡባቸው
ተግባራዊ ስራዎች በማከናወን ተጨባጭ ውጤታማ ለውጥ ማሳየት፡፡
ተግባር 1፡- እሴቶች ት/ቤት ባሉበት ደረጃና አካባቢያዊ ሁኔታ ከህ/ሰብ ባህል፤ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ጉዳዮች አንፃር ወዘተ በመነሳት
ተማሪዎች ሊሳተፉባቸው የሚችሉ ስራዎችን ተግባራት ለይቶ ማቀድ፤ የአሰራርና ስምሪት አፈፃፀም ስርዓት መዘርጋት፤ ባደረጉት ተግባራዊ
እንቅስቃሴ ግምገማና ውይይት እንዲያደርጉ ማድረግ፣
ተግባር 2፡- ተማሪዎች በተግባር የተሳተፉባቸውን ስራዎች እንደየስሜታቸው በመለየት ተሞክሮ እንዲለዋወጡ፣ ከውጤቱም ምን እንደተገኘ
በጋራ እንዲመከሩ ማድረግ፣ በግልና በቤተሰብ የዕለት ተዕለት ኑሮ መተግበር የሚገባቸውን ለይተው ወደ ተግባር እንዲገቡ
የማነሳሳት ስራ መስራት፣
ተግባር 3፡- የሀገሪቱን ራዕይና እሴቶች ከት/ቤቶች ግቢ ውስጥ በጉልህ ቦታ ተፅፈው የት/ቤቱ ማህበረሰብ ሲወጡና ሲገቡ እያዩ የበለጠ
እንዳይረሷቸው ማድረግ፣
ተግባር 4፡- የስነ-ዜጋና ስነ-ምግባር መምህራን በዘመኑ ውስጥ አራት ጊዜ /በየሩብ ዓመቱ /በመገኘት በ 2009 ዓ.ም ትምህርት ዘመን መጨረሻ
ያደርጉትን ምክክር ውሳኔ መነሻ በማድረግ ልምድ በመለዋወጥ ትምህርቱን ማጠናከር፣
ተግባር 5፡- የመምህራን ህብረትን አጠናክሮ በማቋቋም በትምህርት ይዘቶች፣በክበብ እንቅስቃሴዎች ከት/ቤት ውጭ እሴቶን ከማስረፅ አኳያ
በተማሪዎች ዲሲፒሊን ችግሮች አጠቃላይ በመማር-ማስተማሩ በሚያጋጥሙ ችግሮች ዙሪያ ተከታታይ ምክክር ማድረግ፣
ተግባር 6፡- በየደረጃው ያሉ ተማሪዎች በክፍል ውስጥ በንድፈ ሀሳብ ደረጃ የቀስሟቸውን እሴቶች ከት/ቤት ውጭ በማህበረሰብ ውስጥ ተግባራዊ
በሚደረግባቸው ዘርፈ ብዙ ተግባራት ውስጥ ማሰማራት፣
ተግባር 7፡- በወረዳው የትምህርት ተቋማት ውስጥ እሴቶችን በይበልጥ ለማስረፅ የሚያስችሉ ተጓዳኝ ተግባራትን በተጠናከረ መልኩ ተግባር
ላይ ማዋል፣
ተግባር 8፡- የህፃናት ፓርላማ ስርዓትን በሁሉም የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት ተግባራዊ ማድረግና እሴቶችን በተሻለ መልኩ ማስረፅ፣
ተግባር 9፡- የስነ-ዜጋና ስነ-ምግባር ትምህርት ባለፉት ዓመታት ያመጣውን ለውጥ ዳሰሳ በማካሄድ ለቀጣይ ማሻሻያነት እንደ ግብዓት
መጠቀም፣
የስርዓተ ትምህርቱን ትግበራ ለመደገፍ መካተት የሚገባቸውን ወሳኝ ተጓዳኝ ተግባራት በየትምህርት ቤቱ
ማስፈፀም፡፡
ተግባር 1፡- ከት/ቤት መሻሻል ማዕቀፍ ውስጥ ትኩረት የተሰጣቸው ሁለገብ ጉዳዮች አካባቢ እንክብካቤ፣ስርዓተ ፆታ፣ኤች አይ ቪ
ኤድስ፣ሀይጅንና ሳንቴሽንን ማስተግበሪያ አቅጣጫ ቀይሶ ተግባራዊ ማድረግ፣
