You are on page 1of 4

የቡታጀራ የአህለሱንና ወልጀመዓ አመታዊ እቅድ እና ዝርዝር ተግባራት።

መግቢያ

እንደሚታወቀው የቡታጅራ አህለል ሱና ወልጀመዓህ በገጠሩም በከተማው በስሩ ከ20 በላይ መሳጂዶች ያሉ
ሲሆን እነዚህን መስጂዶቸ በመጠቀም ካለፉት 2 አስርት አመታት ጀምሮ ከሞላ ጎደል አቅሙን በፈቀደው
ትክክለኛውን የሸሪዓ አስተምህሮ ለማህበረሰቡ ለማድረስ ደፋቀና በማለት ላይ ሆኖ እስከዛሬ ደርሷል።ሆኖም
ጀመዓው እነዚህን መስጂዶች በበቂ ሁኔታ ማገልገል ባይችልም ግን ዛሬ ላይ የምናየውን የሱናው ማህበረሰብ
መብዛት በአላህ ፈቃድ የአቅሙን አስተዋጽኦ ማድረግ ችሏል፡፡ አነዚህን ስራዎች ሲከውን ግን በተለያዩ ችግሮች
የተፈተነና ከችግሮቹም ጋር ግን ስራውን በተለይም በቂርኣትና በዳዕዋው ዘርፍ ላይ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይል አሁንም
ድረስ እየሰራ ይገኛል፡፡

ከዚህ በፊት የሱናው ጀመዓህ ላይ የነበሩና አሁንም ድረስ የቀጠሉ ችግሮችን እንደሚከተለው በ3 ከፍዬ ለማቅረብ
እሞክራለሁ፡-

1. ኢኮኖሚያዊ ችግር
ጀመዓው የአቅም ውስንነት ያለበት መሆኑ ግልጽ ነው ከዚህም አንፃር ማለትም ከመስፋፋት እና
ከተደራሽነት አኳያ የተሰሩ ስራዎች አነስተኛ ናቸው።ማህበረሰቡም ይንን ጀመዓ መደገፊያ ምረኩዝ አድርጎ
ቢቆጥረው እንጂ ጀመዓውን ለማገዝ የሚሆኑ አቅሞች መፈጠር ላይ ብዙ አልተሰራም
ጀማዓውም የማህበረሰቡም ይሁን የራሱ ፍላጎቶች ካላው አቅም አንፃር ተገቢውን ምላሽ የሚሰጥ ሆኖ
አልተገኘም።
አስፈላጊ የሆኑ የጀመዓው ወጪዎች ከተወሰኑ ሰዎች የሚሸፈኑ ቢሆንም ጀመዓው ከመስፋፋቱ አንፃር ዛሬ
ከደረሰበት ፍላጎት እና ተመጣጣኝ አቅም በየትኛውም ሚዛን መጣኝ ስላልሆነ፣ጀመዓው የውስጡም ይሁን
ከማህበረሰቡ ለሚመጡ ችግሮች መፍትሄ የሚሰጥበት ሂደት የደከመ እና አሰልቺ ስለሆነ ጀመዓውን
ሊመጥን እና ሊያሳድግ የሚችል የገቢ አቅም የለውም።
የኡስታዞች ደሞዝ ለመክፈል፤መድረሳዎች ለማስፋፋት፤መስጂዶች ለማስፋፋት፤ያሉትም መስጂዶች
በኢኮኖሚ ለማጠንከር፤ወዘተ መሰል ችግሮች ለመፍታት አለመቻሉ፡፡
2. ማህበራዊ ችግሮች
ማለትም የሱናው እንግዳ ሆኖ መቆጠር ባይተዋርነትና ጭራቅ አርጎ ማህበረሰቡ ዘንድ መሳሉ ሱናን
ለማስተማር እንቅፋት ሆኖ ታይቷል፡፡በተለያየ ጠሪቃ ውስጥ የተዘፈቀ ማህበሰብ መሆኑን የተብሊግን
የሱፍያው ማህበረሰብ ቀድሞ መስፋፋቱና ቦታ መያዙ ይህንን ጀመዓህ በማህበራዊ ጉዳይ አስተዋጽኦ
እንዳይኖረው ተደርጎ ታፍኖ የቀየ መሆኑ፡፡
3. ፖለቲካዊ ተጽዕኖ
ከፌደራል ጀምሮ እስከ ታችኛው የቀበሌ መዋቅር ድረስ ይህን ጀመዓህ የሚጨቁን እንጂ የሚያግዝ አካል
አለመኖሩ፤

