You are on page 1of 30

ማስታወሻ

ለ፡ ኅብረት ሥራ ማህበራት ማደራጃና ማስፋፊ ዘርፍ ም/ኮሚሽነር፣

ለ፡ ስትራቴጅክ ጉዳዮች ሥራ አስፈጻሚ፣

ከ፡ ፋይናንስ ኅብረት ሥራ ልማት መሪ ሥራ አስፈጻሚ፣

ቀን 26/04/2016 ዓ.ም

የኢ.ኅ.ሥ.ኮ

ጉዳዩ፡ የ 2016 በጀት ዓመት የሁለተኛ ሩብ ዓመት ሪፖርት መላክን ይመለከታል፡፡

በፋይናንስ ኅብረት ሥራ ልማት መሪ ሥራ አስፈጻሚ የ 2016 በጀት ዓመት የሁለተኛ ሩብ ዓመት ዕቅድ
አፈጻጸም -----ገጽ ሪፖርት ከዚህ ማስታወሻ ጋር አያይዘን ያቀረብን መሆናችንን እንገልጻለን፡፡

ከሠላምታ ጋር!!

እንዲያውቁት፡-

 ለኮሚሽነር ጽ/ቤት፣

የኢ.ኅ.ሥ.ኮ
የፋይናንስ ኅብረት ሥራ ልማት ዳይሬክቶሬት

የ 2016 ዓ.ም የሁለተኛ ሩብ ዓመት ዕቅድ ክንውን ሪፖርት

ታህሳሰ 2016 ዓ.ም


የኢ.ኅ.ሥ.ኮ
1. መግቢያ.............................................................................................................................................................1
2. የፋይናንስ ኅብረት ሥራ ልማት መሪ ሥራ አስፈጻሚ ዓላማ....................................................................................1
3. የዝግጅት ምዕራፍ.................................................................................................................................................2
3.1. የ 2016 በጀት ዓመት ዕቅድ ዝግጅት.............................................................................................................2

3.2. ኦሬንቴሽን................................................................................................................................................2
4. የትግበራ ምዕራፍ...............................................................................................................................................2
4.1. የፕሮግራም በጀት ዕቅድ ክንውን..................................................................................................................2

4.2. ዝርዝር ዓላማ፡-.......................................................................................................................................14

4.3. በዝግጅት ምዕራፍ የተከናወኑ ተግባራት፡-...................................................................................................15

4.2. በፕሮግራሞች እና ፕሮጀክት የተከናውኑ ተግባራት፡-....................................................................................21


5. ከሌሎች ተቋማት ጋር በቅንጅት የተሰሩ ተግባራት፡-.............................................................................................23
6. የበጀት ዓመቱ ጠንካራ ጎኖች፣ ያጋጠሙ ችግሮችና የተወሰደ መፍትሄ.....................................................................23
6.1. የታዩ ጠንካራ ጎኖች..................................................................................................................................23

6.2. ያጋጠሙ ችግሮች....................................................................................................................................24

6.3. የተወሰደ መፍትሄ.....................................................................................................................................24

i
1. መግቢያ

በገጠርና በከተማ ለሚኖረው የኅብረተሰብ ክፍል ሌሎች በተለይም የፋይናንስ ተቋማት የማይሸፍኑትንና የማያቀርቡትን የፋይናንስ
አገልግሎት የፋይናንስ የኅብረት ሥራ ማህበራት አገልግሎቱን ተደራሽ በማድረግና ቀልጣፋ የፋይናንስ ስርዓት በገጠርና በከተማ እንዲስፋፋ
በማድረግ ረገድ የማይተካ ሚና አላቸው፡፡ አባላትንና ሌላውን የህብረተሰብ ክፍል ከተለያዩ የፋይናንስ ተቋማትጋር አገናኝ ሰንሰለት ሆነው
እያገለገሉ በመሆኑ የራሳቸውን የፋይናንስ አሠራርና አቅም ማጎልበት አማራጭ የሌለው ጉዳይ እንደሆነ ይታመናል፡፡

ይህንንም በቀጣይ አጠናክሮ ለማስቀጠል የፋይናንስ ኅብረትሥራ ልማት ዳይሬክቶሬትም በበጀት ዓመቱ ዕቅድ አቅዶ ወደ ሥራ ሲገባ
የየራሳቸው ዋና ዋና ተግባርና ዝርዝር ተግባራት ያሏቸው 14 ግቦችንና ከእነዚህ ግቦችም የሚጠበቁው ጤቶችን አስቀምጧል፡፡

በመደበኛው ፕሮግራም የሚከናወኑ ተግባራትን በተጨማሪ በተመረጡ ክልሎችና ወረዳዎች ሠፊ ዕገዛና ድጋፍ የሚያደርጉት የአነስተኛ
የገጠር ፋይናንስ ተቋማት ማስፋፊያ ፕሮግራም፣ በልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮግራም የቤተሰብ ኑሮ ማሻሻያ እና ቆላማ አከባቢ የኑሮ ማሻሻያ
ፕሮጀክት (LLRP) የሚከናወኑ ተግባራትም በዕቅድ ተይዘው ወደ ሥራ የተገባ ሲሆን በአጠቃላይ በፋይናንስ ኅብረት ሥራ ልማት የ 2016
ዓ.ም የሁለተኛ ሩብ ዓመት ዕቅድ ክንውን አፈፃፀምን ተዘጋጅቶ እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡

2. የፋይናንስ ኅብረት ሥራ ልማት መሪ ሥራ አስፈጻሚ ዓላማ

የፋይናንስ አገልግሎትና ስርዓቱን በማሻሻል፣ በማጠናከርና ተደራሽ እንዲሆን ለማድረግ የፋይናንስ ኅብረት ሥራ ማህበራትን አቅም
ማጎልበት ዋናው ዓላማ ሲሆን፣
 የፋይናንስ ኅብረት ሥራ ማህበራትን በማደራጀት ለአባላቱ የፋይናንስ አገልግሎትን ተደራሽ ማድረግ፤

 የፋይናንስ ኅብረት ሥራ ማህበራት በውስጥ አሰራራቸው፣ በቁሳቁስና በገንዘብ አቅማቸው የተጠናከሩ እንዲሆኑ ማድረግ፤

 የፋይናንስ ኅብረት ሥራ ማህበራትን እርስ በእርሳቸውና ከሌሎች የኅብረት ሥራ ማህበራት ጋር በፋይናንስ ግብይት በማስተሳሰር
የፋይናንስ አገልግሎቶችን እንዲያገኙ ማድረግ፤
 የአነስተኛ ገጠር ፋይናንስ ተቋማት ማስፋፊያ ፕሮግራም የተግባር አፈፃፀምን መከታተል፣ መገምገምና ማቅረብ፤

 የፋይናንስ ኅብረት ሥራ ልማት መሪ ሥራ አስፈጻሚ ሥራዎችን በማስተባበር፣ በመደገፍና የንዑስ ፕሮግራም ውጤቶችን በማሳካት
የተቋሙን ተልዕኮ መፈፀም ነው፡፡

3. የዝግጅት ምዕራፍ

3.1. የ 2016 በጀት ዓመት ዕቅድ ዝግጅት

 በመሪ ሥራ አስፈጻሚው በፕሮግራም በጀት፣ በፕሮግራሞችና ፕሮጀክት እንድሁም እንደሴክቴር በ 2015


ዓ.ም የተከናወኑ ተግባራት አፈጻጸም ሪፖርት ተዘጋጅቶ ለምመለከተው አካል በወቅቱ ቀርቧል፣
 በመሪ ሥራ አስፈጻሚው ስር የሚገኙ የዴስክ ኃላፊዎች እና ፈጻሚዎች በዕቅድ አስተዋወቁ ላይ የጋራ
አቅጣጫ በመያዝ የ 2015 ዓ.ም በጀት ዓመት አፈጻፀም ስኬቶችና ተግዳሮቶችን በመገምገም ለሥራ

1
አስፈጻሚ ከተሰጠው ተልዕኮ አኳያ በመቃኘት ሊከናወኑ የሚገባቸው ሥራዎች ተቃኝተው የ 2016 ዓ.ም
በጀት ዓመት ዕቅድ ተዘጋጅቶ እንዲፀድቅ ተደርጓል፡፡
 የታቀደውን ዕቅድ የተግባራቱን ነባራዊ ሁኔታ በማያት ለዴስኮች ሸንሽኖ የማስጠት እና የመፈራረም ሥራ
ተከናውኗል፡፡
 በፌደራልና በክልል ያሉትን የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብርት ሥራ ማህበራትን ለማጠናከር የመስክ ፣ የስልጠና
እና የወርክ ሾፕ እቅዶች ተለይተው ታቀወዷል፣

3.2. ኦሬንቴሽን

 የፋይናንስ ኅብረት ሥራ ልማት ዳይሬክቶሬት የ 2016 በጀት ዓመት ዕቅድ ተዘጋጅቶ በበላይ አመራሩ
ከተገመገመ በኋላ ባለሙያዎች እንዲመለከተውና የጋራ እንዲያደርገው ኦሬንቴሽን ተሰጥቶበታል፡፡

4. የትግበራ ምዕራፍ

4.1. የፕሮግራም በጀት ዕቅድ ክንውን

ግብ 1፡- የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራት አደረጃጀትን ማሻሻል ማዘመን

ተግባር 1፡ በፌደራል ለተደራጁ 4 የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅ/ሥ/ማህበራትን ማጠናከር እና ድጋፋዊ ክትትል ለማድረግ ታቅዶ 3ቱን (75%)
ማጠናከር ተችሏል፡፡
ተግባር 2፡ በክልል ለተደራጁ 116 የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅ/ሥ/ማህበራትን ማጠናከር እና ለአደራጅ ተቋሙ ሙያዊ ድጋፍ ለማስጠት ታቅዶ
40 (111 %) የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራትን ማጠናከር ተችሏል፡፡
የማጠናከር ዓላማ፡-

የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብርት ስራ ማህበራትን፤ በአደረጃጀትና ምዝገባ፤ በአስተዳደር እና አመራር፤በአሰራር ሥርዓት

ዝርጋታ፤ በተግባሮቻቸው እና በአሰራር ግንኙነታቸው በአካል በመገኘት ያሉባቸውን ክፍተቶች ለይቶ ድጋፍና ክትትል

በማድረግ ሙያዊ ክፍተት ለመሙላት፣

የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብርት ስራ ማህበራት አገልግሎታቸውን በማስፋፋት እና ተደራሽ በማድረግ ወጥነት ያለው አሰራር

በመከተል ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ለማስቻል፤

ድጋፍና የማጠናከር ተግበር የተደረገላቸው አካላት፡-

ክልል/ከተማ ዞን/ክፈለ-ከተማ ወረዳ መሠረታዊ የገ/ቁ/ብ/ኅ/ሥራ ምርመራ


አስተዳደር ማህበራት

አዲስ አበባ 11 18 22

አፋር 4 7

2
ሱማሌ 4

ጋምቤላ 1 4

3 በፌዴራል የተመዘገቡ

ድምር 40

የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራት የታዩ ጠንካራ ጎኖች፡-


 የገ/ቁ/ብ/ኅ/ስ/ማህበራት የብድር ምጫቸው የአባላት ቁጠባ በመሆኑ የአባላትን የነፍስ ወከፍ ቁጠባን ለማሳደግ በተጨማሪ
አዳዲስ አባላትን የማስገባት እየሰሩት ያለ ስራ አበረታች መሆኑ
 ከብድር የተረፈውን ብር የተሸለ ገቢ እንዲያስገኝ በፋይናንስ ትስስር አማካኝነት ከፋይናንስ ተቋማት ጋር ትስስር ማድረጋቸው
(በጊዜ ገደብ ቁጠባ ማስቀመጣቸው)
 አባላት የባለቤትነት ስሜት እንዲኖራቸው ያላቸውን ሂሳብ በኦን ላይን / በዳታ ቤዝ እንዲከታተሉት
መደረጉ(የፌ/ፍ/ቤ/ሠ/የገ/ቁ/ብ/ኅ/ሥ/ማህበር)
 ምቹ የሆነ ጽ/ቤት እና በተሟላ የሰው ሀይል እየተመሩ ያሉት የተወሰኑ ኅብረት ስራ ማህበራት የተሸለ ስራ እየሰሩ መሆንቻው
(አዋጭ፣ አሚጎስና አዲሲቷ ኢትዮጵያ)፣
 PEARLS ratio professionally እየተመራ መሆኑና የሂሳብ አያያዙ ጤናማ መሆኑ፤(በተለይ አዋጭና አሚጎስ)፣
 ቴክኖሎጂን መጠቀማቸው እና የሞባይል አፕሊኬሽን በሙከራ ላይ መገኘቱ፣(በተለይ አዋጭና አሚጎስ)፣
 ብድር የሚውስዱ አባላት ገቢ በሚያስገኙ ተግባራት ላይ ትኩረት አድርገው እንዲሰሩ መደረጉ
 ሴቶችን ለማበረታታት ከሌሎች አባላት በ 0.5 በመቶ የወለድ ቅናሽ መቅረቡ (አዋጭና አሚጎስ)፣
 ዘመኑ በደረሰብት ጋር አብሮ ለመዘመን ኮር ባንኪን አገልግሎት መሰጠቱ (አዋጭ)፣
 ከመደበኛ ቁጠባ በተጨማሪ ሌሎች የፋይናንስ አገልግሎቶች ተደራሽ መደረጋቸው (አዋጭ፤ አሚጎስ)፣
 ሂሳባቸው በዘመናዊ በቴክኖሎጅ የታገዘ መሆኑ (ቲመኒየስ)
 በአመራርነት እስከ 50 በመቶ ሴቶች መታቀፋቸው (የወረዳ 02 ነዋሪዎች)
የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራት የታዩ ደካማ ጎን፡-
 አብዛኛው የኅብረት ሥራ ማሀበሩ ሥም በማህተሙና በሰርተፍኬቱ ላይ ያለው ስም ተመሳሳይ አለመሆን
 የእጣ የግንባር ዋጋ መሻሻሉ(የፌ/ፍ/ቤ/ሠ/የገ/ቁ/ብ/ኅ/ሥ/ማህበር)
 መስሪያ ቦታ የሌላቸው መሆኑ(የፌ/ፍ/ቤ/ሠ/የገ/ቁ/ብ/ኅ/ሥ/ማህበር)
 አብዛኛው የኅብረት ሥራ ማሀበር ከስራ ክልል ውጭ አባላት ማፍራታቸው
 አብዛኛው የኅብረት ሥራ ማሀበር ቅጥር ሰራተኛ ቀጥረው የማያሰሩ መሆኑ
 አብዛኛው የኅብረት ሥራ ማሀበር እጣና ቁጠባ ምጥጥን ተግባራዊ አለመደረጉ፣
 ተጨማሪ የፋይናንስ አገልግሎት ለማስፋፋት የተደረገው ጥረት አናሳ መሆኑ (መ/ያልሆነ ቁጠባ፣ የመድህን ዋስትና፣----)
 የአብዛኛው ኅብረት ሥራ ማሀበር ሂሳብ በወቅቱ የማይዘጋ መሆኑ

3
 አመራር ሲቀያየር ርክክብ አለመደረጉ (የፌ/ፍ/ቤ/ሠ/የገ/ቁ/ብ/ኅ/ሥ/ማህበር)
 ለአባላት የሚሰጠው ብድር ተጨማሪ ገቢ ማስገኛ ላይ ትኩረት ስላልተደረገ አባላት ብድር መመልስ ሳይችሉ ሲቀሩ ያላቸውን
ቁጠባና እጣ አቻችለው መውጣት አዝማሚያ መኖሩ (የፌ/ፍ/ቤ/ሠ/ የገ/ቁ/ብ/ኅ/ሥ/ማህበር)፣
 አደራጅ መስሪያ ቤቱ በእውቀት ላይ የተመሰረተ ድጋፍ አለማድረግ
 የአብዛኛው ኅብረት ሥራ ማሀበር የአባላትን የብድር ፍላጎት ለሟሟላት የብድር አቅርቦት ችግር መኖሩ
 የፍይናስ ችግርን ለመቅረፍ ከአቻ ኅብረት ስራ ማህበራት ሆነ ከአበዳሪ ተቋማት ትስስር አለመፍጠር
 በጥናት ላይ ያልተመሰረተ የአርቦን መጠን ማሰባሰብ እና ጊዜው ያለፈበትን አርቦን ለይቶ አለማስቀመጥ (ከአዋጭ በስተቀር)
በተለያ አሚጎስ 2-3፣ የወረዳ 11 ቀበሌ 14 ነዋሪዎች የገ/ቁ/ብ/ኅ.የተ/ኅ/ሥ/ማህበር 4.2 በመቶ የህይወት መድህን አርቦን
ማስከፈል፣
 1 ጽ/ቤት ለ 3 ኅብረት ሥራ ማህበራት በጋራ የሚጠቀሙ መሆኑ(አቦ የሴቶች እድር ገ/ቁ/ብ/ኅ/ሥ/ማህበር)
 ዓመታዊ ዕቅድ የማያዘጋጁ ሆኑ(አቦ የሴቶች እድር ገ/ቁ/ብ/ኅ/ሥ/ማህበር
 የአባላት ቁጥር 896 /2014 አደረጃጀት መመሪያ ላይ ከተቀመጠው በታች የአባላት ቁጥር ያላቸው መሆኑ
 አነስተኛ የብድር መድን ዋስትና አተገባበር ከወጣው መመሪያ ውጪ ሁሉም አባል 10 ብር ከራሳቸው አውጥተው እንዲከፍሉ
መደረጋቸው
 የኅብረት ሥራ ማህበሩ አመራር አደራጅ መ/ቤቱ በሚያዘጋጀው ስልጠና ላይ የመሳተፍ ፍላጎት የሌለው መሆኑ በተጨማሪም
የተወሰነው ብድር ወለድ ምጣኔ (6.25%) ከቁጠባ መለድ (7%) ያነሰ መሆኑ (አቦ የሴቶች እድር ገ/ቁ/ብ/ኅ/ሥ/ማህበር)
 የአባላት ገንዘብ በነባር አመራርና በባለሙያዎች ሲመዘበር ክትትል አለመደረጉ (አዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት የገ/ቁጠባና ብድር
ኅብረት ሥራ ማህበር)
 አብዛኛው ኅብረት ስራ ማህበራት ላይ ከወለድ ምጣና በተጨማር 1 በመቶ የአገልግሎት ክፍያ ማስከፈል (በተለይ አሚጎስ 4
በመቶ የአገልግሎት ወጪ ማስከፈል)
 አመራሮች ሳይመረጡ ከሁለት ምርጫ ዘመን በላይ በአመራርነት መቆየታቸው(ሲቪል ሰርቪስ፣ አለርት. ወዘተ)
 የተወሰኑ ኅ/ስ/መህበራት ከተቋቋሙለት አላማ ውጭ በሌሎች የካፌ አገልግሎት ስራ ላይ መሰማራታቸው(አለርት)
 አብዛኛው ኅብረት ስራ ማህበራት ከዝቅጠኛ መደበኛ ቁጠባን በላይ አባላት ሲቆጥቡ መደ/ባልሆ ቁጠባ ማስቀመጥ (ከ 200-
300 ብሎም ማስቀመጥብዙሃን የ/ገ/ቁ/ብ/ኅ/ሥ/ማህበር)
 ሁሉም ኅ/ስ/ማህበራት የውክልና ድምጽ አሰጣጥን ተግባራዊ ለማድረግ ስራ አለመጀመራቸው
 አብዛኛው ኅብረት ስራ ማህበራት ጊዜውን ጠብቆ ጠቅላላ ጉባኤ አለማድረግ
 አብዛኛው ኅብረት ስራ ማህበራት በየሶስት አመቱ ዕድሳት አለማድረጋቸው
 አብዛኛው ኅብረት ስራ ማህበራት ወቅቱን የጠበቀ የኦዲት ሪፖርት አለማድረግ
 የፋይናንስ አቅርቦት እያለ ለአባላት የብድር ሥርጭት ተደራሽ አለማድረግ(የተባበሩት የሸማ ነጋዴዎች የገ/ቁ/ብ/ኅብረት ሥራ
ማህበራት
 በኅብረት ስራ ማኅበራት አዋጁ ቁጥር 985/2009 አንቀጽ 32 ንዑስ አንቀጽ 3 መሰረት እንደ ስራ አመራርና ቁጥጥር ኮሚቴ
ሁሉ ሌሎች ንዑሳን ኮሚቴዎችም በጠቅላላ ጉባኤ እንደሚመረጡ በሁልም ኅ/ስ/ማህበራት ዘንድ ግንዛቤ አለመኖር፤

