Professional Documents
Culture Documents
Prevention Study
Prevention Study
2
ማውጫ
ርዕስ ገጽ
ምስጋና ----------------------------------------------------------------------------------------------- 3
መግቢያ ----------------------------------------------------------------------------------------------- 4
በድሬደዋ ከተማ አስተዳደር የቦታ ግንባታ ፈቃድ አሰጣጥና ይዞታ አስተዳደር፣ የመሬት
ልማት ... ---------------------------------------------------------------------------------------------- 5
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ካርጎ ተረሚናል ዕቃዎች አያያዝና ቁጥጥር የአሰራር ሥርዓት
ችግሮችና መፍትሄዎቻቸው ----------------------------------------------------------------------- 36
የጥቁር አንበሳ ሆስፒታል የውጭ ሀገር ሕክምና የቦርድ ፈቃድ አሰጣጥ ----------------------- 54
የሸቀጦች ጅምላ ንግድና አስመጪ ድርጅት የሲሚንቶ ሽያጭ አፈፃፀም ሥርዓት ---------- 62
የሥራና ከተማ ልማት ሚኒስቴር የግንባታ ሥራዎች ፈቃድና እድሳት አሰጣጥ የአሰራር
ሥርዓት ---------------------------------------------------------------------------------------------- 64
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የውጭ ማስታወቂያ ፈቃድ አሰጣጥ ቁጥጥርና ክትትል
የአሰራር ሥርዓት-------------------------------------------------------------------------------------- 68
3
መግቢያ
የሙስናን ወንጅል በሀገራችን ለመከላከልና ሀገራችን የተያያዘችውን የልማት፣ የዲሞክ
ራሲና የመልካም አስተዳደር ግንባታው ትርጉም ያለው ተጽእኖ ሊያደርግ በማይችልበ
ት ደረጃ ለማድረስ እንዲቻል የፌደራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን በአዋጅ
ተቋቁሞ የሥነምግባርና የፀረ-ሙስና ትምህርቶችን ማስፋፋት፣ የሙስናን ወንጀልና
ብልሹ አሠራርን መከላከል እንዲሁም የሙስናን ወንጀል መመርመርና በሙስና ወንጀል
ተሳትፈው የተገኙትንም የመክሰስ ተግባራትን በስፋት በማከናወን ላይ ይገኛል።
4
በድሬደዋ ከተማ አስተዳደር የቦታ ግንባታ ፈቃድ አሰጣጥና ይዞታ
አስተዳደር፣ የመሬት ልማት ...
የዚህ ጽሁፍ ዋና መነሻ ኮሚሽኑ በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር የቦታ ግንባታ ፈቃድ
አሰጣጥና ይዞታ አስተዳደር የሥራ ሂደት እና የመሬት ልማት፣ የነዋሪዎች ዳግም
ማስፈርና የከተማ ፕላን ዝግጅት የሥራ ሂደት ላይ በቀረቡ ቅሬታዎች መነሻነት
በኮሚሽኑ የተካሄደ ጥናት ላይ የሚያተኩር ይሆናል፡፡
ይህን ችግር ለመፍታት በከተማ አስተዳደሩ ያለውን የመሬት ሃብት በአግባቡ በመያዝ
በአካባቢው ካሉ የክልል መስተዳድሮች እና ገበሬዎች ጋር በመደራደር /Land -Sharing
System/ በመጠቀም የመሬት ባንክ /Land-stock/ እንዲጨምር ማድረግ ወሳኝ መሆ
ኑ ተጠቁሟል፡፡ መረጃዎችን ለማሰባሰብ የመሬት ቆጠራ ማካሄድን በከተማዋ ያለውን
የመሬት ሁኔታን ዘመናዊ ለማድረግ በቂ መረጃ ማሰባሰብ ያለውን የመሬት ሀብት
በቁጠባ ለመጠቀም የሚያስችል መሆኑ በጥናት ቡድኑ በመፍትሔነት ተጠቁሟል፡፡
5
በመስጠት በአግባቡ ሊከታተለውና ወቅታዊ ምላሽ ሊሰጠው የሚገባ ነው:: የመሬት
ልማትና አስተዳደርን ለመምራት የወጡ አዋጆች፣ ደንቦችና መመሪያዎች በአግባቡ
አለመፈጸም በጥናቱ በሁለተኛ ደረጃ የተቀመጠ ነበር፡፡ የድሬዳዋ አስተዳደር በቻርተር
አዋጅ ቁጥር 416/97 ከተቋቋመበት ጀምሮ የመሬት ልማትና አስተዳደርን በተመለከተ
ለማስፈፀሚያ በርካታ አዋጆችን፣ ደንቦችንና መመሪያዎችን አውጥቷል፡፡ ነገር ግን
የመሬት ልማትና አስተዳደር ባለሥልጣን በሚሰጣቸው አገልግሎቶች ዙሪያ የወጡትን
አዋጆች፣ ደንቦችና መመሪያዎች መሠረት በማድረግ ሥራውን በአግባቡ አለመከናወኑ
ን ጥናቱ ያመለክታል፡፡ ባለሥልጣኑ የመሬት ልማትና አስተዳደርን በተመለከተ የወጡ
አዋጆች፣ ደንቦችና መመሪያዎችን የመሠረታዊ የአሰራር ሥርአት ሂደት ለውጥ መሠረት
አድርጎ ከአዲሱ አደረጃጀትና አሰራር ጋር በሚጣጣም መልኩ የሚሻሻሉ የህግ ማዕቀፎችን
በማሻሻል ተግባራዊ በማድረግ አፈጻጸማቸው በየጊዜው እየተገመገመና ኦዲት እየተደረገ
ለሚከሰቱ ችግሮች ወቅታዊ እርምጃ በመውሰድ ግልጽነትንና ተጠያቂነትን ማስፈን እንዲ
ሁም በወጡና በሚወጡ ሕጎችና መመሪያዎች ዙሪያ ግንዛቤ የማስጨበጥና የማዳበር ሥራ
ቀጣይነት ባለው መልኩ ማከናወን ችግሩን ሊፈቱ የሚችሉ መሆኑን ጥናቱ ያመለክታል፡፡
6
የሚሰጡ ቦታዎችን ለመሸጥ የግልፅ ጨረታ ዘዴን አለመጠቀም ነው፡፡ የከተማ ቦታ በሊዝ
እንዲያዝ የሚፈቀደው በጨረታ መሆኑንና ለጨረታ የሚቀርቡ ቦታዎችን የተመለከተ
ዝርዝር ጉዳዮችን የአፈጻጸም መመሪያው ይገልፃል፡፡ ነገር ግን በከተማዋ በሊዝ የሚሰ
ጡ ቦታዎች የመንግሥትንና የህዝብን ተጠቃሚነት የማያረጋግጡና በአብዛኛው የግልፅ
ጨረታ ዘዴን መሰረት ያደረጉ አይደሉም፡፡
በዚህ አሰራር የጨረታ ሂደቱ ተጨማሪ ጊዜና ወጪ የሚጠይቅ ቢሆንም የሊዝ አፈጻ
ጸም ከመሬት ዝግጅት እስከ ሽያጭና ርክክብ ድረስ ያለው የስራ ሂደት በእቅድና በፕሮ
ግራም እንዲከናወን ለክትትልና ቁጥጥር የተመቻቸ ይሆናል፡፡ በተጨማሪ የሊዝ ቦታ
ሽያጭ አፈጻጸምን ህግና መመሪያ መከተሉ ግልጽነትንና ተጠያቂነትን የተላበሰ
አሰራር ሥርአት እንዲዘረጋ እና አልሚው ቦታውን ለወሰደው ዓላማ በአግባቡ እንዲጠ
ቀምበት ስለሚያደርግ ሊፈጸሙ የሚችሉ የሙስና ወንጀሎችን ለመከላከል ያስችላል፡፡
በሊዝ መሬት ለሚጠይቁ አልሚዎች ቅድመ ሁኔታ ሳያሟሉ መስጠት ጥናቱ ያመለከ
ተው ስድስተኛው ችግር ነው፡፡ ከመሬት ልማትና አስተዳደር ባለሥልጣን በሊዝ መሬት
የሚወስዱ ባለሀብቶች በተጫራቾች መመሪያ መሰረት እንደ ሽያጭ ውሉ ሊለያይ ቢችል
ም ቢያንስ የሚከተሉትን ቅድመ ሁኔታዎችን ማሟላት ይጠበቅባቸዋል፡፡
7
መስጠት ሁኔታዎች ተከስተዋል፡፡
8
ተከትለው መሥራት፣ አለአግባብ የተወሰዱ እርምጃዎች እንዲስተካከሉ ማድረግ፣
የሚሰጡ ውሳኔዎችን በየጊዜው መገምገምና ሪፖርት እንዲቀርብ መጣር፣
ኃላፊነትንና ተጠያቂነትን ማመላከት እንዲሁም አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ በተፈጸመ ህገ
ወጥ ተግባር ላይ አስተማሪ የሆነ አስተዳደራዊ እርምጃ መውሰድ አስፈላጊ ነው፡፡
9
ጥናቱ ያመለከተው ስምንተኛው የአሰራር ችግር ለኢንቨስትመንት በሚሰጡ መሬቶች
ላይ ያለው ክትትል፣ ቁጥጥርና ድጋፍ ደካማ መሆን ነው፡፡ በአስተዳደሩ ኢንቨስትመ
ንት ላይ በተለያዩ ዘርፎች በማምረቻ ኢንዱስትሪ፣ በአገልግሎት እና በከተማ ግብርና
የኢንቨስትመንት መስክ ለመሰማራት መሬት የወሰዱ የግል ባለሀብቶችን በተመለከተ
ሊደረግ የሚገባው አግባብ ያለው ክትትል፣ ቁጥጥርና ድጋፍ ስለማይከናወን በኢንቨስትመንት
ስም መሬት ለመውሰድና ለማልማት በተደጋጋሚ የተወሰኑ ባለሀብቶች መሬት ወስደው
በመሸጥ የሚበለጽጉበት አሠራር ይታያል፡፡ ይህ አሰራር ልማታዊ ባለሀብቶችን ማዕከል
ያደረገና የከተማዋን ኢንቨስትመንት የሚያሳድግ ሳይሆን የጥቅም ግንኙነትን መሰረት
ላደረገ አሰራር በመጋበዝ ሙስናና ብልሹ አሰራር እንዲስፋፋ በር ይከፍታል፡፡
ጥናቱ በዘጠነኛ ደረጃ ያመለከተው ችግር የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ካርታ አሰጣጥ