ከላይ በ3 ተከፍለው የቀረቡት ችግሮች ዋናዋናዎቹ ቢሆኑም ሌሎች ዝርዝር ችግሮች እንዳሉና እዚህ ውስጥ
እንደሚጠቃለሉ ታሳቢ ተደርጎ እነዚህን ችግሮች በጀመዓው ላይ ቀላል የማይባሉ እንቅፋቶች እንደነበሩ
ለቤቱ ግልጽ ነው፡፡

የቡታጀራ የአህለሱንና ወልጀመዓ አመታዊ እቅድ እና ዝርዝር ተግባራት።


የአጭር ጊዜ እቅድ

እነዚህ ችግሮች ከአሁን በኋላ ከተቻለ ሙሉለሙሉ እንዳይቀጥሉ ካልተቻለም እዲቀንሱ ማድረግ አለብን
ብለን ከእናንተ ጋር የአላህ እርዳታ ከፊታችን አርገን የሚከተሉት የአጭር ጊዜ እቅድ አቅደን ተነስተናል፡፡

እቅዱም ስናቅድ ዋናዋና ጉዳዮችን እንጂ ለዚህ በጣም ለተስፋፋው የሱና ጀማዓህ በቂ እቅድ ነው ብለን
እንደማናስብ ግን እንደ መንደርደሪያ ሁሉም የራሱ እንዲያቅድና እንዲሰራ ያደርጋል፡፡በጊዜያዊነት ጀመዓችን
ላይ በአፋጣኝ ምላሽ የሚሹ ጉዳዩች ናቸው ያልናቸውን በአመታዊ እቅዳችን ፊት ለፊት አርገን አቅርበናል፡፡

ግብ 1. በዳዕዋና ቂርኣት ዘርፍ ቢያንስ ለ10 መስጂዶች ዋና ኡስታዞችን መቅጠር (600,000 ብር


ያስፈልገናል።)

1.1. በከተማው በእጃችን ባሉ መስጅዶች ውስጥ ያሉ ኡስታዞች በአግባቡ እና በሞራል ማህበረሰቡን በእወቀት
የተሻለ ደረጃ ያደርሱት ዘንድ ቢያንስ 10 መስጂዶች ላይ የሚገኙ 10 ኡስታዞችን መቅጠር

ግብ 2. በዳዕዋው ዘርፍ ጠንካራ የሆን ሜምበር ማቋቋምና ዳዕዋውን ተደራሽ ማድረግ (840,000 ብር
ያስፈልገናል።)

2.1 ጠንካራ እና ብርቱ የሆነ የዳዕዋ እና ኢርሻድ ሜምበር ማቋቋም።


2.2 ሁሉ አቀፍ የሆነ የዳዒና የሃጢብ ስልጠና መስጠት
2.3 የ5 ደረሶችን ተቀብሎ በኡስታዝነትና በሀጢብነት ለማብቃት አንዱ በዓመት 40,000 ቢጨርስ ለ10 ተማሪ
400,000 ብር ይጨርሳል።
2.4 በሃገር ውስጥም ይሁን ከሃገር ውጭ በሚመጡ ዱዓቶች እና ኡለሞች ለማህበረሰቡ ወቅታዊ እና አስፈላጊ
ርዕሶች ላይ የሚመክሩበት ሂደቶችን ማመቻቸት።
2.5 የጎዳና ዳዕዋን ጨምሮ የንፅፅርና የክርክር ስልጠናዎች በመስጠት
2.6 ዳዕዋው ተደራሽ ይሆን ዘንድ በማቴሪያል እና በገንዘብ ይደግፋል።
2.7 በከተማው እና ከከተማ ውጪ ሰፊ እና አመታዊ የዳዕዎ ፕሮግራም ማደረግ
2.8 በከተማችን 2 መድረሳዎችን በመከራየት ለተማሪዎች በነፃ ቁርዓን የሚቀሩበት እድል ማመቻቸት።ለዚህም
መድረሳዎች ወርሃዊ ክራይ 12,000 ብር ቢሆን ለ2 ኡስታዞች ደመወዝ 12,000 ብር በድምሩ 240,000 ብር
ያስፈልገናል።
2.9 በአክፍሮት አደጋ ዙሪያ ያሉና ወጥመዱ ላይ የወደቁ ቤተሰቦች እና ተማሪዎች የመታደግ ቢያንስ 200,000 ብር
ያስፈልጋል።