4
 ወለድ አልባ ፋይናንስ አገልግሎት ላይ ለው ግንዛቤ በሚፈለገው ደረጃ ማደግ አለመቻል በተለይም ከቀርድሃሰን በስተቀር
ለሌች አገልግሎቶች መስጠት አለመቻል (አፋርና ሱማሌ)፣
 ሕጋዊ ሰውነት እና መተዳደሪያ ደንብ ሳይኖራቸው የሚሰሩ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራት መኖራቸው
(ጋምቤላ ክልል)፣
 ለብድር ወለድ አከፋፈል አሰራርን የተከተለ አለመሆን እና የሚያስከፍሉ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራት
መኖራቸው ለ 10000 ብር 15000 ብር (50 ከመቶ) (ጋምቤላ ክልል)፣

በአደራጅ መስሪያ ቤቶች የተለዩ ድክመቶች፡-


 አደራጅ መስሪያ ቤቱ ኅብረት ስራ ማህበራት ጠቅላላ ጉባኤ እንዲያካሄዱ ክትትል ባለማድረጉ ምክንያት የአመራር አካላት
ጊዜአቸውን የጨረሱ መሆናቸውና አለመተካታቸው፣
 በኅብረት ስራ ማህበራት አዋጅ 985/2009 መሰረት መተዳደሪያ ደንባቸውን አለመሻሻል ማለትም አዋጅ 147/91 እየተጠቀሙ
ያሉ ኅ/ስ/ማህበራት መኖራቸው፣
 ከአደራጅ መስሪያ ቤቱ ክትትል ማነስ ምክንያት በአብዛኛው ኅ/ስ/ማህበራት የብድር ወለድ ምጣኔ ሳይንሳዊ ሳይሆን ከሌሎች
ኅብረት ስራ ማህበራት፣ ከባንክ፣ ከማይክሮ ፋይናንስ ጋር በማነጻጸር እንጂ የራሳቸውን መነሻ አለማሳቀመጥ ማለትም ለብድር
የሚውለው ገንዘብ ያለው/የሚያስከትለው ዋጋ/ወጪ፣ ብድሩን ለማስፈጸም የሚደረግ አስተዳዳራዊ ወጪ፣ መገኘት ያለበት
ትርፍ፣ የማይመለስ ብድር መሸፈኛ ብለው አለመከፋፈል፣ በዚህም ምክንያት ተጨማሪ የብድር አግልግሎት ክፍያ ማስከፈል፣
 የገ/ቁ/ብ/ኅ/ስራ ማህበራት ባንክ አገልግሎት የሚሰጡ ፋይናንስ ተቋማት መሆናቸውን ባለመገንዘብ በገ/ቁ/ብ/ኅ/ስራ ማህበራትና
በሴክተሩ ባለሙያዎች የገ/ቁ/ብ/ኅ/ስራ ማህበራት የሚሰጡትን አገልግሎት ከማስፋት ይልቅ ወደ ባንክና ማይክሮ ፋይናንስ
ይቀየራሉ የሚል አስተሳሰብ መያዙ፣
 አብዛኛው ኅብረት ስራ ማህበራት ቁጠባን እና ለሁሉም አባል ብድር ሳያመቻቹ የብድር ተሳትፎን ለትርፍ ክፍፍል ድልድል
አሰራር ሲጠቀሙ ይባስ ብሎም እስከ ዛሬ በተሰበሰበው ቁጠባ እና እጣን ብድር በመስጠት የተገኘውን ትርፍ በበጀት ዓመቱ
ብቻ ለተቆጠበ ብር ብቻ ድልድሉን ለመስራት ማሰብ
 ከአዋጭ፣ ከአሚጎስ እና ከአዲሲቷ ኢትዮጵያ የገ/ቁ/ብ/ኅ/ስራ ማህበራት ውጪ ያሉት ሌሎች ኅ/ስራ ማህበራት የእጣና የቁጠባ
ምጥጥን ተግባራዊ ሳያደርጉ ሲቀሩ ድጋፍ አለማድረግ
 ለኅ/ስ/ማህበራት ሂሳባቸውን በየወሩ እንዲዘጉ ተገቢውን ክትትልና ድጋፍ አለማድረግ
 የገ/ቁ/ብ/ኅ/ስራ ማህበራት የፋይናንስ ተቋማት እንደመሆናቸው በተማረ የሰው ሀይል አለመመራታቸው
 ከግንዛቤ ማነስ የተነሳ ዝቅተኛ የመደበኛ ቁጠባ ከተቀመጠው በላይ ለሚቆጥቡ አባላት ወደ መደበኛ ያልሆነ ቁጠባ መያዝ
 የፋይናንስ ትስስር የግንዛቤ ችግር በመኖሩ የኅ/ስ/ማህበራት ላይ አንዳንድ ኅ/ስ/ማህበራት ላይ ከፍተኛ ገንዘብ ክምችት መገኘት
 የገ/ቁ/ብ/ኅ/ስራ ማህበራት ከልዩ ስሙ ቀጥሎ ኃ.የተ የሚለውን ቃል አለመጠቀም እንዲሁም አብዛኛው ኅብረት ሥራ ማህበር
የሰርተፊኬት (ህጋዊ ሰውነት) እና ማህተሙ ስም ተመሳሳይ አለመሆን
 በኅብረት ስራ ማኅበራት አዋጁ ቁጥር 985/2009 አንቀጽ 32 ንዑስ አንቀጽ 3 መሰረት እንደ ስራ አመራርና ቁጥጥር ኮሚቴ
ሁሉ ሌሎች ንዑሳን ኮሚቴዎችም በጠቅላላ ጉባኤ እንደሚመረጡ ግንዛቤ አለመኖር፤

5
 የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ መምህራንና ሰራተኞች የገ/ቁ/ብ/ኅ/ሥ/ማህበር የኦዲት አገልግሎትና ሌሎች ድጋፎች
እንዲደረግለት በተደጋጋሚ ቢጠየቅም ምላሽ አለማግኘት( የ 4 አመት ኦዲት አለመደረግ፣በተሻሻለው አዲሱ አዋጅ
አለመተግበሩ)
 ከኅብረት ሥራ ማህበራት አዋጅ 985/2009 እና አስፈላጊ የሆኑ የተለያዩ መመሪያዎች ከአደራጅ መስሪያ ቤቶች ለኅብረት ሥራ
ማህበራት በማውረድ መተግበር አለመቻሉ (ለምሳሌ የሰው ሀብት መመሪያዎች ሳይኖር ቅጥር መቅጠር እና የፋይናንስ መመሪያ
አለመኖር)
 ሌሎች የፋይናንስ አገልግሎት አማራጮችን በግንዛቤ ማነስ የተነሳ ማስፋት አለመቻል(መ/ያልሆነ ቁጠባ፣የመድን
ዋስትና፣የወለድ አልባ …)፣
 የገ/ቁ/ብ/ኅ/ስራ ማህበራት ከተሰማሩበት የስራ መስክ ውጪ ተሰማርቶ መገኘት (ምሳሌ ክበብ ማቋቋም፣የቤት ኪራይ
መስጠት፣የሻውር አገልግሎት)፣