ተግባር 2፡- በየደረጃው ያለ የትምህርት ዘርፍም ሆነ ህብረተሰብና የትምህርት ባለድርሻዎች ስርዓተ ትምህርቱ የሚገመገምበት፣ግብረ-መልስ
የሚሰጥበት ቋሚ ስርዓት መዘርጋትና ተግባራዊ ማድርግ፣
ተግባር 3 ፡- ተጨማሪ የንባብና የፅህፈት ክህሎት ማስተማሪያ የተማሪዎች ተግባር ተኮር ፣የቤተ-ሙከራ ማንዋሎች ተባዝተው ለአዲስና
ለሌሎች ት/ቤቶች ማሰራጨት እንዲሁም በየደረጃው ባሉ በሁሉም ጉዳዮች (any matter) አማካኝነት የሱፐር
ቪዢን ድጋፍ ማድረግ፣
ተግባር 4 ፡- በክፍል ውስጥ እስከ ወረዳ ያሉ ልዩ ልዩ የተማሪዎች አደረጃጀትና የአሰራር ስርዓቶችን በተጠናከረ
የተቀናጀና ተከታታይነት ባለው መልኩ አደራጅቶና የአሰራር ስረዓቶችን በማጠናከር ወደ ስራ በማስገባት
የወረዳውን ተማሪዎች ስነ-ምግባር ማሻሻል፣
ግብ ሃያ ሰባት
በሀገር አቀፍ ደረጃ የወጣውን የስርዓተ ትምህርት መነሻ በማድረግ ክልላዊ ስትራቴዎች
ተዘጋጅተው በዝግጅትና ትግበራ ሂደት በስኬታማነት መፈፀም፡፡
ተግባር 1፡- በአዲሱ የመሰረታዊ የክልሉ የስራ ሂደት ለውጥ ጥናት መሰረት ለመማሪያና ማስተማሪያ መፅሀፍት
ስርጭት በዝርዝር በማቀድ ተግባራዊ ማድረግ፣ለት/ቤቶች መፅሀፍት ስርጭት ብዛት በአይነትና በክፍል
ደረጃ ለይቶ ማቀድ፣
ተግባር 2 ፡- በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚዘጋጁትን የተለያዩ የክፍል ደረጃዎች ትም/ት መምሪያ ማስተማሪያ ማሳወቅ፣
ተግባር 3፡- በሀገር አቀፍ ደረጃ ተዘጋጅተውና ታትመው የሚሰራጩትን የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት የመማሪያ
ማስተማሪያ መፅሀፍትን ለሁሉም የመንግስት ት/ቤት ተማሪዎች በነፃ መታደላቸውን ማረጋገጥ፣
ተግባር 4፡- ተግባር-ተኮር የጎልማሶች መሰረታዊ ትምህርት ስርዓት ትምህርት ማተሪያሎች / መርሀ ትምህርት
የአመቻቾች ማንዋልና የተሳታፊዎችን የተግባር መልመጃዎች መፅሐፍ ማሰራጨት፣
ግብ ሃያ ስምንት
ተግባር 1፡- መምህራን በት/ቤት ደረጃ በሰለጠኑበት የሙያ ማሻሻያ ስልጠና መሰረት በተለያዩ ችግሮች ላይ ተግባራዊ
ጥናትና ምርምር እንዲያካሂዱ ማድረግ ውጤቱን በትምህርት ቤት ጉባኤ ቀርቦ የፓናል ውይይት
ማካሄድ፣ምርጦችን እስከ ክልል ማቅረብና መፍትሔዎችን ለችግር መፍቻነት መጠቀም፣
ተግባር 2፡- አዲስ የተሸሻለውን ስርዓተ ትምህርት ትግበራ አሳታፊ በሆነ ሂደት መገምገምና የማሻሻያ ግብዓቶችን
ማሰባሰብ፣
ተግባር 3፡- ከተቋማት እስከ ወረዳ ባሉ የትምህርት ባለሙያዎች በሴቶች ትምህርት ተሳትፎ ዙሪያ የጉድኝት
ማዕከላት በትምህርት ስራ ያለውን አስተዋፅኦ በስርዓተ ትምህርት ትግበራ ዙሪያ በትምህርት ውስጣዊ