ግብ 3. የእርዳታ ጥሪዎች ምላሽና ሊያግዙ የሚችሉ በጎ አድራጉት ማህበር ማቋቋም። (500,000 ብር


ያስፈልገናል።)

3.1 በጀመዓችን እና አካባቢው ለይ ለሚገጥሙ ችግሮች እና የእርዳታ ጥሪዎች እንደየአስፈላጊነቱ እና


እንደየደረጃው እርዳታ ማድረግ
3.2 ወዲት በሁሉም ዘርፍ ሊያግዙ የሚችሉ በጎ አድራጉት ማህበር አህለልኸይር ማቋቋም።
3.3 ለሃገራዊ ጉዳይን ፤ለመስጂድ እና ለተለያዩ ድንገታዊ ከስተቶች እገዛ ማድረግ

የቡታጀራ የአህለሱንና ወልጀመዓ አመታዊ እቅድ እና ዝርዝር ተግባራት።


የማስፈጸሚያ ስልቶች

1. እቅዱን በተገቢው ሁኔታ አቅዶ ከሚመለከተው አካል ጋር በቂ ግንዛቤ መፍጠርና መተማመን ለዝርዝር
ተግባራት የጊዜ ሰሌዳ ማውጣት
2. በቂ የሆነ የበጀት ምንጭ መፈለግና በአክሽን ፕላን መመራት
3. በበጎ ፈቃደኝነት ስራዎችን የሚሰራ የሰው ሀይል መፈለግና ካልተቻለም እንደ አስፈላጊነቱ ሰው መቅጠር
4. ለዚህ ተግባር በበላይነት የሚመራውና የሚከታተለው መዋቅር ማዘጋጀት
5. ከሌሎች የልምድ ልውውጥ መውሰድና አጋዥ አጋር ሆነው እንዲሰሩ ሁኔታዎችን ማመቻቸት

የክትትልና ግምገማ ሂደቶች

 በየወሩ በየ3 ወሩና በየ6 ወሩ እንዲሁም በየዓመቱ የተሸነሸነ እቅድ ማዘጋጀትና ተግባርን
መከታተል መገምገም ግብረ መልስ መስጠት
 በፋይናንሺልም ሆነ በፊዚካል አፈጻተም ዙርያ ግልጸኝነት መፍጠርና የውጭ ኦዲት የሚደረግበትን
አግባብ መፍጠር

ሊያጋጥሙ የሚችሉ ስጋቶች/ችግሮች

 የሚታሰበውን ያህል ብር ከመሰብሰብ አንጻር ስጋት መኖሩ


 የሰዎች ግንዛቤ በሚፈለገው ልክ እና ጀመዓው በተገነዘበው ልክ ሊሆን እንደማይችል
 የድሮ የጀመዓው ደካማ ጎን እንደሚዛን በመውሰድ ይህን እቅድ ይሳካል ብሎ አለመገመት
 በቂ ጊዜውን ሰጥቶ የሚሰራ አለመገኘት
 የዋጋ ሁኔታ መቀያርና የኑሮ ደረጃ መጨመር በታሰበው በጀት ልክ እንደማይሆን
 በቂ የሆነ ኡስታዝ ላይገኝ ይችላል፡፡

የቡታጀራ የአህለሱንና ወልጀመዓ አመታዊ እቅድ እና ዝርዝር ተግባራት።

You might also like