ትኩረት ተሰጥቶ ሊሰሩ የሚገቡ ጉዳዮች፡-


 የገ/ቁ/ብ/ኅ/ስራ ማህበራት የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ እንዲያገኙ ድጋፍና ክትትል መደረግ አለበት፣
 አቻ ከሆኑ ኅብረት ሥራ ማህበራት ፣ኅብረት ሥራ ዩኒዮኖች፣ መንግስታዊ የሆኑና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች እና ሌሎች
የፋይናንስ ተቋማት ጋር ትስስር እንዲያደርጉ ትኩረት ተሰጥቶ መሰራት አለበት፣
 በየደረጃው ላሉ ለማስፋፊያ አካላት፣ ለኅብረት ሥራ ማህበራት አመራር እና ለቅጥር ሰራተኞች የአቅም ግንባታ ሥልጠና
ማግኘት አለባቸው፣
 የተጠናከረ ኅብረት ሥራ ማህበር መፍጠር እንዲቻል የተለያዩ የማጠናከሪያ ስልቶችን መተግበር አለባቸው (የአባላት ቁጥር
ማሳደግ፣ የቁጠባ መጠን ማሳደግ፣የካታል መጠን፣ሌሎች የፋይናንስ አገልግሎቶችን ማስፋት፣ ማዋሀድ….)
 በከተማ አስተዳደር ደረጃ ለኅብረት ሥራ ማኅበራቱ የሚደረገዉ የክትትልና ድጋፍ አግባብ እንዲሻሻል በክልሉ የሚገኙ
የኅ/ሥራ ማኅበራትን የሥራ እንቅስቃሴን መሠረት በማድረግ፡ ከፍተኛ፣ መካከለኛ እና ዝቅተኛ ደረጃ ላይ የሚገኙትን
በመለየት፡ በከተማ አስተዳደሩ የኅብረት ሥራ ኤጀንሲ፣ በክፍለ ከተማ እና ወረዳ አደረጃጀት ስር ክትትል እና ድጋፍ
እንዲያገኙ ማድረግ፣
 በኢትዮጵያ ኅብረት ሥራ ኮሚሽን በኩል የሚደረገውን የክትትልና ድጋፍ አግባብ በማጠናከር የእንቅስቃሴውን በቀጣይነት
ማጠናከር፣
 የኅ/ሥራ ማኅበራት ከአባላት ቁጠባ ከማሰባሰብ ባሻገር የብድር ስርጭት መጠንን ማሳደግና የብድር ስርጭቱና አመላለስ
ጤናማ እንዲሆን ልዩ ትኩረት መስጠት፣
 የብድር ወለድ ምጣኔ ማስያነት የተጠቀምነውን የማይመለስ ብድር መሸፈኛ በመተዳደሪያ ደንብ ውስጥ ጸድቆ ኅ/ስ/ማህበሩ
ካተረፈው ትርፍ 70% ውስጥ ቀንሶ ለማይመለስ ብድር መጠባበቂያነት መያዝ ቢችል፣
 ጋምቤላ ክልል ውስጥ የሚገኙ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራት እንደገና ተፈትሾ መደራጀት እንደለባቸው
ከክልሉ ጋር መግባባት ላይ የተደረሰ በመሆኑ ድጋፍ እንደምያስፈልገው፣

6
ተግባር 3፡ በፌደራል ደረጃ በተመዘገቡት 4 የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራት በበጀት ዓመቱ 40,000 (ሴት 20,000)፣
በዚህ ሩብ ዓመት 10,000፣ እስኪህ ሩብ ዓመት 18,000 አዳዲስ አባላት ለማፍራት ታቅዶ በዚህ ሩብ ዓመት የተከናወነ
11,010 (ሴት 3,242) ሲሆን እስከዚህ ሩብ ዓመቱ 16,815 (ሴት 5,595) የእቅዱን 93% ማፍራት ተችሏል፡፡
ግብ 2፡ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራትን አገልግሎት
ተግባር 1፡- በሚሰጡትን አገልግሎት ላይ ለአባላት ግንዛቤ እንዲፈጥሩ ለ4 የገንዘብ ቁጠባና ብድር የኅብረት ስራ ማህበራት ክትትልና ድጋፍ
ለማድረግ ታቅዶ ለ3ቱ (75ከመቶ) መስጠት ተችሏል፣
ግብ 3፡- የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራትን አመራር ስርዓት ማሻሻል፣
ተግባር 1፡- በሥራ አመራራቸው ውስጥ የአማካሪ ባለሙያዎችን እንዲያካትቱ ለ 2 በፌዴራል ደረጃ ለተደራጁ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ

ማህበራት ድጋፍና ክትትል ለማድረግ ታቅዶ ለ 2 ቱም (ለአዋጭና በላይ አብ) ተሰጥቷል፣

ተግባር 2፡- ጠቅላላ ጉባዔአቸውን በውክልና አሰራር እንዲመሩ ለ 2 የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራት ድጋፍና ክትትል ለማድረግ ታቅዶ

ለ 2 ቱም (ለአዋጭና በላይ አብ) ተሰጥቷል፣

ግብ 4፡- በሪፎርም የትግበራ አሰራር የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራትን ማደራጀት
ተግባር 2፡ በሚቀርበው የመደራጀት ጥያቄ መሠረት በፌዴራል ደረጃ በዓመቱ 3 በሩብ ዓመቱ 1 አዳዲስ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ
ማህበር ለማደራጀት የታቀደ ሲሆን
 በተለያዩ ክልሎች የተደራጁ 13 ከፍታ የወጣቶች መሠረታዊ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበር ተዋህደን በፌደራል
የእንደራጅ የሚል ጥያቄ ለሥራ አስፈጻሚው ቀርቧል፣
 በዚህ መሠረት የባለሙያ ቡድን በማደራጀት ጥያቄውን በመፈተሽ የውሳኔ ሃሳብ እንዲያቀርቡ በተደረገው መሰረት ጥናት በማድረግ
የውሳኔ ሃሳብ ያቀረቡ ሲሆን የውሳኔ ሃሳብ ከተሰጠበት በኋላ ቀጣይ ሂደቱ የሚቀጥል ይሆናል፡

ግብ 5፡ የኅብረት ሥራ ማስፋፊያ አካላት እና የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራትን የማስፈፀም እና የመፈፀም
አቅም ማሳደግ

ተግባር 4፡- የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማኅበራት እንዲጠቀሙበት የተዘጋጀውን ሶፍት-ዌር ጥቅም ላይ እንዲውል ለ 50
የገ/ቁ/ብ/ኅ/ሥ/ማኅበራት ሁለት ዙር ሥልጠና መስጠት የተያዘ ሲሆን በታቀደው መሠረት ስልጠናው ተሰጥቷል፡፡

በመጀመሪያው ዙር ስልጠና፡-
 የስልጠናው ተሳታፊዎች የኮሚሽኑ የፋይናንስ ኅብረት ሥራ ልማት መሪ ሥራ አስፈፃሚ 12 ባለሙያዎች፣ ከኢንፎርሜሽን
ኮሚኒኬሽን ሥራ አስፈጻሚ 2 ባለሙያዎች እንዲሁም የወልታኔ አምቦ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ዩኒዬን 1 ባለሙያ
ተሳትፈዋል፡፡
የስልጠናው ህደት፡-
 ስልጠናው የተሰጠው የተሸሻለው ሶፍት ዌር ከሶፍትዌር አበልጻጊው ድርጅት እንድመጣ ተደርጓል፣
 የተሸሻለው ሶፍትዌር አንድ በአንድ በመፈተሸ ያሉ እንድስተካከል የተሰጡ አስተያየቶች መስተካከላቸውን በተግባር የማረጋገጥ ሥራ
ተሰርቷል፣
 ሁሉም ተሳታፉ የተሸሻለውን ሶፍትዌር በኮምፒዩተሩ ላይ እንዲቻን በማድረግ ስልጠናውን እንድያገኝ ተደርጓል፡
በሁለተኛው ዙር ስልጠና፡-

7
 የስልጠናው ተሳታዎች ከ40 የገ/ቁ/ብ/ ኅ/ሥራ ማህበራት ሥራ አስኪያጆችና የሕሳብ ሰራተኞች እና 4 የክልል

የፋይናንስ ኅብረት ሥራ ልማት የተውጣጡ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ባለሙያዎች እና የIT ባለሙያዎች

ናቸው፡፡

ስልጠናው የተሰጠበት ህደት፡-

 ቶሎ ወደሥራ ልገቡ የሚችሉ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራት ከክልሎች ጋር በመሆን ተለይቷል፣

 ስልጠናውን የሚሰጡ አካላት ቀድሞ እንዲዘጋጁ ተደርጓል፣

 ስልጠናው የተሸሻለው ሶፍ ዌር ሲሞከርባቸው የነበሩ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራት ዩኒዬኖች

መካከል ወልታኔ አምቦ ዩኒዬን በ acural base accounting system እና ጃቢ ዩኒዬን cash base accounting system

የተሞከረባቸው ባለሙያዎች እንድሁም ከኮሚሽናችል የIT ዴስክ እዲሰጥ ተደርጓል፤

 ስልጠናው የተግባር ስልጠና እንድሆን ለማድረግ ሁሉም ተሳታፊዎች የራሳቸውን የሕሳብ ቋት ይዞ እንዲመጡ

በማድረግ እና ሁሉም ኮምፕዩተር ይዞ እንድመጡ በማድረግ በተግበር የተደረፈ ስልጠና እንድሰጥ ተደርጓል፡፡

የስልጠናው ውጤቶች፡-
 ተሳታፊ ባለሙያዎች በተሸሸለው ሶፍት ዌር ላይ በቂ ግንዛቤ ተፈጥሯል፣
 በፊት የተጨነው እና የተሸሻለው መካከል ያለውን ልዩነት መረዳት ተችሏል፣
 የተሸሸለው ሶፍት ዌር የሚይዛቸው ቴክንካል ጉዳዮች ላይ መግባባት ለመድርስ ተችሏል፣
ተግባር 5፡- የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራት በሶፍትዌር አጠቃቀም ላይ ለ 50 የገ/ቁ/ብ/ኅ/ሥ/ማኅበራት ሙያዊ ድጋፍ
ማድረግ 40 ዎቹ ያሉበትን ደረጃ ለማወቅ ክትትል የተደረገ ማድረግ ተችሏል፡፡

ተግባር 6፡- ለፌዴራል አስፈፃሚ አካላት የፋይናንስ አገልግሎት አሰጣጥ ላይ አንድ ዙር የአሰልጣኞች ስልጠና ለመስጠት ታቅዶ በታቀደው
መሰረት ተከናዎኗል፣

የስልጠናዉ ዓላማ፡-

 የፋይናንስ ኅብረት ሥራ ዘርፍ የሚፈልገውን ክህሎት በማጠናከር የባለሙያን የመፈጸምና የማስፈጸም አቅም
በማሳደግ የተገልጋይን ፍላጎት ማርካት፤
 ከሌሎች መሪ ሥራ አስፈጻሚዎች ጋር ያለውን ቅንጅታዊ አሰራርን በመፍጠር እና የተሻለ ውጤትን ለማምጣት፤