ተጠያቂነትንና ግልፅነትን የተከተለ አለመሆን ነው፡፡ የመሬት ልማትና አስተዳደር
ባለሥልጣን ከሚሰጣቸው ዋና ዋና ተግባራት አንዱ የቦታና ይዞታ ማረጋገጫ ካርታ
አሰጣጥ ነው፡፡ ይህን ሥራ በተገቢው ሁኔታ ለመወጣት ተጠያቂነትና ግልጽነትን የተከተለ
ባለመሆኑ በማህበር ተደራጅተው መሬት ለመውሰድ ጥያቄ ላቀረቡ ተገልጋዮች
በአንድ ሰው ስም ካርታ በመስጠት ህገ ወጥ ተግባር መፈፀም፣ በአንድ ቦታ ላይ ለሁለት
ሰዎች ካርታ መስጠት፣ መሀንዲሶች ሲለኩ ባዶ ቦታ መተውና በህገወጥ መንገድ
እንዲያዝ በሚያመች ሁኔታ ካርታ መስራት፣ በካርታ ላይ ካርታ በመስራት፣ ተገልጋ
ዮችን ለአላስፈላጊ ችግር መዳረግና ፍትህን ማዛባት፣ የመንግስትን ቤት ተከራይተው
ለሚኖሩ ግለሰቦች ማስፋፊያ አግባብ በሌለው መንገድ መስጠት፣ የቀበሌ ቤት በግል ይዞታ
ማዞር ለዚህም የግል ማህደር ማጥፋትና በግለሰብ እንዲቀየር ማድረግ፣ ክፍትና ለመናፈሻ
የሚሆኑ ቦታዎችን ለግለሰቦች በመስጠት የይዞታ ማረጋገጫ እንዲኖራቸው ማድረግ፣
ለአንድ ግለሰብ ከአራት ቦታ በላይ ለመኖሪያ ቦታ መስጠት፣ በውጭ ድርጅቶች
ለቆሻሻ ማስወገጃ የተሠራውን ቦታ በጥቅማጥቅም ለግለሰብ መስጠትና በአካባቢው ነዋሪ
ላይ የጤናና ማህበራዊ ችግሮችን ከሚያስከትሉ ነገሮች መካከል የሚጠቀሱ ናቸው፡፡
ስለሆነም ትክክለኛ የሆነ የቦታና ይዞታ ማረጋገጫ ካርታ አሰጣጥ ሊያሰፍን በሚችል
መልኩ ደንብና መመሪያን መሠረት አድርጎ የሚከናወን ባለመሆኑ ከዚህ ጋር
ተያይዘው ለሚከሰቱ ሙስናና ብልሹ አሰራር የተጋለጠ ነው፡፡በመሆኑም ይህን ክፍ
ተት ለመሙላት ተገልጋዩን ፍትሃዊና በአግባቡ ለማስተናገድ እንዲቻል ደንብና
10
መመሪያን መሠረት ያደረገ የቦታ ይዞታና ካርታ ማረጋገጫ አሰጣጥ እንዲተገበር ማድረግ፣
ቀደም ሲል አላአግባብ የተሰጡ የይዞታ ማረጋገጫ ካርታዎችን በማጣራት አግባብ
ያለው እርምጃ መውሰድ፣ ተፈጻሚነቱን በየጊዜው በመከታተልና በመገምገም ለሚፈ
ጠሩ ችግሮች ወቅታዊ እርምጃ መውሰድና በአገልግሎቱ ዙሪያ የህብረተሰቡን ግንዛቤ
ማሳደግ ተገቢ መሆኑን ጥናቱ አመላክቷል:: በከተማው ያሉትን ህገወጥና ሠነድ
አልባ ይዞታዎች ምዝገባና ይዞታ ማስረጃ የመስጠት ሥራና አዘገጃጀት ትክክለኛ
መረጃዎችን መሠረት ያደረገ አለመሆን በጥናቱ የተመለከተው አስረኛ ችግር ነው፡፡
በከተማው በተለያዩ ጊዜያት ህገ-ወጥ እና ሠነድ አልባ ይዞታዎች በሬጉላራይዜሽን ፕላን
መሠረት በቀበሌ ደረጃ በአጥኚ ድርጅት በተዘጋጀው አማካኝነት አስተዳደሩ የሚያጸድ
ቀው ህገወጥ አሰፋፈሩን ሥርዓት የሚያስይዝበት ፕላን አለው:: ይሁን እንጂ አተገ
ባበሩ ትክክለኛና እውነተኛ መረጃን መሠረት ያደረገ ባለመሆኑ ሰነድ አልባና ህገወጥ
ቤቶች ተሰርተው የቆዩ በማስመሰል ካርታ በገንዘብ እንዲዘጋጅላቸው ማድረግ፣
የሠነድ አልባ ቤቶችን በተመለከተ የመንደር ኮሚቴ ስልጣናቸውን አለአግባብ መጠቀም፣
ለሀሰተኛ ሰነድ የተጋለጠ መሆን፣ የሀሰተኛ ሠነድ ባለጉዳዩ እንዲያዘጋጅ የተመቻቸ
ሁኔታ መኖር፣ በቀበሌ በአግባቡ የማረጋገጥ ሥራ አለማከናወን፣ ፍ/ቤት የባለቤትነ
ት ማረጋገጫ ሲጠይቅ አንዳንድ ቀበሌና የመሬት አስተዳደር ባለሥልጣናት ሀሰተኛ
መረጃ በመስጠትና ውሳኔዎችን በማዛባት ካርታ እንዲያገኙ ማድረግ፣ የተጭበረበረ
ሠነድ ማዘጋጀትና ህግን የማስከበር አቅም ደካማ መሆን በአሠራሩ ውስጥ ይታያል፡፡
ይህም በከተማዋ የልማት እንቅስቃሴ ላይ ከሚያሳድረው አሉታዊ ተጽእኖ ባሻገር
ግልጽነት የጎደለውና በህገ ወጥ ጥቅም ላይ የተመሰረተ ግንኙነት እንዲሰፍን ያደርጋል፡፡
በጥናቱ በአስራ አንደኛ ደረጃ የተመለከተው ችግር አግባብ ያለው የቅሬታ አቀራረብና
አፈታት ሥርአት አለመዘርጋት ነወ። በመሬት አስተዳደር ላይ ተገልጋዩ ቅሬታውን
የሚያቀርብበትና የሚፈታበት ሥርአት በአግባቡ ስላልተዘረጋለት ለእንግልት እና
ለአላስፈላጊ ወጪ መዳረግና ማግኘት የሚገባውን አገልግሎት ህገወጥ በሆነ መንገድ
11
የማግኘት አሰራርን ይፈጥራል፡፡
12
2. አሠራሩን ለመምራት የወጡ ህጎችን ጠንቅቆ በመረዳት ለተፈፃሚነታቸው
ተገቢውን ትኩረት መስጠት፣
13
በኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን በቀረጥ
ነፃ መደብሮች ላይ የሚደረግ የቁጥጥር አሠራር ሥርዓት
14
የሚቻለው መንግሥት ቀረጥ ሳይከፈልባቸው ወደ ቀረጥ ነፃ መደብሮች ውስጥ
የሚገቡ ዕቃዎች ለታለመላቸው ዓላማ ሙሉ ለሙሉ ይውላሉ ለማለት የሚያስችል
የቁጥጥር ሥርዓት በሚፈለገው ደረጃ አለመኖሩን ነው፡፡ ይህ ክፍተትም አንዳንድ መደብሮች
ቀረጥ ያልተከፈለባቸውን ዕቃዎች በማውጣት ከታለመለት ዓላማ ውጭ ሊሸጡ
የሚችሉበት ሁኔታ ይታያል፡፡ ይህ ደግሞ ፍትሃዊ ያልሆነ የገበያ ውድድር እንዲፈጠርና
መንግሥት ማግኘት የሚገባውን ገቢ እንዲያጣ ምክንያት ይሆናል፡፡
15
የገቢና ሽያጭ ሰነድ አለመሆኑን ከጥናቱ ለማወቅ ተችሏል፡፡ በተለይ
በኤርፖርት ቀረጥ ነፃ መደብር ወደ መደብር የገባውን፣ የተሸጠውንና ሚዛኑን መመዝ
ገቢያ መዝገብ ላይ ለረዥም ጊዜ ምዝገባ አለመከናወኑንና በጉምሩክ ሠራተኛው በኩል
የቁጥጥር ሥራው ተገቢው ትኩረት አለመሰጠቱን ታውቋል፡፡ መረጃዎቹ በወቅቱ
ላለመመዝገባቸው በሠራተኛው በኩል የተሰጠው ምክንያት “የመደብሮቹ የሽያጭ ሠራተ
ኞች በኮምፒዩተር ስለማይሠራ መረጃ ማግኘት አልተቻለም” የሚል ነው፡፡ ቀደም ሲል
እንደተገለፀው ጉምሩክ ያስቀመጣቸው የተወሰኑ ሠራተኞች ምዝገባ የሚያከናውኑት
በሚሰጣቸው የገቢና የሽያጭ ደረሰኝ ሳይሆን የቀረጥ ነፃ መደብሮችን የሽያጭ መዝገብን
መሠረት በማድረግ መሆኑን ነው፡፡ ይህ አሠራር ለባለሥልጣኑ ትክክለኛውን መረጃ ለማግኘት
የማያስችለው ሲሆን የቁጥጥር ሥርዓቱን የሚያዳክምና ለሙስናና ብልሹ አሠራር
የሚያጋልጥ መሆኑ በጥናቱ ተመልክቷል፡፡
በሌላ በኩል ከመጋዘን ወደ መሸጫ መደብር የሚገቡ ዕቃዎች መረከቢያ ሰነዶች ስርዝ
ድልዝ የሚበዛባቸው መሆኑ ከጥናቱ መረዳት ይቻላል፡፡ ከመጋዘን ወደ መሸጫ መደብ
ር የሚገቡ ዕቃዎች ለቁጥጥር ያመች ዘንድ የመረከቢያ ደረሰኝ ይዘጋጅላቸዋል፡፡ እነዚህ
ደረሰኞች በትክክሉ መሠራት ሲገባቸው ስርዝ ድልዝ ባለው ሁኔታ ተሠርተው እደሚ
ገኙ ለማረጋገጥ ተችሏል፡፡ ለአብነትም በጥናቱ በናሙና በተወሰደ የቀረጥ ነፃ መደብር
ያለው የመረከቢያ ሰነድ በተገለፀው የዕቃ ብዛትና ዓይነት ላይ ስርዝ ድልዝ ከመደረጉ
ም በላይ ደረሰኙ ላይ የተመዘገበው የዕቃ መጠን ሰርዞ በሌላ የመተካት ሁኔታ እንዳለ
ታውቋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም አንዳንድ የቀረጥ ነፃ መደብር ሠራተኞች ሽያጭ አከናውነው
ለባለመብቱ የሚደርሰውን የሽያጭ ደረሰኝ ቅጠል ከሰጡ በኋላ ባለመብቱ ተጨማሪ
ዕቃዎችንም እንደወሰደ በማስመሰል በቀሪ ደረሰኞቹ ላይ ተጨማሪ ዕቃዎችን እንደሚ
ወስዱ ለመገንዘብ ተችሏል፡፡ ይህም ሀገሪቱ ያላትን ውስን የውጭ ምንዛሬ እንዲባክን
የሚያደርግ እና የቀረጥ ነፃ ባለመብት ተጠቃሚ ላልሆኑ ሰዎች በሕገወጥ መንገድ
እንዲደርሳቸው ዕድል የሚሰጥ ነው፡፡ ይህ አሠራር የነፃ መደብር ሠራተኞች በዋነኛነትም
መንግሥት የጣለባቸውን ኃላፊነት ወደ ጎን በመተው ዕቃዎችን ቀረጥ ሳይከፈልባቸው
በተለያዩ መንገዶች ከመደብር እንዲወጡ ለማድረግና የማጭበርበር ድርጊቶች እንዲፈ
ፀሙ በር እንደሚከፍት የጥናት ቡድኑ ማረጋገጥ ችሏል፡፡ በዚህ የተነሳም የቀረጥ ነፃ
መብት ላላቸው ግለሰቦች ተብሎ ቀረጥ ሳይከፈልባቸው የሚገቡ ዕቃዎችን በአንዳንድ
ሥነምግባር የጎደላቸው የጉምሩክ ሠራተኞችና የቀረጥ ነፃ መብት መደብሮች
በመመሳጠር እቃዎቹ በከተማ ውስጥ እንዲሸጡ በማድረግ ያለአግባብ ተጠቃሚ እንዲሆኑ
ሊያደርግ እንደሚችል ተመልክቷል፡፡
16
በቀረጥ ነፃ መደብሮች እና በመጋዘን ውስጥ ያሉ ዕቃዎችን በተመለከተ በባለሀብቶች
በኩል ዓመታዊ የንብረት ቆጠራ የሚደረግ ቢሆንም በባለስልጣን መ/ቤቱ በኩል