ብቃት ዙሪያ በሳይንስና ሂሳብ አሰጣጥ ዙሪያና በተከታታይ ምዘናና ተማሪ ተኮር የማስተማር ስነ-ዘዴ
ዙሪያ ጥናትና ምርምር እንዲያደርጉ ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠር፣
ተግባር 1፡- የመጀመሪ ደረጃ ትምህርት ማጠናከሪያ ትምህርት፣የመጀመሪያ ትምህርት ማጠናከሪያ ፈተና፣የተማሪዎች
ምዝገባ፣የፈተና ህትመት ስርጭት፣የፈተና አስተዳደርና ውጤትን ማሳወቅ፣
1.1. በ 2009 ዓ.ም በትም/ቤቶች የተፈታኞች ብዛትን መለየትና ከወዲሁ ቅድመ ዝግጅት ማድረግና
በጀት መያዙን ማረጋገጥ
ተግባር 2፡- የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ትምህርት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ፈተና የተማሪዎች
ምዘገባ የፈተና ህትመት፣ስርጭት የፈተና አስተዳደርና ውጤትን ማሳወቅ
1.1. በ 2009 የትም/ቤቶች የተፈታኞች ብዛት መለየትና ከወዲሁ ቅድመ ዝግጅት ማድረግ
ተግባር 3፡- በተከታታይ ምዘና ላይ ባጋጠሙ ችግሮች ላይ ክትትል በማድረግና አፈፃፀሙን በማየት ቀጣይ የመፍትሔ
አቅጣጫ ማስቀመጥ፣
2.1. ክትትል ማድረግና አፈፃፀሙን በማየትና የመፍትሔ አቅጣጫ አስቀምጠው ተግባራዊ ማድረግ፣
ተግባር 4፡- የቀለም ትምህርትና የስፖርት ውድድር የሚካሄድበትን አግባብ ማስቀመጥና መተግበር፣
ተግባር 5፡- በክልል አቀፍ ፈተናዎች አስተዳደር ላይ የተከሰቱ ችግሮች ተለይተው በ 2009 ዓ.ም እንዳይከሰት
ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ውይይት ማካሄድ፣
ተግባር 6፡- የትምህርት ማስረጃ ማረጋገጫ ለሚጠይቁ ተገልጋዮች ተገቢውን አገልግሎት መስጠት፣
ተግባር 1፡- በወረዳው ውስጥ የሚገኙ 1 ኛ ደረጃ ሙሉ ሳይክልና በ 2 ኛ ደረጃ ት/ቤቶች ዋና ዋና ግብዓቶች
እንዲሟሉና እንዲደራጁ በማድረግ የመማር-ማስተማርና ስልጠና ሂደቱን በተጠናከረ መልኩ መደገፍ፣
ግብ ሰላሳ አንድ
አዲስ በተሸሻለው መደበኛና መደበኛ ያልሆውን ትምህርት በመደገፍ የትምህርት ጥራትን
ማስጠበቅ፡፡
ተግባር 1፡- የሬዲዮ ስርጭት ለማይደርስባቸው ት/ቤቶች ሚሞሪ አስጭነዉ ት/ቤቶች እንዲጠቀሙ ማድረግ፣
ተግባር 2፡- የት/ቤት ሚኒ-ሚዲያ ክበባትን ለማጠናከር ለ 110 መምህራንና ተማሪዎች በሚኒ-ሚዲያ አጠቃቀም ላይ
ስልጠና መስጠት፣
ተግባር 3፡- የሬዲዮ ፕሮግራም የጊዜ ሰሌዳ ተዘጋጅቶ ለመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤቶች በወቅቱ እንዲደርስ ማድረግ፣
ግብ አንድ