የተከናወኑ ተግባራት፡-

 ለስልጠናው የሚያስፈልገውን ቅድመ-ዝግጅት በማድረግ አዳማ ከተማ ላይ ከነሐሴ 01 እስከ 07 2015 ዓ.ም
ለተከታታይ ሰባት ቀን ተሰጥቷል፣
 በሥልጠናው ላይ የተሳተፉ ባለሙያዎች ከኅብረት ሥራ ማስፋፊያ መሪ ስራ አስፈፃሚ ከአርብቶ አደርና ቆላማ
አካባቢ ኅብረት ሥራ ማኅበራት ማደራጀት፣ ማጠናከር እና ማዘመን ዴስክ፣ ከኅብረት ሥራ የህግ አገልግሎት እና
ኢንስፔክሽን መሪ ስራ አስፈፃሚ፣ ከኅብረት ሥራ ማኅበራት የብቃት ማረጋገጫ መሪ ስራ አስፈፃሚ፣ ከኅብረት ሥራ
ማኅበራት ኦዲት መሪ ስራ አስፈፃሚ እና ከፋይናንስ ኅብረት ሥራ ልማት መሪ ሥራ አስፈፃሚ ናቸው፣

8
የስልጠናው አሰጣጥ ሂደት፡-
 በተሰጡ የስልጠና ሪዕሶች ላይ የተሸለ ተሞክሮ ያላቸው ባለሙያዎች እንድሰጡ ተደርጓል፡
 ስልጠናው በተግባር እና በተሞክሮ የታገዘ እንዲሆን ለማድረግ በዘርፉ የተሸለ ክህሎት ያላቸው ባለሙያዎች ከፍርቄ
የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራት ዩኒዬን፣ ከነፃነት ፋና ከፍርቄ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ
ማህበራት ዩኒዬን እና ከአዋጭ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበር በመጋበዝ በተጨማሪነት ስልጠናውን
እንዲሰጡ ተደርጓል፣
ስልጠናው የተሰጠባቸው ሪዕሶች፡
 የኅብረት ሥራ ማህበራት አደረጃጀት ጽንሰ-ሃሳብ እና መመሪያ፣

 የፋይናንስ ግብይት ጽንሰ-ሃሳብ፣

 ወለድ አልባ የፋይናንስ አገልግሎት ጽንሰ-ሃሳብ እና አተገባበር፣

 የኅብረት ሥራ ማህራት አነስተኛ ኢንሹራንስ (Micro-Insurance) ጽንሰ-ሃሳብ እና አተገባበር፣

 የ PEARLES ጽንሰ-ሃሳብ እና አተገባበር፣

በስልጠናው የታዩ ጠንካራ ጎን

• ስልጠናው የተሰጠበት በዝግጅት ጊዜ የተሰጠ በመሆኑ ፈጻሚውን በተሸለ ያዘጋጀ መሆኑ፣


• ለስልጠናው የተሰጠው ጊዜ ጥሩ መሆኑ እና ሰልጣኙ በደንብ እንዲያስብ፤ እንዲገነዘብ ያደረገ መሆኑ፣

• የስልጠናው አቀራራብ ሰልጣኙ የተሰጡ ስልጠናዎችን በአግባቡ እንዲረዱ ደረገ መሆኑ፣

• አሰልጠኞች ከገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራት በጋበዛቸው ስልጠናው በተግባር የተደገፈ ማድረጉ፣

• የሰልጠኞች ቁጥር የተመጠነ መሆኑ ለተሳትፎ አመቺ አድርጎታል፣

• የሰልጣች ስብጥር /አደራጅ፤ ኦዲት፤ እንስፔክሸን፤ ሰርትፍኬሼን/ መሆኑ እርስ በርስ ለመማማር ምቹ ሁኔታ የፈጠረ
መሆኑ፣

የስልጠናው ውጤቶች፡-

 በተሰጡ ሪዕሶች ላይ ሰልጣኞች የተሸለ ግንዛቤ እንዲኖራቸው አድርጓል፣


 የቀጣይ ተግባራት አፈጻጸም ፈጻሚውን በተሸለ ያዘጋጀ መሆኑ፣
 የተለያዩ ክፍሎች መካከል የተሸለ መናበብ እና የሥራ ግንኙነት የፈጠረ መሆኑ፣

የተገኙ ልምዶች፡-

 በፌዴራል ደረጃ ያሉ ባለሙያዎችን ለብቻው ማሰልጠን በጋራ እንዲወያዩ እድል የሚፈጥር በመሆኑ የጋራ አረዳድ
እንዲኖር እድል የሚፈጥር መሆኑ፣

9
 አነስተኛ ቁጥር ያላቸው ሰልጣኞችን በአንድ ላይ ማሰልጠን ግንዛቤ ለመፍጠር የተሸለ መሆኑ፣
 የስልጠና ሪዕሶችን በመለየት በዘርፉ የተሸለ ክህሎች ያላቸው ባለሙያዎች እንዲያሰለጥኑ ማድረግ የተሸለ ግንዛቤ
መፍጠር እንደምችል፣
 በስልጠናዎች በተግባር ሥራ ውስጥ ያሉ የኅብረት ሥራ ማህበራት ባለሙያዎችን በአሰልጣኝነት መጠቀም የተሸለ
ክህሎት ማስጨበጥ እንደምቻል፣

ግብ 6፡- የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራት የመረጃ አቅርቦት ተደራሽነትን ማሳደግ

ተግባር 1፡- በዓመቱ የ 2016 አራት የሩብ ዓመት ሪፖርቶችና የ 2017 ዓመታዊ ዕቅድ በድምሩ 6 ሪፖርቶች በሩብ ዓመቱ 1

ዕቅድ እና 2 ሪፖርት ለማዘጋጀት በታቀደው መሠረት የዓመቱ የዘርፉ የሴክቴር፣ የፕሮግራም በጀት፣ የ PSNP-

LH, LLRP እና RUFIP ዕቅዶች እና የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ሪፖርት ተዘጋጅቶ ለሚመለከተው አካል ቀርቧል፣

ተግባር 2፡ መሠረታዊ መረጃዎችን በማሰባሰብ፣ በመተንተንና በማደራጀት በተሟላ ሁኔታ (100%) ለተጠቃሚዎች

ተደራሽ ለማድረግ ታቅዶ ተከናውኗል

ተግባር 3፡ የክልሎች አንድ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅ/ሥ/ማ ሪፖርት ማቅረቢያ ፎርማቶችን በማሻሻል ለማዘጋጀት

ታቅዶ አንድ ሰነድ ተዘጋጅቷል፣


ግብ 7፡- የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራት የቁጠባ መጠን ማሳደግ

ተግባር 1፡- በፌዴራል ደረጃ ለተደራጁ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራት በማጠናከር ያሰባሰቡትን ቁጠባ

እና ካፒታል በዓመት ብር 3 ቢሊዮን እና የሩብ ዓመቱ ብር 0.75 ቢሊዮን እስከዚህ ሩብ አመት 1.35 ቢሊዮን

ለማሰባሰብ ታቅዶ በሩብ ዓመቱ የተሰበሰበ የቁጠባ መጠን ብር 70,162,382 እስከዚህ ሩብ አመት

1,570,237,038 ብር እና ካፒታል በብር 94,080,551 በድምሩ ብር 1,664,317,589 ከ 100% በላይ ማሰባሰብ

ተችሏል፣

ተግባር 2፡- በፌዴራል ደረጃ ለተደራጁ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራት በማጠናከር ከህፃናት በዓመቱ ብር

20 ሚሊያን እና በግማሽ ዓመቱ ብር 9 ሚሊየን ለማሰባበስ ታቅዶ ብር 7,785,488 ብር በአፈጻጸሙ 85.5 %

ከ 2,731 (ሴቶች 983) ሕጻናት ማሰባሰብ ተችሏል፣

ግብ 8፡- የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራት የብድር አቅርቦት ማሳደግ

ተግባር 1፡- በፌዴራል ደረጃ ለተደራጁ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራት በማጠናከር በዓመቱ ብር 5 ቢሊየን

በሩብ ዓመቱ ብር 2.5 ቢሊየን ለማሰራጨት ታቅዶ ብር 2,094,031,798 ብር አፈጻጸሙ 83.6% ለ 2,835

(ሴ 1,006) አባላታት ማሳራጨት ተችሏል፣


ግብ 9፡- የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራት የአደጋ ስጋትን መቀነስ
ተግባር 1፡ በፌደራል ደረጃ ተቋቋሙ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራት የአነስተኛ ብድር መድህን ዋስትና

አገልግሎት በመስጠት በዓመቱ ብር 50 ሚሊዮን በሩብ ዓመቱ ብር 25 ሚሊዮን ለማሰባሰብ ታቅዶ ብር

10
2,094,031,798 ብር በማሸፈን ብር 57,469,708 ከዕቅድ በላይ አርቦን ማሰባሰብ የተቻለ ሲሆን ጉዳት የደረሰባቸው

ብር 101,810.57 ተክፍሏቸዋል፤

ግብ 10፡- በገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራት የሚሰጠውን የወለድ አልባ የፋይናንስ አገልግሎት ማስፋፋት፣
ተግባር 1፡ በፌዴራል የተደራጁ 2 የገንዘብ ቁጠባና ብድር የኅ/ሥ/ማህበራት የወለድ አልባ የፋይናንስ አገልግሎትን መስጠት እንዲጀምሩ
ድጋፍ እና ክትትል ለማድረግ ታቅዶ ለ 2 ቱ ተሰጥቷል፤
ተግባር 2፡ በዓቱ 40 በሩብ ዓመቱ 20 የወለድ አልባ የፋይናንስ አገልግሎት የሚሰጡ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅ/ሥ/ማህበራትን ማጠናከር
እና ለክልሎች ድጋፋዊ ክትትል ለማድረግ ታቅዶ ለ 11 (55 ከመቶ) ተደርጓል፤
ተግባር 3፡- በወለድ አልባ የፋይናንስ አገልግሎት ላይ ለክልሎች ድጋፍና ክትትል ለማድረግ በታቀደው መሠረት አንድ ዙር