ከመደብሮች ጋር በጋራ ዓመታዊ የንብረት ቆጠራው የማይከናወን ስለሆን በመጋዘኖች እና
በመደብሮች ውስጥ ያሉ ንብረቶች ከወጪ ቀሪ ሚዛንና በቆጠራ መካከል የሂሳብ ማስታ
ረቅ ሥራ አለመሰራቱን ለማረጋገጥ ተችሏል፡፡ በዚህ የተነሳ በዓመቱ መጨረሻ ቀረጥ
ሳይከፈልባቸው የገቡ ንብረቶች መጉደል አለመጉደላቸው የሚታወቅበት አሰራር
የለም፡፡ ይህ አሰራር አንዳንድ ግለሰቦች ለመንግሥት ቀረጥ ያልተከፈለባቸው
ን ዕቃዎች ከቀረጥ ነፃ መደብር ውጪ በመሸጥ መንግሥት የውጪ ምንዛሪ
እና የከሽያጭ ትርፍ ግብር እንዳያገኝ ከማድረጉም ባሻገር ዕቃዎች የመጡበትን ዓላማ
በመሳት የቀረጥ ነፃ መብቱ በሌላቸው ግለሰቦች እጅ እንዲገቡ በማድረግ ፍትሐዊ የሆነ
የገበያ ውድድር ሥርዓት እንዳይኖር እድሉን ይከፍታል፡፡
17
ግልፅነትን ማስፈን ይችላል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ በመመሪያው መሠረት ሃላፊነታቸውን
በማይወጡ አካላት ላይ ተገቢውን ክትትል በማድረግ አስፈላጊው የእርምት ርምጃ የሚወ
ሰድበትን ሥርዓት ዘርግቶ አሁን እየታየ ያለውን ወጥነት የጎደለውን አሰራር ወደ አንድ
አቅጣጫ የማምጣት ሥራ ማከናወን እንደሚያስፈልግ በጥናቱ የቀረበ የመፍትሄ ሀሳብ
ነው፡፡
የትርፍ ሰዓት ክፍያ አከፋፈል ሥርዓት የጥቅም ግጭት የሚፈጥር መሆኑ ሌላው በባ
ለሥልጣን መሥሪያ ቤቱ የታየ የአሰራር ሥርዓት ችግር ነው፡፡ የኢትዮጵያ ገቢዎችና
ጉምሩክ ባለስልጣን ቁጥጥር የሚያደርግባቸው የተወሰኑ የቀረጥ ነፃ መደብሮች ከአስ
ራ ስምንት ሰዓት በላይ የሚሰሩ ሲሆን ሠራተኞችም ከመደበኛው ሥራ ሰዓት ውጪ
ለሚሰሩባቸው ሰዓታት የትርፍ ሰዓት ክፍያ ይፈፀምላቸዋል፡፡ እያንዳንዱ የቀረጥ ነፃ
ሽያጭ መደብር በመቆጣጠር ሥራ ላይ የተሰማራ የጉምሩክ ሠራተኛ የትርፍ ሰዓት
ክፍያ የሚከፈለው በሚቆጣጠሩት መደብሮች ሲሆን ክፍያ መጠኑና የአከፋፈሉ
አይነት በመደብሮች በጎ ፈቃድ ላይ የተመሰረተ መሆኑን ለመረዳት ተችሏል፡፡ ሠራተኞቹ
የቁጥጥር ሥራውን የሚያከናውኑት ባለስልጣን መ/ቤቱን ወክለው ቢሆንም ትርፍ
ሰዓት ክፍያው የሚፈፀምላቸው ግን በቀረጥ ነፃ መደብሮች መሆኑ የጥቅም ግጭት
የሚፈጥር እና ተቆጣጣሪ ሠራተኞቹ የሚያገኙትትን ጥቅም ላለማጣት ሲሉ የተሰጣቸ
ውን ኃላፊነት በአግባቡ እንዳይወጡ እንዲሁም መንግሥት ማግኘት የሚገባውን ጥቅም
እናዳያገኝ የሚያደርግ አሰራር ሆኖ ይታያል፡፡
18
ባለስልጣን መ/ቤቱ የቀረጥ ነፃ መደብር ሠራተኞችን ተጨማሪ የሰው ሀይል ቀጥሮ
በፈረቃ ከማሰራት ይልቅ በትርፍ ሰዓት ክፍያ ማሰራት የተሻለ አማራጭ እንደሆነ
ያምናል። ስለሆነም ለሠራተኞች ወጥ የሆነ የትርፍ ሰዓት ክፍያ ሥርዓት በመዘርጋት
ክፍያውን ባለሥልጣን መሥሪያ ቤቱ እንዲፈጽም ማድረግ በመፍትሄ ሀሳብነት የቀረበ
ሲሆን ይህም ሠራተኞቹ የቁጥጥር ሥራቸውን ያለምንም ተፅዕኖ እንዲሰሩ ያስችላቸዋል፡፡
19
የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን የግዥ አፈፃፀም ሥርዓት
20
ቤት የሚዘጋጁት አንዳንድ የጠቀሜታ ዝርዝሮች /ስፔስፊኬሽንስ/ የሚገዙትን
ዕቃዎች ወይም አገልግሎቶች በግልጽ የሚያሳዩ ባለመሆናቸው የግዥ ውሳኔዎች ወደ
አልተፈለጉ አቅጣጫዎች እንዲያጋድሉ በማድረግ የአሠራር ክፍተቶች ሊፈጥሩ እንደሚችሉ
ጥናቱ ያሳያል፡፡
የሥራ ክፍሎች በበጀት ዓመቱ ውስጥ ለማከናወን ከያዙት የሥራ መጠንና መርሃ
ግብር ጋር የሚጣጣም የግዥ አቅርቦት ፍላጎትን መሠረት በማድረግ የበጀት ዓመቱን
ዕቅድ በተቀናጀ መልኩ እንዲፈጽሙ እንዲሁም ስለንብረት አጠቃቀማቸው ወቅታዊ
ሪፖርት አዘጋጅተው እንዲያቀርቡ ተገቢውን ክትትል ማድረግ በመፍትሄ ሃሳብነት
በጥናቱ ተጠቁሟል፡፡ ይህም በዕቅድና በመርሃ ግብር በመመራት በገበያ ላይ በጥራትና
በመጠን ሊገኙ የሚችሉ ጥቅሞችን ያስገኛል፤ እቃዎች ለረዥም ጊዜ ያለ አገልግሎት
ተከማችተው ለብልሽት እንዳይዳርጉም ጠቀሜታው ላቅ ያለ ነው፡፡
21
ከመዳረጉም በተጨማሪም የውስጥ ቁጥጥሩን በማዳከም ለሙስናና ለብልሹ አሠራር
ይዳርጋል፡፡ ለአብነትም የደንብ ልብስና የሌሎች አስፈላጊ ቁሳቁሶች ግዥን መጥቀስ
ይቻላል፡፡
በፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን የታየው ሌላው የአሠራር ሥርዓት ችግር በግዥ አፈፃፀም
መመሪያው ለእያንዳንዱ የግዥ ከተቀመጠው የገንዘብ ጣሪያ መጠን በላይ ግዥን
መፈፀም ነው፡፡ የጥቅል ግዥ የሚያስገኘውን ጥቅም ከግምት በማስገባት ግዥ ፈፃሚ
አካላት በዚህ መልክ እንዲያከናውኑ እና ቀደም ሲል በዕቅድ ያልተያዘ ነገር ግን አጣዳፊ
የሆነ ግዥ ሲመጣ ቢያንስ ሶስት አቅራቢዎችን በማወዳደር ግዥ በዋጋ ማቅረቢያ
ማከናወን እንደሚቻል የመንግሥት ግዥ መመሪያ ይደነግጋል፡፡ ሆኖም በፌደራል
ፖሊስ በመመሪያው የተቀመጠው ገንዘብ ጣሪያ መጠን ሳይጠበቅ እና የአቅራቢዎች
ዝርዝር በሌለበት ሁኔታ ግዥ አንደሚከናወን ጥናቱ አረጋግጧል፡፡ ለአብነትም በቁጥር
1 /ፌፖኮ1/28/121/ ግንቦት 10 ቀን 1999 ዓ.ም በፕሮፎርማ ቁጥር 48780 አምስት
ጠረጴዛዎች በ43,368.80 ለዋናው መሥሪያ ቤት ግዥ የተከናወነ ሲሆን ታሕሣሥ 7
ቀን 2000 ዓ.ም ሶስት ኮምፒዩተሮች ከነፕሪነተራቸው በ47,472.00 ለሆስፒታልና
ለፋይናንስ መምሪያ በፕሮፎርማ ግዥ መፈፀሙን መመልከት ይቻላል፡፡ ይህ ዓይነት
አሠራር የመንግሥት ገንዘብ አለአግባብ እንዲወጣ ከማድረጉም ሌላ ለሙስናና ብልሹ
አሠራር በር የሚከፍት ይሆናል፡፡
22
ይህ ደግሞ በተገልጋዮች ዘንድ ቅሬታን የሚያስከትልና የግዥ ሂደቱን የሚያራዝም
ሆኖ ተገኝቷል፡፡ በአጠቃላይ ሙስናና ብልሹ አሠራርን ከመከላከል አንፃር ከፍተኛ
ጥንቃቄን የሚሹ ግዥዎች በሶስት የጨረታ ኮሚቴ አባላት ብቻ ውሳኔ እንዲተላለፍባቸ
ው ማድረግ ተገቢ ሆኖ አይታይም፡፡
23
የሚከሰቱትን ክፍተቶች በማውጣት ለማኔጅመንቱ አጋዥ ሪፖርት በማቅረብ የእርምት
ርምጃ እንዲወሰድ የሚያስችልበት ሁኔታ ጉልህ ሆኖ አልታየም፡፡
ስለሆነም በቀጣይ የኮሚሽኑ የውስጥ ኦዲት በጨረታ ኮሚቴ ውስጥ በታዛቢነት የሚሳ
ተፍበትና በየወቅቱ የሥራ ሪፖርት ለማኔጅመንቱ የሚያቀርብበት አሰራር መዘርጋት
እንዳለበት ጥናቱ ጠቁሟል፡፡
24
የፌዴራል ፍርድ ቤቶች የፍርድ አፈፃፀም መምሪያ የአሰራር ሥርዓት
25
ወቅት በየጊዜው በከፍተኛ ደረጃ እየጨመረ ካለው የቤት ሽያጭ ዋጋ ጋር
እንዲጣጣሙ /Selling price Adjustment/ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመመካከ
ር አሰራሩ የሚስተካከልበትን ሁኔታ ማመቻቸት የአሰራር ሥርዓት ችግሩን ለመፍታት
የቀረበ የመፍትሄ ሃሳብ ነው፡፡
ይህን የአሰራር ሥርዓት ችግር ለመቅረፍ ግልጽ የሐራጅ ሽያጭና ድርሻ ክፍፍል
አፈጻጸም መመሪያ ከዝርዝር ሕጉ ጋር በማገናዘብ ተቀርፆ ተግባራዊ ማድረግ በጥናቱ
የቀረበ የመፍትሄ ሃሳብ ሲሆን ይህም ክፍተቶችን ለመከላከል እና ወጥ የሆነ አሰራር
እንዲኖር ለማድረግ ያግዛል፡፡
26
ቅንጅታዊ አሰራር ጠንካራ አለመሆን ነው፡፡ የፍርድ አፈፃፀሙ በወቅቱ ተግባራዊ እንዲሆ
ን ከሚመለከታቸው አካላት /የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መሬት አስተዳደር፣ የአዲስ
አበባ ወይም የፌዴራል የፖሊስ፣ የቀበሌና ሌሎች ተባባሪ አካላት/ ጋር ጠንካራ ቅንጅታዊ
አሰራር ባለመፈጠሩ በሚከሰቱ ምልልሶች መብዛት ባለጉዳዮች ሊጉላሉ ስለሚችሉ ጉዳዩን
በአፋጣኝ ለማስፈፀም ሲባል ለሙስናና ብልሹ አሰራር ክፍተት ሊፈጥር ይችላል፡፡
የዘርፉ የፍርድ ማስፈፀም አቅም ውስንና ያልተጠናከረ መሆን ሌላው ለብልሹ አሰራርና
ሙስና የሚዳርግ ሁኔታ ነው፡፡
አሁን ያለው የሰው ኃይል ሥራው ከሚጠይቀው አንፃር በብዛትና በጥራት፣ በሙያና
ልምድ አናሳ ከመሆኑ አንፃር የማስፈፀም አቅሙና የቁጥጥር ስልቱ ዝቅተኛ ሆኖ