በወረዳው ሁሉም እድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህፃናት በሙሉ ትምህርት ቤት ገብተው
እንዲማሩ ማስቻል፡፡
ተግባር አንድ
በወረዳው እድሜያቸው ሰባት ዓመት የሞላቸው ሁሉም ህፃናት ትምህርት ቤት የሚገቡበት ቅድመ ሁኔታዎችን
ማመቻቸት፣
ወ 2600 ሴ 2636 ድ 5236 ተማሪዎች እድሜያቸው ሰባት ዓመት የሞላቸውን መቀበልና የአንደኛ ክፍል ጥቅል
ቅበላን ወ 3389 ሴ 3435 ድ 7324 ማድረስ
የአንደኛ ደረጃ ጥቅል የትምህርት ሽፋንን ወ 17975 ሴ 15685 ድ 32763 ማድረስ
በሁለቱ 2 ኛ ደረጃ ት/ቤቶች የሚማሩ ተማሪዎችን የትምህርት ሽፋንን 750 ማድረስ
5 አዲስ ግንባታና በ 35 ት/ቤቶች ተጨማሪ መማሪያ ክፍሎችን መገንባት፣በ 102 ት/ቤቶች መማሪያ ክፍሎች ጥገና፣3
ፈፅሞ የተጎዱትን ት/ቤቶች አፍርሶ የመገንባት ስራ ማካሄድ
በወረዳ ደረጃ 3 የልዩ ፍላጎት ዩኒት ማዕከል መገንባት
በዚሁ የት/ት ዘመን በሁሉም የክፍል ደረጃዎችና የትምህርት አይነቶች የመማሪያ መፃህፍትን ለሁሉም ተማሪዎች
በነፍስ ወከፍ ማዳረስ
በወረዳው ለተማሪዎች በቀመር የሚመደበውን የ 2009 ዓ.ም መደበኛ በጀት ክትትል በማድረግ ተገቢ የማሻሻያ ሀሳብ
በማቅረብ ግብረ-መልስ ለሚመለከታቸው አካላት መስጠት
ከህብረተሰቡ፣ከረድዔት ሰጭ ድርጅቶችና ከአካባቢው ተወላጆች ወዘተ ሀብትን በማሰባሰብ ወደ አንድ ቋት
ማስገባትና ይህን ከተለያዩ ምንጮች የተገኘን ሀብት ፍትሃዊ በሆነ መልኩ ድልድል መፈፀም
ተግባር ሶስት
በወረዳው የአካቶ ት/ት ባሉት ት/ቤቶች በሚማሩ ተማሪዎች ጥናት በማካሄድ ፕሮጀክት በማዘጋጀት የሃብት
ማፈላለግ ማመንጨት ተግባር መፈፀም፣
ግብ ሁለት
መሠረታዊ የጎልማሶች ትምህርት በወረዳው ባሉ ቀበሌዎች ፕሮግራሙን
ማጠናከር፡፡
ተግባር አንድ
መሠረታዊ የጎልማሶች ትምህርት ፕሮግራም በሁሉም የወረዳው ቀበሌዎች በመጀመር የጎልማሳውን አቅም
ማጠንከር፣
ወ 7293 ሴ 5737 ድ 13030 አዲስና ወ 4844 ሴ 3829 ድ 8673 ነባር ጎልማሶችን መመዝገብ
በ 130 ጣቢያዎችና በ 115 አመቻቾች ትምህርቱን መስጠት(በሁሉም ቀበሌዎች)፡፡ይህን የሚያስተባብሩ 3
ባለሙያዎችም ተቀጥረዋል፡፡
ተግባር ሁለት
ወረዳዊ የተቀናጀ ተግባር-ተኮር የጎልማሶች ትምህርት ስትራቴጂ ተዘጋጅቶ ፕሮግራሙን በሁሉም ቀበሌዎች
ተጠናክሮ መስጠት መጀመር፣
ተግባር ሶስት
ወረዳዊ የህዝብ ንቅናቄ ሰነድ በማዘጋጀትና ከወረዳ እስከ ቀበሌ በማስተዋወቅ ግንዛቤ
መፍጠር፣
ተግባር አራት
ማንበብ፣መፃፍና ማስላት የማይችሉ ወጣቶችና ጎልማሶችን መረጃ በየደረጃው አጠናቅሮ
መያዝና ለሚመለከተው ክፍል ማሳወቅ፣
ግብ ሶስት
የትምህርት ፍትሀዊነትን ማስጠበቅ፡፡