መስጠት ተችሏል፡፡

የድጋፍ አሰጣጡ ሂዳት፡-

 በወለድ አልባ የፋይናንስ አገልግሎት አሰታጥ ላይ ለሶማሌ ክልል ኅብረት ሥራ ኤጀንሲ ላይ ቴክኒካል ድጋፍ ተሰጥቷል፣
 ድጋፉ የተደረገው ከሥራ ክፍላችን መሪ ሥራ አስፈጻሚ እና የወለድ አልባ ዴስክ ኃላፊ የተገኙ ሲሆን በተጨማሪም
የተሸለ ክህሎትና ተሞክሮ ያላቸው ከኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ሼህ ሙሀመድዘይን ዘህረዲን
እና የፍርቄ የገንዘብ ቁ/ብ/የኅ/ስ/ማህበራት ዩኒዬን የሸሪዓ አማካሪ የሆኑት ኡስታዝ አብዱልሀዲ ነስሩን በመጋበዝ
እንዲገኙ በማድረግ በአተገባቡ ላይ ሰፊ ውይይት በማድረግ መስተካከል የሚገባቸው ጉዳዮች እንዲስተካከሉ ማድረግ
እንዲቻል ድጋፍ ተደርጓል፣
 ድጋፉ የተሰጠው ክልሉ አዘጋጅቶት በነበረው የወለድ አልባ የፋይናንስ አገልግሎት አተገባበር ውይይት ላይ ጠገኙተው
የነበሩ የሶማሌ ክልል የፋይናንስ ኅ/ስራ ልማት መሪ ስ/አስፈፃሚ፣ የሶማሌ ክልል የክልል እና የወረዳ LLRP
አስተባባሪዎች፣ የሶማሌ ክልል የሸሪዓ አማካሪዎች፣ የሶማሌ ክልል የወረዳ ኅብረት ሥራ ጽ/ቤት ኃላፊዎች፣ የሶማሌ
ክልል የክልል እና የወረዳ ኅብረት ሥራ ቡድን መሪዎች፣ የሶማሌ ክልል የክልል እና የወረዳ ኅብረት ሥራ ባለሙያዎች
ናቸው፣

የተሰጡ ሙያዊ ድጋፎች፡-

 በገንዘብ ቁጠባና ብድር የኅብረት ሥራ ማህበራት ስለሚሰጡ የወለድ አልባ የፋይናንስ አገልግሎቶች የነበረውን
የተሳሳተ ግንዛቤ በተለይም ስለቁጠባ አገልግሎቶች አሰራር ስርዓት እና ስለብድር አገልግሎትቶች አሰራር ስርዓት
ለማረም ጥረት ተደርጓል፡፡
 የወለድ አልባ የብድር አገልግሎት አሰራር ስርዓት ከሸሪዓ ድንጋጌዎች አንጻር በኡለሞች እና በሸሪዓ አማካሪዎች
መካከል በተለይም የሙራባሃ ብድር አገልግሎት ላይ የነበረው አከራካሪ ነጥቦች ዙሪያ ሰፊ ውይይት በማካሄድ ግልፅነት
ለመፍጠር ተሞክሯል፤

 በክልሉ ሸሪዓ-መር የሆነ ወለድ አልባ የፋይናንስ አገልግሎትን በመስጠት የአባላትን የፋይናንስ ፍላጎት ለማሟላት እና
ተደራሽነቱን ለማሳደግ ከማን ምን ይጠበቃል በሚል ከሚመለከታቸው ኃላፊዎች እና የሸሪዓ አማካሪዎች ጋር
የወደፊት አቅጣጫ አስቀምጠናል፡፡

11
ግብ 11፡- በገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራት የሴቶችን እና ወጣቶችን ተጠቃሚነት ማሳደግ
ተግባር 1፡ በፌዴራል ደረጃ የተደራጁ 4 የገ/ቁ/ብ/ኅ/ሥራ ማህበራት የሴቶችን ተሳትፎ በአባልነት 20,000፣ በአመራርነት 13 እና 2 ቢሊዮን ብር ብድር ለሴቶች

በመስጠት ተጠቃሚ እንዲያሳድጉ ድጋፍ እና ክትትል ለማድረግ ታቅዶ ለ 3 ቱ ተደርጓል፣

ተግባር 2፡ በፌዴራል ደረጃ ከየተደራጁ 4 የገ/ቁ/ብ/ኅ/ሥራ ማህበራትን በማጠናከር የወጣቶችን ተሳትፎ በአባልነት 8,000፣ ድጋፍ እና ክትትል ለማድረግ ታቅዶ ለ 3 ቱ
ተደርጓል፣
ግብ 12፡- የበጀት አጠቃቀም ውጤታማነትን ማሳደግ

ተግባር 1፡ ለፋይናንስ ኅብረት ሥራ ልማት መሪ ሥራ አስፈፃሚ የተመደበ መደበኛ በጀትን ውጤታማ በሆነ መንገድ ሙሉ በሙሉ 100% ለመጠቀም ታቅዶ ---------
ከመቶ መጠቅም ተችሏል፤
ተግባር 2፡- በፕሮግራሞችና ፕሮጀክት ለዘርፉ የተመደበ በጀትን ውጤታማ በሆነ መንገድ ሙሉ በሙሉ 100% ታቅዶ ---------ከመቶ መጠቅም ተችሏል፤

ግብ 13፡- የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራት የዲጂታል ኢኮኖሚ ትግበራን ማሳደግ

ተግባር 1፡- በፌደራል የተደራጁ 3 የገ/ቁ/ብ/ ኅ/ሥራ ማህበራት የዲጂታል ኢኮኖሚ ትግበራ ውስጥ ማስገባት ታቅዶ 1 (33.3 ከመቶ) ማስገባት
ተችሏል፤

ተግባር 2፡ በፌደራል የተደራጁ 3 የገ/ቁ/ብ/ ኅ/ሥራ ማህበራት የፋይናንስ መረጃ ቋት እና ዘመናዊ የሂሳብ አያያዝ ትግበራ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ድጋፍ
ለማድረግ ታቅዶ 1 (33.33 ከመቶ) ማስገባት ተችሏል፣

ተግባር 6፡- የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራት ላይ ተዘርግቶ የነበረውና የተሻሻለውን software ለ 50 ለገንዘብ

ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራት መጫን በዕቅድ የተያዘ ሲሆን የ software ተጠቃሚ የሆኑ 40

የገ/ቁ/ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራትን ነባራዊ ሁኔታ የመለየት ሥራ ተሰርቷል፡፡

ግብ 15፡- የገ/ቁ/ብድር ኅ/ሥራ ማህበራት አሰራር ስርዓት ማሻሻል፣

ተግባር 1፡ አንድ የገ/ቁ/ብድር ኅ/ሥራ ማህበራት የፋይናንስ አገልግሎት አሰጣጥ መመሪያ ማጠናቀቅ ታቅዶ ተጠናቆ ለሚመለከተው አካል ተልኳል፡፡

ተግባር 2፡-የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራት ህጋዊ ሰውነት እድሳት ማስፈጸሚያ አንድ ማኑዋል ለማዘጋጀት ታቅዶ ተከናውኗ፣

ተግባር 3፡ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራት አንድ የውህደት አሰራር ለማዘጋጀት ታቅዶ ተከናውኗል፤

ግብ 16፡- ቅንጅታዊ አሰራርን ማሳደግ

ተግባር 2፡ ዓለም-አቀፍ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራት አመታዊ በዓል አንድ ዙር ማክበር ታቅዶ

ተከናውኗል፡፡

 የክብረ በአሉ ተሳታፊ የነበሩ አካላት፡-


ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች፣ ኢትዮጵያ ኅብረት ስራ ኮሚሽን አመራሮችና ባለሙያዎች፣ የተመረጡ ኅብረት ሥራ
ማህበራት የኒየኖች ሥራ አስኪያጆች እና ቦርድ አመራር አካላት እንዲሁም ከሌሎች ባለድርሻ አካላት የተወከሉ ተሳታፊዎች
ናቸው፡፡ በዓሉ በአለም አቀፍ ደረጃ ለ 75 ኛ ግዜ፣ በአገር አቀፍ ደረጃ ለሁለተኛ ጊዜ “Membes Helping members through
saving and credit cooperatives” የቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራት አባላት እርስ በርስ ይደጋገፋሉ!!" በሚል መሪ ቃል
ተከብሯል፡፡

12
አጠቃላይ ጥሪ የተደረገላቸው ተሳታፊዎች 400 ሲሆን የተገኙ ተሳታፊዎች ብዛት 382 (ሴት 104) 95.5% ናቸው፡፡
 ክብረ በአሉ የተካሄደበት ቦታና ቀን፡- ኢንተርኮንትኔታል ሆቴል ህዳር 27 ቀን 2016 ዓ.ም ነበር፡፡
የክብረ በዓሉ ዋና ዓላማ፡-
የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራት በአገሪቷ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ልማት ስኬቶችና ያሉባቸው ተግዳሮቶች
በባለድርሻ አካላት እንዲታወቁና የዘርፉን ውጤታማነት ለማሳደግ ምቹ ሁኔታዎችን ለመፍጠር ነው፡፡