መገኘቱ በፍርድ አፈፃፀሙ ስራ ላይ ተፅእኖ ያሳድራል በምሳሌነትም ሥራው በሸያጭ
ሙያ በቂ ዕውቀትና ልምድ ባላቸው ባለሙያዎች የሚከናወን ያለመሆኑ፣ የፍርድ
አፈፃፀም ሠራተኛና በተለይ ስለ አንዳንድ ንብረቶች በቂ እውቀት ስለሌላቸው በሚያ
ስከብሩበት ወቅት ጉድለታቸውን ያለመመዝገብ /ይህ ሁኔታ በቸልተኝነትም ሊፈፀም
ይችላል፣ በሐራጅ ጊዜ ደግሞ ዕቃው ተቀይሮ ወይም ሆነ ተብሎ እንዲበላሽ ተደርጐ
ሊቀርብ ይችላል/፣ ሲረከቡ ስለነበረበት ሁኔታና አካላት በቂ መረጃ ማግኘትም አስቸጋሪ
መሆኑ ተጠቃሽ ነው፡፡
የሰው ሃይሉን ፈትሾ ቁልፍ በሆኑ የስራ መደቦች ብቃት ያለው የሰው ኃይል በቋሚነ
ት በዕድገት፣ በዝውውር ወይም በቅጥር መመደብና በሐራጅ ሽያጭ አሰራር ላይ ለባለ
ሙያዎች ስልጠና መስጠት ለችግሩ በመፍትሄ ሃሳብነት በጥናቱ ቀርቧል። የተመረጠው
መፍትሄ ተግባራዊ ሲሆን ብቃትና የተሟላ ሥነምግባር ያላቸውን ሠራተኞችን
ለማግኘት ሊያስቸግር እና አዲስ ሠራተኞችን ለመቅጠር በቂ በጀት ላይፈቅድ ስለሚች
ል የተሟላ ብቃትና ሥነምግባር ያላቸውን ሠራተኞችን ለመሳብ የሚያስችሉ የሥራ
ሁኔታዎችን ከገበያ ጋር በተጣጣመ መልኩ ማመቻቸትና አዲስ ሠራተኞችን
ለመቅጠር በቂ በጀት እንዲፈቀድ ጥረት መደረግ እንዳለበት በጥናቱ ተጠቁሟል፡፡
27
ጥረት ለሕገወጥ ድርጊቶች ያበረታታል፡፡
ይህን የአሰራር ሥርዓት ችግር ለመፍታት በጥናቱ የቀረበው የመፍትሄ ሃሳብ በፍት
ሐብሄር ሥነሥርዓት ሕግ ቁጥር 423 የሐራጅ ሽያጭ መደረጉን ለሕዝብ ስለማሳወቅ
በሚል በተደነገገው መሠረት በሐራጅ ሽያጭ ማስታወቂያው ሊገለፁ የሚገባቸውን
ዝርዝር መረጃዎችን በመግለፅ ተጫራቾች በቂ መረጃ እንዲያገኙ በማድረግ፣ በጥቅም
ላይ የሚውለው የሐራጅ ሽያጭ ማስታወቂያ ዘዴ እንደ ንብረቱ የግምት መጠን
መወሰን ቢቻል፣ በፌዴራል ፍ/ቤቱ የአሰራር ማንዋል ላይ በተገለፀው መሠረት ከብር
5000 በታች ከሆነ በተለያዩ ቦታዎች ማስታወቂያውን በመለጠፍ፣ ከብር 5,000-50,000
ከሆነ ሰፊ ሽፋን ባለው ጋዜጣ እንዲወጣ ማድረግ፣ ከብር 50,000 በላይ ከሆነ ከጋዜጣው
በተጨማሪ በቴሌቪዥን እንዲገለጽ በማድረግ በሚል የቀረበው ተግባራዊ ቢደረግ
የተሟላና ግልጽ መረጃዎችን በማግኘት በቂ ተጫራቾች በመጀመሪያ ጨረታ ላይ
እንዲቀርቡና እንዲሳተፉ ይጋብዛል። የፍርድ ባለዕዳንም ሆነ የፍርድ ባለመብቱን ንብረቱ
በተገቢው ዋጋ እንዲሸጥ በመርዳት ተጠቃሚ ያደርጋል፡፡
ፍርድ ላረፈባቸው ንብረቶች የርክክብ ቅፆች የተሟሉና ግልጽ መረጃዎችን /detail lists
and conditions/ ለመያዝ በሚያስችል መልኩ የተቀረጹ አለመሆን፣ የንብረቶች የገቢ
ና የወጪ ርክክብ፣ አያያዝና አጠባበቅ ሁኔታ ለቁጥጥር የሚያመችና በግልጽ ተጠያቂ
ነትን ለማስከተል የማያስችል መሆኑ በንብረት አስተዳደር ምዝገባ ዙሪያ በቂ ልምድና
ሙያ ያካበተ ባለሙያ አለመመደብ፣ በርክክብም ሆነ በሽያጭ ተገቢ ቁጥጥር ለማድረ
ግ /check and balance/ ማመዛዘኛ በመስራት የሚረጋገጥበት አሠራር አለመኖሩ፣
ንብረቶች ሳይሸጡ ለረጅም ጊዜ መቆየትና እነዚህን ንብረቶች ለማስወገድ የሚቻልበት
ግልፅ መመሪያ አለመኖር፣ የመጋዘን ኪራይና ዋጋ አተማመን /storage and
handling cost valuation/ ከወቅቱ የገበያ ዋጋ ጋር ተመጣጣኝና በጥናት ላይ የተመሠ
ረተ አለመሆን በንብረት አስተዳደሩ ከታዩት ችግሮች ዋና ዋናዎቹ ሲሆኑ ይህም ንብረት
እንዲባክን፣ ለስርቆትና ለብልሽት እንዲዳረግ ክፍተት ሊፈጥር እንደሚችል ጥናቱ
ያመላክታል፡፡
28
እንደንብረቱ ውድነት የሚከፈልበትን አሰራር በጥናት ተመርኩዞ ማዘጋጀት፣
የርክክብም ሆነ የሽያጭ አፈጻጸሙ ተገቢው ትኩረት እንዲሰጠው ቢደረግና በርክክብ
ወቅት ኦዲተር በገለልተኛነት የሚታዘብበት፣ ስለዕቃው ዝርዝር ሁኔታ የሚያውቅ
ባለሙያ በግንባር እንዲገኝ የሚደረግበትን ሁኔታ ማመቻቸት፣ በውሳኔ ትዕዛዝ
ላይ ለአፈፃፀም አስፈላጊ የሆኑ መረጃዎች በዝርዝር የንብረቶቹን ዓይነት፣ ግምትና
ሞዴል ካላቸው፣ ብዛት እና የሚገኙበት አካል በግልጽ ተጠቅሶ ቢቻል በጠባቂ እንዲሆኑ
ማድረግ በጥናቱ የተገለፁ ችሮችን ለመቅረፍ የቀረቡ የመፍትሄ ሃሳቦች ናቸው፡፡
ሒሳብ አያያዝን በተመለከተ የሂሳብ መዝገብ አያያዝና ቁጥጥር ማነስ አሰራሩም መሰረታ
ዊና ተቀባይነት ያለው የፋይናንስ አሰራር ሥርዓትን /GAAP - Generally Accepted
Accounting Principles and Policies/ ተከትሎ የማይሰራና ቁጥጥሩ የላላ መሆኑ
ለሙስናና ብልሹ አሰራር የሚያጋልጥ ሁኔታ ነው፡፡
29
ማድረግ፣ የሂሳብ ሥራውን በባለሙያ ማሰራት፣ ግልጽነትና ተጠያቂነትን ለማስፈን
ለሠራተኞች የሥራ መዘርዝር እንዲሰጣቸውና የሠራተኞችን አቅም ለመገንባት በቂ
ስልጠና እንዲያገኙ ማድረግ ናቸው፡፡ ለዚህም ሲባል ደረጃውን የጠበቀ የሂሳብና ቁጥጥ
ር ሥራ ለማከናወን በሙያው የሰለጠነ ሠራተኛ ለማግኘት ከፍተኛ ደመወዝ ሊጠየቅ
ስለሚችል በመ/ቤቱ ልምድ ያላቸውን ሠራተኞች በሙያው በቂ ስልጠና እንዲያገኙ
ማድረግ እና ከገበያው ሁኔታ ጋር በተገናዘበ መልኩ በቂ በጀት በመያዝ የሰው ኃይሉን
በቅጥር ማሟላት ሊወሰድ የሚገባው እርምጃ ነው፡፡
30
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የብር ኖት
ሕትመትና ሳንቲም ቀረፃ አገልግሎት ግዥ አሰራር
31
የወጣው የግዥ አፈፃፀም መመሪያ የማይከተል በመሆኑ አሰራሩ ወጥነትና ተጠያቂነት
እንዳይኖረው ያደርገዋል፡፡
ሌላው በባንኩ የታየው ለሙስና እና ብልሹ አሰራር ክፍተት የሚፈጥር ሁኔታ ባንኩ
የብር ኖቶች ህትመትና ሳንቲም ቀረፃ አገልግሎት ግዥ ከፈፀመ በኋላ ጥራቱን
የጠበቀ የብር ኖት እና ሳንቲም ቀረፃ ስለመከናወኑ ናሙናውን በማየት ማረጋገጥ የሚችል
ብቃት ያለው ባለሙያ የሌለው መሆኑ ነው፡፡
ባንኩ አሁን እያደረገ ካለው የጥበቃ ስራ በተጨማሪ በካሜራ (በCCTV) ቢታገዝ የባንኩን
32
የቁጥጥር ሥርዓት የተጠናከረ እንደሚያደርገው በጥናቱ እንደ መፍትሄ ተቀምጧል፡፡
ያገለገሉ የገንዘብ ኖቶች መረጣ እና አወጋገድ የአሰራር ሥርዓት ሂደት በጥናቱ
ለሙስና እና ብልሹ አሰራር ክፍተት የሚፈጥር ሁኔታ ታይቷል፡፡ ይህም በገንዘብ አወጋገድ
የሥራ ሂደት የሚሳተፉ አካላት በሥራቸው ሊኖራቸው የሚገባን ሚና በግልጽ
በማንዋል የተደገፈ አለማድረግ አንዱ ነው፡፡
33
በማዘጋጀት በክምችት ያሉ የብር ኖቶች አቀማመጣቸው በጊዜ /በወር እና በቀን
እንዲሁም በሳምንት/ በመለየት መጀመሪያ የገባውን መጀመሪያ ወጭ የሚደረግበትን
አሰራር በመዘጋት ነው፡፡
ለዚህ የአሰራር ሥርዓት ችግር ባንኩ ወርቅ ተረካቢው ባለሙያ የወርቁን ትክክለኛነት
ለማረጋገጥ የሚችልበትን ብቃት እንዲያገኝ ስልጠና የሚሰጥበትን ሁኔታ ቢያመቻች
ወይም በዚህ ሥራ ሙያዊ ብቃት ያላቸውን ባለሙያዎች በመቅጠር እና ቴክኖሎጂ
ባፈራው መሳሪያ በመታገዝ የወርቁን ትክክለኛነት እያጣራ የሚረከብበትን ሥርዓት
በተናጠል ለማስፈን ያስችላል፡፡ ባንኩ በቋሚነት የወርቅ ጥራት ማረጋገጥ የሚችል
ባለሙያ ሊኖረው እንደሚገባ አስፈላጊነቱ የማያጠያይቅ መሆኑ በጥናቱ ተጠቅሷል፡፡
34
የወርቅ ግብዓት ሥርዓትን በተመለከተ በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ መንገድ የሚመለከታ
ቸው አካላት ማለትም የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር፣ የማዕድን እና ኢነርጂ ሚኒስቴር፣
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ፣ የገቢዎች ሚኒስቴር፣ የጉምሩክ ባለስልጣን እና የተለያዩ ወርቅ
አምራች ድርጅቶች ወይም ማህበራት በተጠናከረ መልኩ የመረጃ ልውውጥ ሥርዓት
ባለመዘርጋቱ በተጭበረበረ ሃሰተኛ የወርቅ ንግድ ፈቃድ በመጠቀም እንዲሁም ከጂኦሎ