ተግባር አንድ፡-
o ስርዓተ-ፆታን በትምህርት ስራ ውስጥ ማካተት
በየደረጃው በሚገኙ የትምህርት ፕሮግራሞች የስነ-ፆታዊ ክፍተትን/Gender Disparity/ የሚያጠቡ ተግባራትን መፈፀም፡፡
ለዚህም ለ 2009 ዓ.ም የሴቶችን የት/ት ተሳትፎ ለማጎልበት 15685 ለማድረስ ዕቅድ ተይዟል፡፡
ህ/ሰቡ ስለሴት ልጅ ያለውን አስተሳሰብ ስለ ሴቶች ትምህርት አስፈላጊነትና ችግሮች የግንዛቤ ማጎልበቻ በተለያዩ
መድረኮች መፍጠር
በት/ቤት ዙሪያ የሚገኙ አደረጃጀቶችን በመጠቀም ያለ እድሜ ጋብቻንና ጠለፋን ለማስቀረት ጥረት ማድረግ
በትምህርታቸው ጥሩ ውጤት ላመጡ ሴት ተማሪዎች ማበረታቻ ማለትም የገንዘብና የማቴሪያል ድጋፍ
የሚያገኙበትን ሁኔታ መፍጠር
በየት/ቤቶች የሴት ተማሪዎች የተጨማሪ ትምህርት ድጋፍ ማድረግ
ተግባር ሁለት
በከተሞችና በገጠር መካከል ያለውን የትምህርት አቅርቦት ልዩነት/urban-Rural inequity/ ለማጥበብ በገጠርና
በኋላቀር አካባቢዎች የትምህርት ተቋማት በተጠናና በተጠናከረ ሁኔታ ማስፋፋት፣
ተግባር ሶስት
ዝቅተኛ የተማሪ ተሳትፎ ባላቸው ቀበሌዎች ልዩ ትኩረት በመስጠት የትምህርት ተሳትፎን የሚያጎለብቱ የተለያዩ
ተግባራትን መፈፀም፣
የሳተላይት ትምህርት ቤቶችን በማስፋፋት መክፈትና የት/ት ዕድል ያላገኙትን ዕንዲያገኙ ማድረግ
እንደ አከባቢው ተጨባጭ ሁኔታ ማህበረሰብ አቀፍ አፀደ-ህፃናት ተቋም ማቋቋም
ግብ አራት
የትምህርት ብቃትን ማሻሻል፡፡
ተግባር አንድ
በ 2009 ዓ.ም በጀት ዓመት በመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤቶች የመማሪያ ሴክሽን ተማሪ ጥምርታ በስታንዳርዱ መሠረት
ማድረግ፣
ተግባር ሁለት
በየደረጃው የሚገኙ የትምህርት ተቋማት የተማሪዎችን መድገምና ማቋረጥ ምጣኔን የሚያሻሽሉ ተግባራትን
በውጤታማነት መፈፀም፣
የመድገም ምጣኔን 3% በታች ማድረስ
የማቋረጥ ምጣኔን ከ 2% በታች ማድረስ
የየእርከኑን ማጠናቀቂያ ምጣኔ ማሻሻል
ግብ አምስት
በወረዳችን በሚገኙ በሁሉም ት/ቤቶች ደረጃቸውንና ጥራታቸውን የጠበቁ
የትም/መሳሪያዎች ማቅረብ፡፡
ተግባር አንድ
የትም/መሳሪያዎች አቅርቦትን አስመልክቶ ረቂቅ ስታንዳርድና የመረጃ መሠብሠቢያ ፎርማት በማዘጋጀት መረጃውን
በመሰብሰብ፣በማጠናከርና የመነሻ ሀሳብ በማዘጋጀት በሀሳቡ ላይ በስራ ሂደቱ ውይይት በማድረግ ማፅደቅና ስታንዳርድ
ማዘጋጀት፣
ተግባር ሁለት
በተዘጋጀው ረቂቅ ከባለ ድርሻ አካላት ጋር ውይይት በማድረግ የተፈጥሮ ሳይንስ፣የሂሳብ፣የህብረተሰብ ሳይንስ፣የሰ.ማ.ጎ
የትም/መሳሪያዎችን በየዓይነቱ በየትም/ት ሳብጀክቱ የስራ ዝርዝር አዘጋጅቶ ወደ ስራ መግባት፣
ተግባር ሶስት