4.2. ዝርዝር ዓላማ፡-

 በገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራት አንቅስቃሴ የተገኙ ስኬቶችን በየደረጃው በሚገኙ አካላት እንዲታወቁ ማድረግ፣
 በገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማኅበራት የሥራ እንቅስቃሴ ላይ ያሉ ማነቆዎች በሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት
እንዲታወቁ ማድረግ፣
 በገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማኅበራት የሥራ እንቅስቃሴ ላይ ያሉ ማነቆዎች እንዲፈቱ ምቹ መደላድል በመፍጠር የአባላት
ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥና የሚኖራቸውን አገራዊ አስታዋፅኦ ለማሻሻል፣
 ተሳታፊ አካላት በገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራት የተገኙ ምርጥ ተሞክሮዎችን እንዲለዋወጡና እንዲሰፋፉ ለማድረግ፤
 ባለድርሻ አካላት በሚመለከታቸው ተግባር ላይ የነቃ ተሳትፎ እንዲያደርጉ የጋራ መግባባት ላይ ለመድረስና ተቀናጅቶ በመስራት
ለዘርፉ ውጤታማነት ምቹ ሁኔታዎችን ለመፍጠር፤
ክብረ በዓሉ አስፈላጊነት፡-
የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራት የአገራችንን የኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ፖሊሲዎችን፣ ስትራቴጂዎችን፣ የድህነት ቅነሳ
ፕሮግራሞችንና ዕቅዶችን በማስፈፀም ረገድ ሃገራዊ ዕድገቱን በመደገፍና ፍትሃዊ ተጠቃሚነትን በማረጋገጥ በኩል አስተዋፅኦ የሚያደርጉ
ተቋማት ናቸው፡፡
በተለይም፡-
 ለተለያዩ አገልግሎቶች የሚውል የብድር ፍላጎት በማሟላትና የግብይት ሥራውን በማሳለጥ፣
 በገጠር አነስተኛ የፋይናንስ አገልግሎቶችን በቀላሉ ተደራሽ በማድረግ፣
 ከአርሶ አደር፣ አርብቶ አደርና ከተማ የሚኖር ህብረተሰብ ቁጠባን በማሰባሰብ እና የብድርና የኢንሹራንስ አገልግሎት ችግሮችን
በቅርበት ሆነው በመፍታት እንዲሁም አገልግሎቶችን በማመቻቸት የህብረተሰቡን የኑሮ ደረጃ እንዲሻሻል በማድረግ፣
 ኢኮኖሚውን በመደገፍና በማሳደግ አስተዋፅኦ ያላቸው ተቋማት በመሆናቸው፣
 የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራት በገጠርና በከተማ የሚኖረውን ህብረተሰብ በኢኮኖሚ በማስተሳሰር የሚሰሩ
በመሆናቸው ፣
 በአብዛኛው በዝቅተኛና መካከለኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኘውን የህብረተሰብ ክፍል በተለይ ወጣቶችንና ሴቶችን በብዛት በማሳተፍና
ተጠቃሚ በማድረግ የላቀ ድርሻ ያላቸው ተቋማት ናቸው፣
ሆኖም በገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማኅበራት የሥራ እንቅስቃሴ ፈርጀ ብዙ ስኬቶች ቢመዘገቡም የሚጠበቅባቸውን ድርሻ
በሚፈለገው ደረጃ እንዳያወጡ ዘርፈ ብዙ ውስጣዊና ውጫዊ ማነቆዎች አሉባቸው፡፡ ስለሆነም ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር
በመቀናጀት የኅብረት ሥራ ማኅበራቱን መልካም ተምክሮዎች እንዲታወቁ በማድረግና በማስፋፋት እንዲሁም በሥራ ሂደት

13
ያጋጠሙ ችግሮችን በመፍታት የተቋማቱን ውጤታማነትና የአባላትን ተጠቃሚነት በማሳደግ የሚኖራቸውን አገራዊ ፋይዳ ለማጎልበት ምቹ
ሁኔታዎችን ከመፍጠር አንፃር ይህን አገራዊ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማኅበራት ክብረ በዓል ማካሄድ አስፈላጊ ነው፡፡

4.3. በዝግጅት ምዕራፍ የተከናወኑ ተግባራት፡-

 ተሳታፊ አካላትንና አወያዩችን የመለየት ሥራ ተሰርቷል፣


 የሥራ ማስፈፀሚያ ዕቅድ ተዘጋጅቷል፣
 የተለያዩ ንዑሳን ኮሚቴዎችን በማዋቀር እና ሥራ በማከፋፈል የውሎ ግምገማ ተካሂዷል፣
 የስብሰባ አዳራሽ የማመቻቸት ሥራ ተሰርቷል፣
 በበዓሉ ለሚሳተፉ አካላት ጥሪ የማስተላለፍ ተግባር ተከናውኗል፣
 ለውይይት የሚቀርብ ፅሁፍ መገምገምና ለመድረኩ በሚመጥን ሁኔታ ተዘጋጅቷል፣
 ለዝግጅቱ የሚያስፈልጉ ግዢዎችን እና ፕሮፎርማዎችን ከሚመለከታቸው የግዥ ባለሙያዎች ጋር በመሆን
የማመቻቸት ሥራ ተሰርቷል፣
 መርሀ ግብር በማዘጋጀት በሚመለከተው አካል ማስፀደቅ፤

በክብረ በዓሉ የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት፡-

በመጀመሪያ በተያዘው የድርጊት መርሃ ግብር መሠረት የበዓሉን አጠቃለይ ፕሮግራም የማስተዋወቅ ተግባር በታዋቅ የመድረክ
አስተዋዋቅ እንድመራ ተደርጓል፡፡ መድረኩ በማርች ባንድ በመታጀብ እና ከፍተኛ የመንግስት የሥራ አመራሮች የተከፈተ
ሲሆን በዓሉን አስመልክቶ የተዘጋጀው የመወያያ ጹሑፍ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበት በመጨረሻም የኢለቱ ክቡር እንግድች
ማጠቃለያ እና የሥራ መመሪያ ሰጥቶበታል፡፡

የቀረቡ ጥያቄዎች፣ የተሰጡ መልሶች፣ የተሰጡ የማዳበሪያ ሃሳቦችና ገንቢ አስተያየቶች፡-

የቀረቡ ጥያቄዎች

 ከፖሊሲ አንፃር

 የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማኅበራት እያደጉ ሲመጡ ምን አንደሚሆኑና መዳረሻቸውም ምን መሆን
እንዳለበት የሚያሳይ ፍኖተ ካርታ ቢኖር?

 ማዳበሪያ በኩፖን ስርጭት ለምን በጸደይ ባንክ በኩል እንዲሰራጭ ይደረጋል፣

 በኅብረት ሥራ አዋጁ ላይ በተቀመጠው መሰረት መሬት በነጻ የሚያኙበት ሁኔታ ቢመቻች፣

 የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማኅበራትን ከማጠናከር አንፃር በኅብረት ሥራ ማኅበራት መካከል በትብብር
ለመስራት እንዲቻል አደረጃጀቱ ምን መምሰል እንዳለበት ተፈትሾ ቢስተካከል?

14
 የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማኅበራት በሰለጠነ የሰው ኃይል እና በዕውቀት እንዲመሩ ለሁሉም የገንዘብ ቁጠባና
ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራት አመራር አካላት በሥራ አመራር ስልጠና ቢሰጥ?

ከክትትልና ድጋፍ አንፃር፡-

 የኅብረት ሥራ ማኅበራት ካላቸው አስተዋፅዖ አንፃር ከአሰራር፣ከቴክኖሎጂ አጠቃቀም፣የአባላትን ችግር ከመፍታት


አንፃር ምን ያህል ለአባላት ተደራሽ ናቸው?

ከአደረጃጀት፡-

 ቀደም ሲል በነበሩት ግዜያት በተለያዩ አካላት የኅብረት ሥራ ባንክን ለማቋቋም ጥረት ተደርጎ ስኬታማ አልነበረምና
ክቡር የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ምክትል ገዥ ዛሬ ከገቡት ቃል አንፃር በአሁኑ ስዓት ለማቋቋም የሚቻለው ከባለፈው
የተለየ ምን ነገር ቢኖር ነው?

 ልክ አንደ አዋጭ የገንዘብ ቁጠባና ብድር (ኃ/የተ) ኅብረት ሥራ ማህበር በሥራ ላይ ያሉ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት
ሥራ ማህበራት አደረጃጀትና ማስፋፋት ሞዴሎችን በመቃኘትና በማሻሻል በሌሎች የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት
ሥራ ማህበራት ተግባራዊ ማድረግ ቢቻል?

ለቀረቡ ጥያቄዎች የተሰጡ መልሶች፡-

ከፖሊሲ አንፃር፡-

 የኅብረት ሥራ ባንክን ለማቋቋም ከፖሊሲ፣ከአሰራር እንዲሁም ከአደረጃጀት አንፃር ከተፈቀደልንና ምቹ ሁኔታዎች ካሉ


የኅብረት ስራ ባንክን ለማደራጀት በቅርብ ግዜ ወደ ሥራ ይገባል፣

 በኅብረት ሥራ አዋጁ ላይ በተቀመጠው መሰረት መሬት በነጻ የሚያኙበት ተግባራዊነቱ ላይ የሚመለከታቸው አካላት
ትኩረት ሰጥተው መስራት ይገባቸዋል

 የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማኅበራት ለአባላት ፈጣንና ተደራሽ አገልግሎት ለመስጠት አሰራራቸውን
ማዘመንና በቴክኖሎጂ ማስደገፍ ይገባቸዋል፣

 የኅብረት ሥራ ማኅበራት ሁለት መሠረታዊ ችገሮች ያሉባቸው ሲሆን እነሱም፡ የቦታ አቅርቦት እና የፋይናንስ አቅርቦት
ችገሮች ናቸው፣ እነዚህንም ችገሮች ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት ለመፍታት ጥረት ይደረጋል፣
 የመሬት ይዞታን በብድር ማስያዣነት በመጠቀም ብድር ማግኘት እንደሚቻል በብሄራዊ ባንክ የወጣው መመሪያ
የገ/ቁ/ብ/ኅ/ሥ/ማህበራት የፋይናንስ ተቋማት ባለመሆናቸው ምክንያት የመመሪያው ተጠቃሚ አለመሆናቸው እንዴት
ይታያል?