ጂካል ሰርቬይ መ/ቤት የልኬት ሰርተፊኬት ከተሰራ በኋላ ወርቁን ባንክ በማቅረብ ረገድ
ያለውን ክፍተት በመጠቀም ማጭበርበር እንዲፈፀም ክፍተት ፈጥሯል፡፡
35
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ካርጎ ተርሚናል ዕቃዎች
አያያዝና ቁጥጥር የአሰራር ሥርዓት ችግሮችና መፍትሄዎቻቸው
36
ሠራተኛ የሌለና ከመጋዘን ውጪ ቆይቶ በመጋዘን ቦታ ሲኖር የሚገባበት ሁኔታ
መኖሩ ታውቋል፡፡ በዚህ ሂደት ከመንገደኞች አውሮፕላን ዕቃዎች በሚራገፉበትና
በካርጎ መጋዘን መካካል ረዥም ርቀት ያለው በመሆኑ ዕቃዎቹ በመንገድ ላይ ቢጠፉ
ሊታወቅ የሚቻልበት ሁኔታ መኖሩ አጠራጣሪ ከመሆኑም በላይ ጉድለትም ቢከሰት
አየር መንገዱ ተጠያቂ ሊያደርገው የሚችል አካል ያለመኖሩ ዕቃዎች ለመጥፋት
ያላቸው ተጋላጭነት ከፍተኛ መሆኑን ያሳያል፡፡ ይህ አሰራር ዕቃዎችን በተለይ በምሽ
ት ጊዜ አሳቻ ቦታ በመሰወር ለመስረቅ /ለማስወጣት/ አመቺ ሁኔታ ሊፈጥር መቻሉን
ያመለክታል፡፡ አየር መንገዱ ዕቃዎችን በሀላፊነት ተረክቦ መጋዘን ገቢ ሊደረጉ የሚች
ልበት አሰራር ባለመቀየሱና የቁጥጥር ተግባሩ ለአየር መንገዱ ተጠሪ ባልሆነና ሊቆጣ
ጠረው በማይችለው በደህንነት /ሴኩሪቲ/ ላይ እንደወደቀ ታሳቢ መደረጉ ተጠያቂነትን
በማላላት ለዕቃዎች መጥፋትና ላልተገባ የካሳ ክፍያ ሊዳርገው የሚችልበት ክፍተት
ሊፈጠር እንደሚችል አመላካች ነው፡፡
37
ጭነት ወደ መጋዘን ከገባ በኋላ ሲስተም ላይ ተጭኖና የብተና ሥራ ተከናውኖ ወደ
ተገቢው ቦታ ይላካል፡፡ በዚህ ወቅት ለትራንዚት የተራገፈው ዕቃ መጋዘን ውስጥ
ተገፍቶ ወይም በፎርክ ሊፍት ሠራተኛ ተጭኖ ለየሀገሩ በተዘጋጀው መደርደሪያ ላይ
ወይም ለትራንዚት ተከልሏል በሚባልበት ክልል ሜዳው ላይ /በመጋዘን ውስጥ/
ይራገፋል፡፡ በሌላ በኩል ለአየር መንገዱ ሥራ አገልግሎት የሚመጣው /COMAT/
እንዲሁም ለሌሎች ለምሳሌ በ DHL እና ለግል ድርጅት /ለሚድሮክ፣ ኢካስ/ የሚመጡ
ዕቃዎች በተመሳሳይ መልኩ በዚሁ መጋዘን ውስጥ ይቀመጣሉ፡፡ በመጋዘኑ ውስጥ
በሚገኙ የተለያዩ የሥራ ዘርፎች መካከል የሰነድ ርክክብ ባለመኖሩና ከመጋዘኑም ጥበት
የተነሳ ዕቃዎቹ በውጪ ሜዳ ላይ እና በመጋዘን ውስጥ መሬት ላይ በየቦታው ተበታትነው
ማየት የተለመደ ነው። በዚህ የተነሳ ለአንዱ የተላከው ዕቃ ከሌላው ጋር የሚደበላለ
ቅበትና በዚህ አጋጣሚም ዕቃዎች የሚጠፉበት ሁኔታ የሚከሰት መሆኑን የተገኘው
መረጃ ያመለክታል፡፡ ይህን ክፍተት ተጠቅሞ ዕቃዎችን በስርቆት ለማውጣት ሰፊና ምቹ
ሁኔታን የሚፈጥር ሆኖ ይታያል፡፡
38
ሳይደረጉ ወይም ሳይጫኑ ቢቀሩ አመቺ ጊዜ በመጠበቅና ሁኔታዎችን በማመቻቸት
ዕቃዎችን በስርቆት ለማስወጣት ክፍተት ከመፍጠሩም በላይ ኤየር ዌይ ቢል /AWB/
የሌለው ዕቃ በሚመጣበትም ወቅት ምዝገባ የማይካሄድ በመሆኑ እንደዚሁ ለስርቆት
በከፍተኛ ሁኔታ ሊጋለጥ እንደሚችል የተገኘው መረጃ ይጠቁማል፡፡
39
ተገቢው መረጃ ሳይያያዝ ሊያልፍ ይችላል፡፡ ስለዚህ በመሸኛ ደብዳቤዎቹ ላይ የተቀመጡ
ትን እንደ ቼክ ሊስት መጠቀምና መልዕክት ልውውጦች ላይ የተቀመጠው /AWB/ ቁጥር
ትክክል መሆኑን አረጋግጦ የሚያቀርበው እና የሚላከውን ሰነድ የሚያዘጋጀው
ሠራተኛ በቅፁ ላይ ስምና ፊርማ ሊካተት የሚያስችል አሰራር ቢዘረጋ ተጠያቂነትን
ያጎለብታል፡፡
ይህን ችግር ለማቃለል አየር መንገዱ ባለው መዋቅር ያሉት ክፍት የሥራ መደቦች
በአብዛኛው የተሟላና በሂደትም ላይ ያለ መሆኑ /ከላይ በተገለፀ/ የሥራ መደቦች መረ
ጃው የሚጠቁም ቢሆንም ከዚህ ባለፈ ሁኔታ የሰው ሃይሉ ከሥራው ጋር መጣጣሙን
በድጋሚ በመፈተሽና ተገቢውን ጥናት በማካሄድ በውጤቱ መሰረት ሊስተካከል
የሚችልበትን ሁኔታ ማመቻቸት ወሳኝ እንደሆነ ጥናቱ ጠቁሟል፡፡
በመረጃ ማሰባሰቡ ወቅት የተገኘው መረጃ በአየር መንገዱ በኩል ዕቃዎች ከአውሮፕላ
ን እስከ መጋዘን እስከሚደርሱ ብሎም በመጋዘን አካባቢ በሚከማቹበትም ሆነ ከመጋዘን
ወደ አውሮፕላን በሚጓጓዙበት ወቅት የእቃዎቹ ቁጥጥር በደህንነቱ አማካኝነት
እንደሚከናወን ይገልፃል፡፡ የኤርፖርት ሴኩሪቲ በበኩሉ ሥራው ከዕቃው ጋር ለደህንነ
ት አደጋ ሊያስከትሉ የሚችሉ በተለይ በወጪ ዕቃዎች ላይ የሚያተኩር ሆኖ በኤክስሬ
ይ ማሽን ካለፉ በኋላ ንኪኪ እንዳይፈጠር ብሎም የአውሮፕላንና የደንበኞችን ደህንነት
በተመለከተ ቁጥጥር እንደሚያደርግና ለዕቃዎቹ መጥፋት ኃላፊነት የሌለበት መሆኑን
በአፅንኦት ይገልፃል፡፡ ይህ ሁኔታ ዕቃዎች ከአውሮፕላን ወርደው በመጋዘን እስከሚገቡ
በሜዳው ላይ በሚቆዩበት ጊዜ ዕቃዎችን የሚቆጣጠር አካል ያለመኖሩን ከማመልከቱ
በላይ የዕቃዎች መጥፋት ቢከሰትም በዚህ ሂደት መጥፋቱን ለማረጋገጥ ያለመቻሉና
በሁለቱም በኩል ዕቃዎችን በተመለከተ ተጠያቂ የሌለበት አሰራር መኖሩን ይጠቁማል፡፡
40
ከዕቃዎች ጥበቃና ቁጥጥር አንፃር ሊከናወኑ የሚገባቸውን ተግባሮች በመለየትና በመ
ወያየት በግልፅ መረዳት፣ በአየር መንገዱ በኩል ሊወሰድ የሚገባውን እርምጃ አጥንቶ
መተግበር እና በተወሰነ የጊዜ ገደብ ቋሚ የጋራ መድረክ በመፍጠር የቅንጅት ሥራው
ን በተጠናከረ መንገድ እንዲከናወንና ለችግሮቹም በወቅቱ መፍትሄ ለመስጠት ጥረት
ማድረግ የአሰራር ሥርዓት ችግሩን ለመቅረፍ በጥናቱ የተጠቆመ ሊተገበር የሚገባው
መፍትሄ ነው፡፡
41
በብሔራዊ የመረጃ ደህንነት አገልግሎት የኢሚግሬሽንና
ዜግነት ጉዳይ ዋና መምሪያ የመንገደኞች የይለፍ ማረጋገጫ
አሰጣጥ እና የአገልግሎት ክፍያ ገንዘብ ገቢ አሰባሰብ የአሰራር ሥርዓት
42
እርምጃ ለመውሰድ ማስቻሉ፣ ጥሩ ሥነምግባር ያላቸው ሠራተኞች እንዲበረታቱና
እንዲበራከቱ ማድረጉና ግልፅነትና ተጠያቂነት ያለው አሰራር እንዲሰፍን ማድረጉ
የሚሰጣቸው ጥቅሞች ናቸው፡፡
43
ከአገልግሎት የሚሰበሰብ ገንዘብ በየእለቱ ወደ ባንክ ገቢ አለማድረግ፣ ከመጠን በላይ
በካዝና ገንዘብ ማሳደር፣ የዕለት ገንዘብ ሰብሳቢዎች በየዕለቱ የሚሰበስቡትን ገንዘብ
አግባብ ያለው ወቅታዊ ቁጥጥርና ክትትል እየተደረገበት ለባንክ ገቢ አለመሆን፣
የሂሳብ ምዝገባ በየቀኑ ስለማይመዘገብ አግባብ ያለውን ክትትልና ቁጥጥር ማድረግ
አለመቻልና የገቢ ሒሳብ ምዝገባ ሳይከናወን ለረጅም ወራት ማከማቸት፣ የገቢ
ሒሳብ እንቅስቃሴ መዝገብ በኮምፒውተር በየጊዜው ስለማይመዘገብ ሒሳቡን በወቅቱ
አለመዝጋት፣ የገንዘብ መቀበያ ደረሰኞች አያያዝና አጠቃቀም ብክነት ያለበት መሆንና
ተከታታይነት አለመኖርና እና የሚሰበሰበው ገንዘብና ወደ ባንክ ገቢ የሚሆነው ገንዘ
ብ ከደረሰኞች ጋር በወቅቱና በዕለቱ ማመዛዘኛ /balance/ አለመሰራት…ወዘተ ናቸው፡፡
44
በማድረግ፣ ሪፖርቶችን ወቅታዊና አግባብ ባለው መልኩ በማዘገጀትና ለሚመለከታ
ቸው አካላት በማቅረብ የተደራጀ የመረጃና የሪፖርት አቀራረብ፣ አያያዝና አጠቃቀም
ሥርዓት መዘርጋት ሲሆን ይህም ጠንካራ የመረጃና የሪፖርት አቀራረብ፣ አያያዝና
አጠቃቀም ስርዓት እንዲኖር ያደርጋል፤ ለሙስናና ለብልሹ አሰራር ክፍተት የሚፈጥ
ሩ ሁኔታዎችን ይከላከላል፡፡ ችግሮችን በቀላሉና በወቅቱ በመለየት የማስተካከያ ዕርምጃ
ለመውሰድ ያስችላል፡፡
45
ላይ ሥልጠና የሚሰጥ ቢሆንም እንኳን የፎርጀሪና ማጭበርበር መንገዶች እንደ ወቅታ
ዊ ቴክኖሎጂ የሚሻሻሉና የሚለወጡ በመሆኑ በብቃት ለመከላከል የሚያስችል የአሰራር
ሥርዓት አልተዘረጋለትም፡፡ ስለዚህ በሁለቱም የሥራ ክፍሎች የሚሰራበት የአሠራር
ሥርዓት በቀላሉ ለሙስናና ብልሹ አሰራር ክፍተት ለሚፈጥሩ ሁኔታዎች የተመቻቸ
ነው፡፡
46
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቤቶች አስተዳደር አሰራር ሥርዓት
47
በተለያዩ ምክንያቶች ባለሁለት መኝታ ቤትን ብቸኛ ለሆነ ተጠቃሚ በጊዜያዊነት
መፍቀድ… ወዘተ የሚሉ እርስ በርስ የሚጣረሱ አንቀፆች መኖር፣ በአንቀፅ 7(2)