በማንኛውም መንገድ ማለትም በግዥ ወይም በዕርዳታ የሚገኙ የትም/መሳሪያዎችን በፍትሀዊነት በወቅቱ በየተቋማቱ
እንዲደርስ ማድረግ፣
ዓላማ፡- የሲቪል ሰርቪስ ማሻሻያ ፕሮግራምን በመተግበር ውጤታማ አሰራሮችን መፍጠር ነው፡፡
የሚከናወኑ ተግባራት
- የውጭ አስተዳደርን በተመለከተ ት/ቤቶች የፋይናንስ አሰራራቸውን በባንክ አካውንት እንዲጠቀሙ ማድረግ
- ውል የወሰዱና ያልወሰዱ መምህራን እና ሰራተኞችን መረጃ በተገቢው ሁኔታ በመያዝ እንዲያሟሉ ማድረግ
- የቅሬታ ማስተናገጃ ስርዓትን ማሻሻልና ቅሬታን በፅሁፍ ተቀብሎ ምላሽ በደብዳቤ መስጠት
ግብ ሁለት
የዕቅድ ክንውን የስራ ግምገማ ማካሄድናለቀጣይ እቅድም መሰረት መጣል፡፡
ዓላማ ፡-በየዕለቱ የዕቅድ አፈፃፀምን በመገምገም ችግሮችን ፈጥኖ ለማስተካከል እንዲቻል ነው፡፡
የሚከናወኑ ተግባራት
- የተማሪ ቁጥር መረጃ ት/ቤቶች በየሳምንቱ ለወረዳ ይልካሉ፤ወረዳ ለዞን በማጠናከር ያስተላልፋል
ክፍል 4
( )
ዕቅዱን ለመፈፀም ያሉ መልካም አጋጣሚዎች፣ሊያጋጥሙ የሚችሉ ችግሮች ስጋቶች ፣መፍትሄዎችና የምንከተላቸው አቅጣጫዎች፣
የትምህርት ቤቶች አከፋፈት በወቅቱ የቀበሌው አመራርና ወላጆች በተገኙበት በደመቀ ስነ-ስርዓት
እንዲፈፀም ማድረግ
በስነ-ስርዓቱ ላይ የትምህርት ቤቱን ዕቅድና ከወላጆች የሚጠበቀውን ተሳትፎ በማስተዋወቅና ሌሎችንም ወሳኝ ተግባራት
በማከናወን መፈፀም፣
ህብረተሰቡ የጊዜ ሰሌዳውን ጠብቆ በየ ወሩ በመወያየት በተማሪዎች ውጤትና ዲሲፕሊን መሻሻል እንዲያመጣና
ተቋሙንም በፋይናንስ የማገዝ ስራ እንዲሰራ መግባባት፣
በአዲሱ የመርሱ መመልመያ መመሪያ መሰረት ለሁለቱ 2 ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ም/ርዕሳነ መምህራንን በመመደብ
ማሰማራትእንዲሁም 5 የ 1 ኛ ደረጃ ሱፐርቫይዘሮችን፣1 የ 1 ኛ ደረጃ ም/ር/መ/ር እና 11 የ 1 ኛ ደረጃ ር/መ/ራን
መመደብ፣
የስራ ሂደት ፀሀፊዎችንና ፈፃሚዎችን/ባለሙያዎችን ማሟላት፣
መልካም አስተዳደርን በየደረጃው ለማስፈን ጥረት ማድረግ
ትርጉም ያለው ከተቆጣጣሪነት መረጃ ከመልቀምና ከማቀባበል ያለፈ የሱፐርቪዥን ድጋፍ መስጠት፣
ስራዎችን በቼክሊስት ቆጥሮ ለየስራ ሂደቱና በየደረጃው ላሉ ተቋማት ማስረከብ፣
ወቅታዊ፣ታማኝና ተከታታይነት ያለው የሪፖርትና ግብረ-መልስን ስርዓት አጠናክሮ ተግባራዊ ማድረግ፡፡ከሁሉም በላይ
ደግሞ ከሪፖርት ጥንቅር በኋላ ለበታችኛው አካል የሚሰጠው ግብረ-መልስ በራሱ አስተማሪ የስልጠናና ማስተካከያ
መሳሪያ መሆኑን በመረዳት በአግባቡ መተግበር፡፡
ክፍል 5
5. የዕቅዱ አተገባበር፣የግንኙነትና የሪፖርት አደራረግ ስርዓት
5.1 በትምህርት ቤት ደረጃ ፡-