መሠረት የመኖሪያ ቤት ድልደላ ኮሚቴ ተጠሪነቱ ለአስተዳደርና ልማት ምክትል
ፕሬዝዳንት ይሆናል ሲል በአንቀፅ 7(4) መሠረት ደግሞ ኮሚቴው 8 አባላት እንደ
ሚኖሩትና ከነዚህም መካከል የአስተዳደርና ልማት ተባባሪ ም/ፕሬዝዳንት እንደ አባል
ድምፅ የሚሰጥ መሆኑን ይገልፃል፡፡
48
ጥያቄውን ማቅረብ እንዲችል ማድረጉ የሚቀርቡ ማስረጃዎችን ተዓማኒነት ያጠናክራል፡፡
ይህን ችግር ለመፍታት አግባብ ያለው የቤቶች ርክክብ ሥርዓት እንዲኖር ማድረግና
የዩኒቨርሲቲው ባልደረቦች ሥራቸውን ሲለቁ በመልቀቂያ ወረቀት /ክሊራንስ/ ላይ
የሚመለከተው አካል /የቤቶች አስተዳደር መምሪያ/ እንዲፈርም ማድረግ በጥናቱ
የቀረበ የመፍትሔ ሀሳብ ነው፡፡
ይህ የመፍትሔ ሀሳብ ተግባሪዊ ሲሆን የUNDP ቅጥር የሆኑና ወርሃዊ የቤት አበል
በትምህርት ሚኒስቴር በኩል የሚከፈላቸው የዩኒቨርሲቲው አባላት ኮንትራታቸው
ሲያልቅ እና በነፃ የሚኖሩትን /visiting professors or volunteers/ በተመለከተ ወቅታዊ
መረጃ በቀላሉ ለማግኘት ስለሚያዳግት እና ተጠቃሚዎች ዩኒቨርስቲውን ሲለቁ ወደ
ሥራ ክፍሉ ላይመጡ ስለሚችሉ የቤቶች አስተዳደር የሥራ ክፍል ከትምህርት
ሚኒስቴርና ከሚሰሩበት የሥራ ክፍል ጋር በመሆንና በመከታተል አስቀድሞ ለተጠ
ቃሚዎች ማሳወቅ የመፍትሄ ትግበራውን ተከትሎ መወሰድ ያለበት እርምጃ መሆኑ
በጥናቱ ተጠቁሟል፡፡
49
በቅጣት ደረጃ የተቀመጡትን አንቀፆች ማሻሻል ተገቢ ነው፡፡
50
የአሰራር ሥርዓት ችግሩን ለመፍታት የተጠናከረ የውስጥ ቁጥጥር ሥርዓት በሥራ
ክፍሉና በውስጥ ኦዲት መዘርጋት ቢቻል እና ይህን ሥራ ዩኒቨርሲቲው ማከናወን
ካልቻለ የውጪ አካል እንዲሠራው /out source/ በማድረግ ሁኔታዎችን ማመቻቸት
በጥናቱ የተጠቆመ የመፍትሔ ሀሳብ ነው፡፡ ይህ የመፍትሔ ሀሳብ ለአስተዳደራዊ
ጉዳዮች ተጨማሪ ወጪ ሊያስወጣ ስለሚችል በቂ ትኩረት በመስጠት አስቀድሞ በጀት
እንዲያዝ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡
51
ተጨማሪ ክፍያ ለኪራይ ቤቶች ኤጀንሲ ከፍሏል፡፡ ነገር ግን ቤቶች እስከ ሁለት ዓመት
ተዘግተው ኪራይ መክፈል፣ ኪራይ ሳይከፍሉ በነፃ የሚኖሩትን ታሳቢ ያላደረገ የቤት
ኪራይ ክፍያው በወሩ ስለሚፈፀም ነዋሪዎች መክፈል ከሚገባቸው የቤት ኪራይ
በታች እየከፈሉ እንዲኖሩ የተመቻቸ ሁኔተ ፈጥሯል። የውሃ የስልክ የመብራት ክፍያም
በተመሳሳይ ገቢ አሰባሰብ ላይ ችግር ያለበት ሆኖ ይታያል፡፡ ዩኒቨርሲቲው ከኪራይ
ቤቶች አስተዳደር ኤጀንሲ ተከራይቶ የነበረው ወረዳ 21 ቀበሌ 01 የቤት ቁ. 397/33፣
ወረዳ 2 ቀበሌ 12 የቤት ቁ. 487/02 እና የቤት ቁ. 332/21 እንዲሁም ቦሌ ከሦስት
ዓመት በፊት ከዩኒቨርስቲው ሥራ ለቀው ውጭ አገር የሚኖሩ የቤት ኪራዩንም ሳይከፍ
ሉ ለ2ኛ ወገን አከራይተው እንደሄዱ እንደ ምሳሌ መንሳት ይቻላል፡፡
ለዚህ የአሰራር ሥርዓት ችግር በጥናቱ የተጠቆመው የመፍትሄ ሀሳብ ዓመታዊና ድንገ
ተኛ ቆጠራ ማካሄድ ነው፡፡ ይህን ሥራ ዩኒቨርሲቲው በራሱ ማከናወን ካልቻለ በውጪ
አካል ማሠራት ይችላል። ይህ አሠራር በተጠቃሚዎች ዘንድ ከሚፈጠረው ችግር ጋር
በተያያዘ ጥሩ ምላሽ ላያገኙ ይችላሉ፡፡ ሆኖም ግን ተገልጋዮችን በማሳመን በሚቀርቡ
ችግሮች ላይ ወቅታዊ የመፍትሄ እርምጃ መውሰድ እንደሚያስፈልግ በጥናቱ ተቀምጧል፡፡
52
ስለመድረሳቸው ማረጋገጫ የለም። እንዲሁም ወጪ ያደረገው ተጠቃሚ አካል ብቻ በንብ
ረቱ ስለመጠቀሙ በቂ የሆነ መከታታያና መቆጣጠሪያ ስልት ካለመዘርጋቱም በላይ ዕቃዎች
ከቤቶች ጋር ወይም ብቻቸውን ለሌላ ሦስተኛ ወገን በኪራይ መጠቀሚያ ሲሆኑ ይታያል።
53
የጥቁር አንበሳ ሆስፒታል የውጭ ሀገር ሕክምና የቦርድ ፈቃድ አሰጣጥ
አንድ ታካሚ መጀመሪያ በውጭ ሀገር ተቀብሎ ሕክምና የሚያደርግለት የጤና ተቋም
አፈላልጎ ማግኘቱንና ተቀባይነት ማግኘቱን የሚያሳይ ደብዳቤ ለሕክምና ቦርድ አባላት
ያሳያል፡፡ በመቀጠልም የሕክምና ክፍሉ ወይም ሆስፒታሉ የውጭ ሕክምና ቦርድ
የምስክር ወረቀት ይሰጣል፡፡ ይሁን እንጂ ታካሚው የውጭ ሕክምና ማግኘቱን የሚገ
ልፀውን ደብዳቤ ለሕክምና ቦርድ አባላት ከማሳየት ውጪ በሰነድ ማስረጃነት ከሕክምና
54
ታሪኩ ጋር ካለመያያዙም በላይ ለትክክለኝነቱም ለሆስፒታሉ ሜዲካል ዳይሬክተር
የሚቀርብበት አሠራር አለመኖሩን ጥናቱ ይጠቁማል፡፡ በዚህ የተነሳም ታካሚዎችን
ተቀብሎ ሕክምና የሚያደርግላቸውን ተቋም ያገኙ ወይም ያላገኙ ታካሚዎችን
በትክክል ለመለየት አያስችልም፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ታካሚው የት ሀገር ሄዶ እንደ
ሚታከም የሚያሳይ ገላጭ ማስረጃ ባለመኖሩ የአሠራር ሂደቱ ግልጽነት ይጎድለዋል፡፡
በመሆኑም የውጭ ሀገር ሕክምና ቦርድ ምስክር ወረቀት ለማግኘት በውጭ ሀገር ባለ
ሕክምና ተቋም ተቀባይነት ያላገኙ ታካሚዎች በቀላሉ የውጭ ሀገር ሕክምና ቦርድ
ማስረጃ አለአግባብ ተጽፎ እንዲሰጣቸው መንገድ ይከፍታል፡፡
ይህንን ችግር ለመቅረፍ ታካሚው የውጭ ሀገር ሕክምና ሊሰጠው የሚችል ተቋም
ማግኘቱን የሚገልጽ የሰነድ ማስረጃና ፎቶ ኮፒውን ከሕክምና ፋይሉ ጋር አያይዞ
ለሜዲካል ዳይሬክተሩ ማቅረብ እና ዳይሬክተሩ ትክክለኝነቱን ካረጋገጠ በኋላ ዋናውን
ማስረጃ በመዝገብ ቤት በኩል ለታካሚ ተመላሽ ማድረግ እንዲሁም ኮፒውን ከዋናው
ጋር በማመሳከር ከታካሚ ሕክምና ታሪክ ጋር ተያይዞ እንዲቀመጥ ማድረግ በመፍት
ሄ ሃሳብነት ተጠቁሟል፡፡ ይህም የሰነድ መጭበርበርን ከመቀነሱም በላይ የውጭ ሀገር
ሕክምና ቦርድ ምስክር ወረቀት ሊሰጣቸው የሚገባና የማይገባቸውን ታካሚዎች
/ግለሰቦች/ በሰነድ ማስረጃው መሠረት ለመለየት ያስችላል፡፡
የውጭ ሀገር ሕክምና ቦርድ ምስክር ወረቀት አዘገጃጀት በቀላሉ በተጭበረበረ ሰነድ
ተዘጋጅቶ የሚቀርብበት ሁኔታ እንዳለ ጥናቱ አመልክቷል፡፡ ለአብነትም ያለ ሆስፒታ
ሉ ሜዲካል ዳይሬክተር ፊርማ አስመስሎ የማቅረብ፣ ሆስፒታሉ ያልፃፈውን እንደፃፈ
አድርጎ ለተለያዩ መንግሥታዊና መንግሥታዊ ላልሆኑ ተቋማት የተሳሳተ የሕክምና
ማስረጃ የሚቀርብበት ሁኔታ መኖራቸውን መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ ለሰነድ መጭበ
ርበሩ በሆስፒታሉ የሚዘጋጀው የውጭ ሕክምና ቦርድ ምስክር ወረቀት ራሱን በቻለ
ወጥ እና ልዩ በሆነ መንገድ ተዘጋጅቶ፣ ቁጥር ተሰጥቶት እና እንደማንኛውም ንብረት
የገቢ እና ወጪ ሥርዓት ተከናውኖበት አለመቅረቡ በምክንያትነት በጥናቱ ተጠቁሟል፡፡
እንዲሁም የሚዘጋጀው የምስክር ወረቀት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲን ዓርማ ወይም
በሥሩ የሚተዳደሩትን ሥራ ክፍሎች ዓርማ እና ሄደር ያልያዘ በመሆኑ ለመጭበርበር
55
የተጋለጠ እንዳደረገው ተጠቅሷል፡፡
ይህን ችግር ለማቃላልም የውጭ ሀገር ሕክምና ቦርድ ምስክር ወረቀት አንድ ወጥና
ልዩ በሆነ ሰነድ ማዘጋጀት፣ የሆስፒታሉ ዓርማና ሄደር እንዲኖረው ማድረግ፣
የሞዴል /ሴሪ ቁጥር ተሰጥቶት መዝገብ ቤት/ ንብረት ክፍል ገቢ ማድረግና ለሥራ
ሲፈለግ በወጪ ማዘዣ ተጠይቆ ጥቅም ላይ ማዋል እንደመፍትሄነት በጥናት ቡድኑ
ቀርቧል፡፡ በተጨማሪም የሕክምና ቦርድ አባላትንና የሜዲካል ዳይሬክተሩን/ተወካዩን
የፊርማ ናሙና በሆስፒታሉና በጤና ጥበቃ ሚኒስቴር መዝገብ ቤቶች ማስቀመጥና
የተለያዩ የጤና አገልግሎት ክፍሎች ይዘው የሚመጡትን የምስክር ወረቀት ማመሳከር
እንደሚያስፈልግም ተጠቁሟል፡፡
56
አዲስ አበባ ጤና ቢሮ የግል ሆስፒታሎች፣
ዲያግኖስቲክ ላብራቶሪዎች፣ ኤች.አይ.ቪ ምርመራና የውጪ ዜጎች
የግል ክሊኒክ የሙያ ፈቃድ አሰጣጥ
በሌላ በኩል የሙያ ፈቃዱን ለመስጠት ህጋዊ ስልጣን የተሰጠው የሥራ ኃላፊ
በግልፅ የማይታወቅ መሆኑም /በፅሁፍ የሰፈረ ባለመኖሩ/ ሌላው የታየ ችግር ነው፡፡ ለምሳሌ
አንዳንድ የሙያ ፈቃድ በኢንስፔክተሩ አስተያየት መነሻ ብቻ የሚሰጡ ሲሆን ሌሎቹ
ደግሞ በቡድን መሪው አስተያየትና ውሳኔ ወጥነት በሌለው መልኩ የሚሰጡ መሆኑን
ለመገንዘብ ተችሏል፡፡ ይህ አሰራር ማን ምን እንሚሰራ በግልፅ ባልተቀመጠበት ሁኔታ
የሚከናወን በመሆኑ ኃላፊነትና ተጠያቂነት እንዳይኖር የሚያደርግና ለሙስናና ብልሹ
አሰራር ክፍተት የሚፈጥር ነው፡፡
57
ኃላፊ ተገቢውን የሥልጣና ውክልና መስጠትና የሚመለከታቸው የሥራ ክፍሎች
እንዲያውቁት ማድረግ፣ የውሳኔ ሃሳቡ በምክትል የቢሮ ፀሐፊ እንዲፀድቅ እና የጤና
አገልግሎት ማደራጃና ማከፋፈያ መምሪያ በሙያ ፈቃዱ ላይ እንዲፈርም ማድረግ
የተሻለ አማራጭ ነው፡፡
ለዚህ የአሰራር ሥርዓት ችግር ከፈቃድ ሰጪው የሥራ ዘርፍ ውጪ የሆኑ ባለሙያ
ዎች ያሉበት የኢንስፔክሽን ቡድን ማደራጀት፣ ማመሳከሪያ /check list/ በማዘጋጀትና
ዕቅድ በመንደፍ በተወሰኑ ጊዜያት ውስጥ የግል ህክምና አገልግሎት ሰጪ ተቋማትን
በመፈተሽ ብቃቱንና ደረጃውን ማረጋገጥ የሚሉት በመፍትሄ ሃሳብነት የቀረቡት
ናቸው፡፡
የመረጃ ቅበላ፣ አያያዝና ቁጥጥር የተሟላና የተጠናከረ አለመሆን ሌላው በጥናቱ የታየ
የአሰራር ሥርዓት ችግር ነው፡፡
58
የቢሮው መዝገብ ቤት አሰራር ወጥነትና ተጠያቂነት ያለበት እንዲሁም የተጠናከረ
ቁጥጥር ያለው አሰራር እንዲኖረው ለማስቻል መመሪያ ማዘጋጀት፣ ለሠራተኞች ሥራ
መዘርዝር አዘጋጅቶ በመስጠትና በቂ ስልጠና እንዲያገኙ በማድረግ መረጃዎች በአግባ
ቡ እንዲደራጁና እንዲጠበቁ ማድረግ፣ የሙያ ፈቃድ ጥያቄዎች በመዝገብ ቤት ገቢ ሆነ
ውና ተመዝግበው እንዲቀርቡና ለማህደር ቀሪ የሚደረገው የሙያ ፈቃድ ዋናው ሳይሆ
ን ኮፒ እንዲሆን በማድረግ ሰነዶች እንዳይጠፉ፣ እንዳይለወጡ፣ እንዳይሰረቁና ለህገወጥ
ድርጊት እንዳይውሉ ተገቢውን ምዝገባና ቁጥጥር በማካሄድ ችግሩን ማቃለል ያስችላል፡፡
በጤና ጥበቃ ሚኒስቴር በወጣው የግል ሆስፒታል መመሪያ ቁጥር 1/1989 ክፍል 5
ተራ ቁ.12 እና 13 ላይ ፈቃድ ስለማገድና ስለመሰረዝ የተደነገገ ቢሆንም በአፈፃፀም
ላይ ችግሮች እየተከሰቱ መገኘታቸው በቃለ መጠይቁ ወቅት ለመረዳት ተችሏል፡፡
በመመሪያው ውስጥ የህክምና ሥነምግባር ያላከበረ ፈቃዱ እንደሚታገድ /እንደሚሰረ
ዝ/ ተደንግጓል። ይሁን እንጂ እገዳው /ስረዛው/ የሚቆየው እስከመቼ እንደሆነ፣ የታገ
ደበትን የሙያ ፈቃድ መልሶ ሌላ የሙያ ፈቃድ ቢጠይቅ ሊወሰድ ስለሚገባው እርምጃ
መመሪያው በግልፅ ያስቀመጠው ነገር ባለመኖሩ አፈፃፀሙን አስቸጋሪ አድርጎታል፡፡ በዚህ
ዓይነት አሰራር የሚወሰነው ውሳኔ በግለሰቦች አስተያየት ላይ እንዲመረኮዝ ለማድረግ
የሚያስችል በመሆኑ ለድርድርና ለአድሎ ክፍተት ሊፈጥር ይችላል፡፡
ይህን የአሰራር ሥርዓት ችግር ለመፍታት በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የጤና
አገልግሎት አሰጣጥ አስተዳደርና አመራር አዋጅ ቁጥር 10/1995 ክፍል ሁለት ተራ
ቁ. 15 ‘‘ቢሮው የመንግሥትና የግሉ ዘርፍ የጤና ተቋማትና በእነዚህ የጤና
ተቋማት ውስጥ የሚሰሩ ባለሙያዎችና ድጋፍ ሰጪ ሠራተኞች ሊከተሉት የሚገባውን
የሙያ ሥነምግባር ደንብ አዘጋጅቶ በካቢኔው አፅድቆ ሥራ ላይ እንዲውል ያደርጋል’’
ይላል፡፡ በዚህ መሠረት ቢሮው የሥነምግባር ደንቡን አዘጋጅቶ ቢያፀድቅ በህክምናው ዘርፍ
የሚታየውን ኃላፊነት የጎደለውን አሰራር በማስቀረት ግልጽነትና ተጠያቂነትን ያለበት
አሰራር ለማስፈን ያስችላል፡፡
59
የማይኖርበት ሁኔታ ከመታየቱም በላይ ባለሃብቶቹ ሲመጡ በጤና ቢሮ ወይም በክፍለ
ከተማ የሚስተናገዱ ስለመሆናቸው በቃል ከቢሮው እንደሚገለፅላቸው ለመረዳት ተችሏል፡፡
ይህም ጤና ቢሮው አንዳንድ ጊዜ በራሱ የሙያ ፈቃዱን የሚሰጥበትና በሌላ ጊዜ ደግሞ ወደ
ክፍለ ከተማ ሄደው እንዲወስዱ ሊደረግ የሚችልበት ሁኔታ መኖሩ ለፍቃድ ጠያቂው ግልፅ
ባልሆነ ሁኔታ ሊጉላላ ይችላል። በዋነኛነትም አሰራሩ ለአላስፈላጊ ድርድር በር የሚከፍት ነው፡፡
ይህን የአሰራር ሥርዓት ችግር ለመቅረፍ በጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ነሐሴ 1994 ዓ.ም
የግል ክሊኒክ ፈቃድ አሰጣጥ ለሁለተኛ ጊዜ ተሻሽሎ በወጣ መመሪያ ላይ ልዩ
ክሊኒክ ብሎ ባሰፈረውና ሊሟሉ የሚገባቸውን ሁኔታዎች በደነገገው መሠረት ተግባራ
ዊ መደረግ ይኖርበታል፡፡
60
መኖሩን የማጣራትና ስታንዳርድና ብቃቱን የማረጋገጡ ሥራ ደካማ መሆኑን
ያመለክታል፡፡ ይህም ከተፈቀደ ደረጃ በላይ መረጃ ባላቀረበ ባለሙያ ባልተፈቀደ የህክምና
መሣሪያ ጭምር አገልግሎት ሊሰጥበት የሚያስችል ክፍተት የሚፈጥርና ለብልሹ
አሰራር ሊያጋልጥ የሚችል ይሆናል፡፡
የአሰራር ሥርዓት ችግሩን ለመፍታት በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የጤና አገልግሎ
ት አሰጣጥ የአስተዳደርና አመራር አዋጅ ቁጥር 10/ 1995 ክፍል አንድ አንቀፅ 3 ንዑስ
አንቀፅ 4 ‘‘ማንኛውም የጤና አገልግሎት በመስጠት ተግባር ላይ ለሚሰማራ ሰው
ከቢሮው የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ሳያገኝ ሥራ መጀመር አይችልም’’ በማለት የተደነገገ
ውን ተግባራዊ ማድረግ ወሳኝ ነው፡፡
61
የሸቀጦች ጅምላ ንግድና አስመጪ
ድርጅት የሲሚንቶ ሽያጭ አፈፃፀም ሥርዓት
62
በደብረ ዘይትና በአዳማ የጅንአድ ቅርንጫፎች ለግል ቤት ሠሪዎችና ኢንቨስተሮች
የሚሰጣቸው የሲሚንቶ መጠን የአካባቢው የከተማ ልማት ጽ/ቤት ግንባታው አሁን
ያለበትን ደረጃ ከግምት በማስገባት ሲሆን በአዲስ አበባ ቃሊቲ ቅርንጫፍ ግን ሲሚንቶ
ፈላጊዎች ቀደም ብለው ለሙገር ሲሚንቶ ፋብሪካ ጥያቄ ያቀረቡበትን መረጃ መሠረት
በማድረግ ነው፡፡ ይሁን እንጂ ይህ መረጃ ወቅታዊ ያልሆነ፣ ከሙገር ሲሚንቶ መውሰ
ድ አለመውሰዳቸውን እንዲሁም ከወሰዱ ምን ያህል መጠን እንደወሰዱ የሚረጋገጥበት
አሠራር አለመኖሩ እና የሚፈቀድላቸውም ሲሚንቶ ግምታዊና ለግል ውሳኔ የተጋለጠ
መሆኑ በጥናቱ ታውቋል፡፡ ይህም በሽያጭ ማዕከሎች ወጥ የሆነ አሠራር አለመኖሩን
የሚያመለክት በመሆኑ በሁሉም ማዕከሎች በተመሳሳይና ወጥ በሆነ መልኩ ሽያጩን
ማከናወን እንደሚያስፈልግ ተጠቁሟል፡፡
በጅንአድና በሥራና ከተማ ልማት ሚኒስቴር መካከል ያለው የሥራ ግንኙነት ግልጽነ
ት የሌለው መሆኑ ሌላው በጥናቱ የተጠቆመ የአሰራር ሥርዓት ችግር ሆኖ ታይቷል፡፡
የሥራና ከተማ ልማት ሚኒስቴር ሲሚንቶ ፈላጊዎችን በደረጃ ሲመድብ መስፈርቱ
በግልጽ ባልተቀመጠበት ሁኔታ /ደረጃ አንድ፣ ደረጃ ሁለትና ደረጃ ያልተሰጣቸው/ ብሎ
በመከፋፈል የተወሰኑት ደንበኞች ቅድሚያ እንዲያገኙ መደረጉን ለማረጋገጥ ተችሏል፡፡
ይህም በሥራና ከተማ ልማትና በጅንአድ መካከል የተፈጠረው የሥራ ግንኙነት ምን
መምሰል እንዳለበት በግልጽ የሰፈረ መመሪያ ያልተገኘ በመሆኑ አሠራሩ ተጠያቂነትን
የሚያላላ፣ ለሙስናና ብልሹ አሠራር ክፍተት ሊፈጥር የሚችልበት ዕድል ሰፊ ነው፡፡
63
የሥራና ከተማ ልማት ሚኒስቴር የግንባታ
ሥራዎች ፈቃድና እድሳት አሰጣጥ የአሰራር ሥርዓት
64
የግንባታ ሥራ እንዲያከናውኑና የሕዝብ ሀብት ያለአግባብ እንዲባክን ከማድረጉም
በተጨማሪ ሕገወጥ ሥራ እንዲሰራ በር የሚከፍት ሆኖ ታይቷል፡፡
65
ምክንያት ተቋራጮች ከዚህ በፊት ያከናወኗቸውን ሥራዎች ብቃትና ውጤታማነት እንዲሁ
ም ግንባታው በሚከናወንበት ሥፍራ ተቋራጩ ያስመዘገባቸው ማሽነሪዎችና ባለሙያዎች
ሥራ ላይ ስለመኖራቸው በተጨባጭ የሚረጋገጥበት ሥርዓት አልተዘረጋም። በዚህ
ሁኔታ የሚሰጡ የሥራ ተቋራጭነት ፈቃዶች ጥራታቸውንና የጥንካሬ ደረጃውን
ያልጠበቁ ግንባታዎች እንዲገነቡ እና የህዝብን ደህንነት አደጋ ላይ እንዲወድቅ የሚያደርጉ
ናቸው፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ከተለያዩ ቦታዎች ሊቀርቡ በሚችሉ ሐሰተኛ ፕሮጀክት