በትምህርት ቤቶች ያሉት ልዩ ልዩ አደረጃጀቶች በየሳምንቱ የፓኬጁን አፈፃፀም ይገመግማሉ፣ለጉድኝት ማዕከላት ሪፖርት
ያደርጋሉ፣በየሳምንቱ የተማሪ ቁጥር በፆታ፣ በእድሜና በክፍል ደረጃ ለይተው እንዲሁም የተማሪዎችን ውጤት ለማሻሻል
ከጣሉት ግብ አኳያ አፈፃፀሙ እንዲሁም የመምህራን ተከታታይ ስልጠና፣የስነ-ዜጋ ትምህርት እንቅስቃሴ በስርዓተ-
ትምህርቱ ተግባራት ዙሪያ ያከናወናቸውን ተግባራት ገምግመው ለጉድኝት ማዕከል ያስተላልፋሉ፣
ሞዴል መምህርና ክፍል መርጠው ሌሎች መምህራንና ክፍሎች ወደዚህ ስታንዳርድ እንዲደርሱ ያደርጋሉ፣
ሁሉም የወረዳው ት/ቤቶች የሚያስፈልጉ መረጃዎችን ለየስራ ሂደቶች ይልካሉ፣
5.2 በጉድኝት ደረጃ ፡-
ሱፐርቫይዘሮች በተመደቡበት ጉድኝት ማዕከላት የሚገኙ ት/ቤቶችን ር/መምህራን በማዕከሉ በማሰባሰብ ዘወትር በየአስራ
አምስት ቀኑ ስራ እንዲገመግሙ ማድረግ፣
የጉድኝት አባል መምህራን በወር አንድ ጊዜ እየተገናኙ በሚያስተምሩት የት/ዓይነት በተናጠልና በጋራ ተሞክሮና ልምድ
ይለዋወጣሉ፣
የጉድኝት ሱፐርቫይዘሮች ር/መምህራንን ከመደገፍ ባለፈ የጉድኝታቸውን መምህራን ተገቢ የሆነ ሙያዊ ድጋፍና ክትትል
ይደረጋል፣
የጉድኝቱ የተማሪ መረጃ ሪፖርትና ሌሎች ዋና ዋና አፈፃፀሞች በተቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ለወረዳ እንዲደርስ
ይደረጋል፣
የጉድኝቱ ት/ቤቶች መምህራን የ 1 ኛ ክፍል ተማሪዎችን ለማብቃት ፎረም በማቋቋምና ልምድ በመለዋወጥ ደረጃ
እየሰጡ ለወረዳ ሪፖርት ያደርጋሉ፣
ሁሉም በጉድኝቱ ያሉ መምህራን የጎልማሶችን ትምህርት በትኩረት ይዘው ለውጥ በሚያመጣ መልኩ ይንቀሳቀሳሉ፣
በት/ቤቶች ያለውን አፈፃፀም ገምግመው በውጤታቸው መሰረት በየወሩ ደረጃ ያወጣሉ፣ግብረ-መልስ ይሰጣሉ፣
ሞዴል ርዕሰ-መምህር፣ት/ቤትና ክፍል ተመርጠው ሌሎቹ ወደዚያ ስታንዳርድ እንዲደርሱ ጥረት ይደረጋል፣
5.3 በወረዳ ደረጃ:-
የወረዳ ማኔጅመንት ኮሚቴ በየሳምንቱ እየተገናኘ የዕቅድ አፈፃፀሙን ይገመግማል፣በወር አንድ ጊዜ ወደ ቀበሌ እየሄደ
ይገመግማል፣ይደግፋል የአንድን ት/ቤት የተሻለ ተሞክሮ ወደ ሌላ ያስተላልፋል እንዲሁም ርዕሳነ-መምህራንና
መምህራንን በማንቀሳቀስ የልምድ ልውውጥ እንዲካሄድ ያደርጋል፣
በየወሩ ለጉድኝት ማዕከላትና ለት/ቤቶች በጥራት ማስጠበቂያ ፓኬጅ አፈፃፀም ደረጃ እያወጣ መረጃ ይይዛል፣ግብረ-
መልስ ይሰጣል፣
የተቀናጁት ተግባር-ተኮር ጎልማሶችን ትምህርት ትኩረት ሰጥቶ መስራትና ይህንንም በተግባር ያረጋገጠ ግምገማ በዕቅድ
በተመራ አግባብ ማካሄድ፣
በአራቱም ሩብ ዓመታት በወረዳ ደረጃ የሱፐርቫይዘርና ር/መ/ራን ግምገማና ክትትል ይካሄዳል፣