አፈፃፀም ማስረጃዎች ምክንያት በፈቃድ አሰጣጥ ዙሪያ የማጭበርበር ሥራ
እንዲፈፀም በር ይከፍታል፡፡
66
ካለመደራጀታቸውም በላይ 2 ፋይሎች ወይም 3.92% ያህሉ የፋይል ምዝገባ ቁጥር 0109፣
0894 ሙሉ ለሙሉ አባሪ ቁጥር የተሰጣቸው ሲሆን 5 ፋይሎች ወይም 9.81% ያህሉ
የፋይል መዝገብ ቁጥር 1171፣ 0761፣ 1268፣ 2077፣ 0012 አባሪ ቁጥር ምዝገባ
ተጀምሮ የተቋረጠባቸው ናቸው፡፡ ቀሪዎቹ 44 ፋይሎች 86.27% የሚሆኑት ደግሞ
አባሪ ቁጥር አልተሰጣቸውም፡፡ ይህ ሁኔታ በተለያዩ ምክንያቶች ፍይሎች ከአንድ
ሥራ ክፍል ወደ ሌላ የሥራ ክፍል ለሥራ ጉዳይ ሲንቀሳቀሱ መረጃዎች ተገንጥለው
ሊጠፉ የሚችሉበትን ሁኔታ በማመቻቸት ሕገወጥ ለሆነ የሥራ አፈፃፀም መንገድ
የሚከፍት አሰራር ነው፡፡
ከዚህ በፊት ለፋይሎች አባሪ ቁጥር የመስጠት ሥራ የተጀመረ ቢሆንም ሥራው ጥናቱ
በተካሄደበት ወቅት የተቋረጠ በመሆኑ ጉዳዩ የሚመለከታቸው ኃላፊዎችና ሠራተኞች
ለችግሩ ተገቢውን ትኩረት ላይሰጡ ይችላሉ፡፡ ስለዚህ ጉዳዩ የሚመለከታቸው
ኃላፊዎች ለችግሩ ተገቢውን ትኩረት ሰጥተው ለጊዜው ተጨማሪ የሰው ኃይል
በመመደብ ሥራው በአጭር ጊዜ ውስጥ የሚጠናቀቅበትን ሁኔታ በማመቻቸት
የመፍትሄ ትግበራውን ተከትሎ የሚከሰተውን ስጋት ማስወገድ ይቻላል፡፡
67
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የውጭ
ማስታወቂያ ፈቃድ አሰጣጥ ቁጥጥርና ክትትል የአሰራር ሥርዓት
ወሳኝ በሆኑ ቦታዎች የዉጭ ማስታወቂያ ሠሌዳ ጨረታ ሳያወጡ ፈቃድ መስጠት
ሌላው በጥናቱ የታየ የአሰራር ሥርዓት ችግር ነው፡፡
68
ቦታዎች ጥናት ሳይደረግባቸውና ጨረታ ሳይካሄድባቸዉ አገልግሎት ላይ ይዉላሉ፡፡
ይህ አሰራር አገልግሎቱን የሚፈልጉ ድርጅቶችና ግለሰቦች በውድድር ላይ
በተመሠረተ መልኩ እንዳይስተናገዱ በማድረግ የተሻለ ገቢ ለማሰባሰብ ካለማስቻሉም በላይ
ግለሰቦች በድርድር የሚፈልጉት ቦታና ስፋት ያለውድድር ለማግኘት የሚችሉበት ሁኔታ
ሊፈጥር ይችላል፡፡
በሌላ መልኩ በልደታ ክ/ከተማ የግንባታ ፈቃድ የሥራ ሂደት ፈቃዱን ከሰጠ በኋላ
ለክ/ከተማዉ ወይም ለቀበሌው ሬጉላቶሪ ፈቃድ የተሰጠበትን ኮፒ አይሰጥም፡፡ በዚህ
ምክንያት ቀበሌዎች ላይ ያሉ ሬጉላቶሪዎች ፈቃድ መሰጠቱን አያውቁም፡፡ ከዚህ በተ
ጨማሪ የደንብ አስከባሪ የሥራ ሂደት ተጠሪነቱ ለፍትህና ህግ ጉዳዮች በመሆኑ የሬጉ
ላቶሪው የሥራ ሂደት በትብብር ደብዳቤ ከማሳወቅ ውጭ ደንብ አስከባሪዎች ሥራውን
ባይሰሩ የሚጠየቁበት የተዘረጋ ሥርዓት የሌላቸው በመሆኑ ወጥነት በጎደለው መልኩ
እየሰሩ ይገኛሉ፡፡ የደንብ ማስከበር የሥራ ሂደት በአግባቡ ባይሰሩ ወይም ከሥነምግባር
69
ውጪ ከባለጉዳዮች ጋር በመስማማት ቁጥጥሩን በማላላት ባለጉዳዮች ፈቃዳቸውን
እንዳያሳድሱ፣ ህገወጥ ማስታወቂያ የሰቀሉም እንዳያነሱ ለማድረግ የማያስችል ነው፡፡
ከላይ በዝርዝር ለመግለጽ እንደተሞከረው የውጭ ማስታወቂያ ፈቃድ አሰጣጥ
ቁጥጥርና ክትትል ሥራን በባለቤትነት የሚሠራው የሥራ ዘርፍ በግልጽ ባለመታወቁ
ኃላፊነትና ተጠያቂነትን በማላላት ለሙስናና ብልሹ አሰራር ክፍተት ከመፍጠሩም
በተጨማሪ ለመንግሥት ገቢ መደረግ ያለበት ሳይሰበሰብ የሚቀርበት አጋጣሚን
የሚፈጥር ሊሆን ይችላል ፡፡
70
ቁጥጥር የላላ መሆኑ ነው፡፡
• በየካ ክ/ከተማ ደረጃ 18,432 ድርጅቶችና ግለሰቦች የንግድ ፈቃድ የወሰዱ ሲሆን
ህጋዊ የውጭ ማስታወቂያ ፈቃድ የወሰዱ ግን 29 ብቻ መሆናቸውን ከየካ ክ/ከተማ
ገቢዎች ኤጀንሲ ለመረዳት ተችሏል፡፡
71
• በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ቀበሌ 17/18 ደግሞ 1970 የንግድ ፈቃድ የወሰዱ ሲኖሩ
በህጋዊ መንገድ የማስታወቂያ ፈቃድ የወሰዱ 216 ብቻ ናቸው፡፡
የፋይልና ሪከርድ አያያዝ ደካማነት በጥናቱ የታየ የአሰራር ሥርዓት ችግር ነው፡፡
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በናሙና ከተመረጡት ስድስት ክፍለ ከተሞች ውስጥ
ብዙዎቹ የውጭ ማስታወቂያ የፋይልና ሪከርድ አያያዝና አጠባበቅ ሥርዓት ባልጠበቀ
መልኩ ተበታትኖና ተዘበራርቆ የሚገኝ መሆኑን ለመመልከት ተችሏል፡፡ ማስታወቂያ
የወሰዱ፣ ያላሳደሱ እና በህገወጥ መንገድ የሚያስተዋውቁ ግለሰቦችና ድርጅቶች
72
መኖራቸውን ለመከታተልና ለመቆጣጠር የሚያስችል የሪከርድና ማህደር ሥርዓት
አልተዘረጋም፡፡ ከአንድ ዓመት በላይ ሳያሳድሱ የቆዩ የማስታወቂያ ተጠቃሚ ድርጅት ወይም
ግለሰብ የተጠቀመበትን የማስተዋወቅ የገንዘብ ቅጣት ሳይከፍል የሚቀርበት ሁኔታ አለ።
ሕገወጥ ማስታወቂያ ተጠቃሚዎችን ህጋዊ በሆነ መንገድ ከሚጠቀሙት ለይቶ ለማወቅ
የሚያስችል የፋይል አያያዝ ሥርዓት አልተዘረጋም፡፡ ይህ ዓይነት አሰራር ከማስታወቂያ
ፈቃድ ተጠቃሚ ደንበኞች ላይ ሊገኝ የሚገባው ገቢ በአግባቡ እንዳይሰበሰብ አስተዋጽኦ
የሚያደርግና የመንግሥትን ገቢ ግለሰቦችና ድርጅቶች ለራሳቸው ጥቅም እንዲያውሉት
የሚዳርግ ነው። ተቆጣጣሪ ሠራተኞች ከባለጉዳዮች ጋር የጥቅም ተካፋይ እንዲሆኑ በር
የሚከፍት በመሆኑ አሰራሩ ለሙስናና ለብልሹ አሰራር ሊያጋልጠው ይችላል፡፡
73
የውሃ ሥራዎች ኮንስትራክሽን ድርጅት የማሽነሪ
እና ተሽከርካሪ አገልግሎት ግዢ እና ክፍያ አፈፃፀም ሥርዓት
74
በማድረግ እንዲሁም ድርጅቱ ካለፈው ግዢ ተሞክሮና ልምድ በመነሳት አቅራቢዎችን
እየገመገመ መልካም አፈፃፀም የሌላቸውን ድርጅቶች ወጥ በሆነ መልኩ የሚለይበት
አሰራር በማስፈን ሕገወጥ ተግባር የሚፈፅሙትን መለየት እንደመፍትሄ ተቀምጧል፡፡
75
ተግባራዊነቱንም በቅርብ መከታተል ለችግሩ የተሻለ የመፍትሄ ሃሳብ ሊሆን እንደሚችል
ተጠቁሟል፡፡ በድርጅቱ የማሽነሪ እና የተሽከርካሪ ኪራይ አገልግሎት ሰጪ ድርጅቶች
/አቅራቢዎች/ ለመወዳደር ሲጋበዙ የድርጅቱን ጥቅም ሊያስጠብቅ በሚችል መልኩ ተወዳ
ዳሪዎች ተገቢውን ነጥቦች እንዲያሟሉ መስፈርቶቹ በግልፅ እንዲቀመጡ የማይደረግበት
ሁኔታ እንዳለ ለመታዘብ ተችሏል፡፡ ይህም የተሟላ የጨረታ መመሪያ፣ የዕቃው
ወይም የአገልግሎት ዝርዝር፣ የዋጋ ሰንጠረዥ፣ የባለቤትነት መታወቂያ /ሊብሬ/፣ አንዳ
ንዶቹን የንግድ ፈቃድም አለመጠየቅ በመኖሩ እና የውል ሁኔታዎች በአግባቡ ተገልፀው
እንዲካተቱ አለመደረጉ በድርጅቱ የታዩ የአሰራር ሥርዓት ችግሮች ናቸው፡፡
76
የኪራይ መሣሪያዎችን ጉዳይ የምህንድስና ክፍሉ ሪፖርት ተጠናቅሮ አለመቅረብ /በተ
በታተነ ሁኔታ መሆን/፣ በሰነዶች ላይ የምዝገባ ስህተት በተደጋጋሚ ስለሚፈፀም ሰነዱ
ዋናው መ/ቤት ተልኮ እንዲታረም ወደ ፕሮጀክት የሚመለስበት ሁኔታ መኖር፣ የፕሮ
ጀክቱ ጽ/ቤት ባለቤታቸው ያልታወቁ የኪራይ መሣሪያዎች ሥራ ላይ አሰማርቶ መሣሪ
ያዎች የሰሩበትን የክፍያ ማስረጃ ለዋናው መ/ቤት መላክ የሚጠቀሱ ችግሮች ናቸው።
77
የኪራይ ማሽነሪ የሥራ ሰዓት፣ የነዳጅ ፍጆታ፣ የጥገና /በዝርዝር እንዲገለፅ በማድረግ/
ወጪን ከማሽኑ የሥራ ሪፖርት ጋር በማገናዘብ በውስጥ ኦዲት እንዲሁም በፕሮጀክት
ኃላፊዎች በኩል ቁጥጥር የሚደረግበትን አሰራር መዘርጋት ተገቢ ነው፡፡
በተመሳሳይ የነዳጅ ማደያ ማሽን ሲበላሽ ወቅታዊ መፍትሄ በመስጠት ትክክለኛ መለኪያ
በመጠቀም የነዳጅ እደላው ሥራ እንዲከናወን መደረግ እንዳለበት ጥናቱ አመልክቷል፡፡
ይህን የአሰራር ሥርዓት ችግር ለመፍታት ለውስጥ ሠራተኞች ጠንካራ የሆነ የሥነም
ግባር ደንብ ማዘጋጀትና ስልጠና በመስጠት ተግባራዊ ማድረግ፣ አከራዮች በሚገቡት
78
ውል መሠረት ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ እና የቅሬታ አቀራረብና አፈታት ሥርዓት
በመዘርጋት ጥፋት አጥፍተው በሚገኙ ሠራተኞችና አከራዮች ላይ ተመጣጣኝና አስተ
ማሪ የሆነ እርምጃ በመውሰድ የቁጥጥር ሥርዓቱን ማጠናከር ይገባል፡፡
79