ከክትትልና ድጋፍ አንፃር፡-

15
 የቀረቡ ልሞዶች እና ተሞክሮዎች ተስፋ ሰጪ ናቸው፡፡ በዚህ ውስጥ ግን ብዙ ማነቆዎች እንዳሉ ሊታወቅ ይገባል፡፡
ማነቆዎችን ለመፍታትም ሁላችንም የበኩላችንን ርብርብ ማድረግ ይገባል፣

 ለአዋጭ ውጤታማ መሆንና ለከፍተኛ ዕድገት መድረስ ምክንት የሆኑ ጉዳዮች በጥናት ቢለዩ፣በዚህም መሠረት ከጥናቱ
ከሚገኝ ውጤት በመነሳት ወደ ተሻለ ውጤት እንበቃለን፣

ከአደረጃጀት አንፃር፡-

 በኢትዮጵያ ኅብረት ሥራ ኮሚሽን በኩል የኅብረት ሥራ ማህበራት ሊግ እና አገራዊ ኅብረት ሥራ ማኅበበራት


ፌዴሬሽን ለማደራጀት በዕቅድ ተይዟል፣
 የኅብረት ሥራ ማኅበራትን ለማሳደግ በመተባበርና በመተጋገዝ መንፈስ በጋራ ከሰራን የምንመኘውን ለውጥ
ማምጣት ይቻላል፣
 የኅብረት ሥራ ማኅበራትን ማነቆዎች ለመፍታት ሁላችንም የሚመለከተን ባለድርሻ አካላት የተቻለንን ጥረት
ብናደርግ የተሻለ ለውጥ እናያለን፡፡ስለሆነም የሁላችንም መተባበር፣መደጋገፍና ለራስ ቃል በመግባትና ተቀናጅተን
በመስራት የምንመኘውን ውጤት እውን ማድረግ ይቻላል፡፡
የተሰጡ የማዳበሪያ ሃሳቦችና አስተያየቶች፡-

ከፖሊሲ አንፃር፡-

 የኅብረት ሥራ ማኅበራት የኅብረት ሥራ ባንክ ለማቋቋም ከፈለጉ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አስፈላጊው እገዛ
እንደሚደረግ የብሔራዊ ባንክ ምክትል ገዥ ቃል ገብተዋልና ለስኬታማነቱ

 የኅብረት ሥራ ማኅበራት አዋጅ 985/2009 ማስፈፀሚያ ደንብ እስካሁን ድረስ ያለመውጣቱ በአሰራር ላይ ከፍተኛ
ችግር እያስከተለ ስለሆነ በአጭር ግዜ ውስጥ ፀድቆ ተግባራዊ የሚሆንበት መንገድ ቢመቻች፤

 በየኅብረት ሥራ ማኅበራቱ ጥቅም ላይ ያልዋለ መጠባበቂያ ገንዘብ አለና ጥቅም ላይ የሚውልበት ሁኔታ ቢፈጠር፣

ከድጋፍና ክትትል አንፃር፡-

 የአዋጭ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማኅበር የሥራ ተሞክሮ መሠረት በማድረግ የተገኙ መልካም ልምዶችን
በሁሉም ክልሎች በሚገኙ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማኅበራት ለማስፋፋት በየደረጃው በሚገኙ
የሚመለከታቸው አካላት ጥረት ቢደረግ፣

 የኅብረት ሥራ ማኅበራት ያላቸው ተሰሚነትና ጠቃሚነታቸው ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ ነው፡፡ ስለሆነም ለዘርፉ የሥራ
እንቅስቃሴ መጠናከር የሁሉም ባለድርሻ አካላት ቅንጅታዊ ድጋፍ ያስፈልጋል፣

 በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በኩል አብዛኛው ከውይይቱ የተነሳው ሃሳብ ለወደፊት ልናከናውነው የሚገባ የቤት ሥራ
የሚሰጠንና የኅብረት ሥራ ማኅበራትን ችግሮችን ለመፍታት ተቀራርቦ መስራትን ይጠይቃል፣

16
 በኢትዩጵያ ኅብረት ሥራ ኮሚሽን በኩል የተጀመረው ከሌሎች የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት የሚደረግ ቅንጅታዊ
አሰራር ቢጠናከር፣
 የኅብረት ሥራ ማኅበራት እንዲያድጉ በዕውቀት የተመሰረተ እንቅስቃሴ ማድረግ አለባቸው፡፡ ለስኬታማነቱም ሁሉም
በየደረጃው የሚገኙ የሚመለከታው አካለት በመቀናጀት የዘርፉን አቅም ለመገንባት አስተዋፅኦ ማድረግ ይኖርባቸዋል፣
 የኅብረት ሥራ ማኅበራት ዋናው ማነቆ የውስጥ አቅማቸው አለመጠናከር ነው፡፡ ስለሆነም የውስጥ አቅማቸውን
ለማጠናከር ትኩረት ቢሰጠው፤

ከአደረጃጀት አንፃር፡-

 የኅብረት ሥራ ማህበራትን ቁጥር ከማብዛት ይልቅ ከውጤታማነት አንፃር ጥራት ላይ ትኩረት ቢደረግ፣ ሲደራጁ
በአነስተኛ የአባላት ቁጥር ሊጀምር ይችላል፡፡ ሆኖም ግን የአባላት ቁጥር እንዲያድግ ትኩረት ቢሰጠው፣
የማጠቃለያ ሃሳብና ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች፡-

ከክብረ በዓሉ ተሳታፊዎች መብራራት የሚገባቸውና ግልፅ ያልሆኑ ጉዳች ተነስተው ሰፊ ማብራሪያ ተሰጥቷል፡፡ በተጨማሪም
የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማኅበራት የሥራ እንቅስቃሴ ልማቱን ለማጠናቀር የሚያገለግሉ ገንቢ ሃሳቦችና
አስተያየቶች ቀርበው የጋራ መግባባት ላይ ተደርሷል፡፡ በሌላ መልኩ መድረኩ መማሪያ እና ሁሉንም ባለድርሻ አካላት ወደ
የአስተሳሰብ አንድነት ያመጣ ነበር ብሎ መውሰድ ይቻላል፡፡

በአጠቃላይ የአገራችን የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማኅበራትን በገጠርና በከተማ በማስፋፋት የአርሶና አርብቶ
አደሩን የቁጠባ ባህልና ልምድ በማሳደግና የብድር አገልግሎት ተደራሽ በማድረግ ዘርፉ ህብረተሰቡን የሚያሳትፍ
ተከታታይ፣ዘላቂና ፈጣን ልማት ለማረጋገጥና በዜጎች መካከል ፍትሃዊ የሃብት ክፍፍል እንዲፈጠር ወሳኝ ሚና የሚጫወቱ
የልማት ተቋማት መሆናቸውን መገንዘብ ተችሏል፡፡

ስለሆነም የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማኅበራት በአገር ልማት እየተጫወቱ ያለውን ሚና በመገንዘብ በዘርፉ
ተከታታይ፣ ዘላቂና ፈጣን ልማትን ለማረጋገጥና በዜጎች መካከል ፍትሃዊ የሃብት ክፍፍል እንዲፈጠር በየደረጃው የሚገኙ
የኅብረት ሥራ ማኅበራት ማስፋፊያ አካላት ያሉ መልካም ተሞክሮችን ከየአካባቢው ነባራዊ ሁኔታ በሚጣጣም መልኩ
በማስፋፋት ተግባራዊ በማድረግ የኅብረት ሥራ ማኅበራቱን ለውጤት ማብቃት ይኖርባቸዋል፡፡ በተጨሪም በየደረጃው
በሚገኘው ፈፃሚ፣ አስፋፃሚና ባለድርሻ አካላት የተጀመረውን የኅብረት ሥራ ማህበራት ሪፎርም ተግባራዊ ማድረግ፣
አገልግሎት አሰጣጥ ማዘመን፣ ጠንካራ የኅብረት ሥራ መፍጠር፣ አደረጃጀቱን ማጠናከር እና የፋይናንስ አገልግሎትን
ማስፋፋት፡፡

ትኩረት የሚደረግባቸው ዋና ዋና ጉዳዮች፡-


 የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማኅበራት በገጠርና በከተማ በመስፋፋት ከተደራጁበት ተልዕኮና ዓላማ አንፃር
በአባላት ኦኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊ፣ዲሞክራሲያዊና ባህላዊ ዘርፍ ሁለንተናዊ እንቅስቃሴ በማድረግ በአገር ልማት
የሚጠበቅባቸውን አስተዋፅኦ በማበርከት ዘርፉ ተከታታይ፣ ዘላቂና ፈጣን ልማት ለማረጋገጥና በዜጎች መካከል ፍትሃዊ
የሃብት ክፍፍል እንዲፈጠር ወሳኝ ሚና የሚጫወቱ የልማት መሳሪዎች መሆናቸውን መገንዘብ ይቻላል፡፡

17
 ባለንበት ወቅት ለገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማኅበራት እንቅስቃሴ መጠናክር እክል የሆኑ ጉዳዮችና አሰራሮች
እየተሻሻሉ ስለሆነ ለመጪው ጊዜ መሻሻል የሚገባችውን ችግሮች ለይተን ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመቀናጀት
እንዲስተካከሉ እናደርጋለን፣
 የኅብረት ሥራ ማኅበራትን የአባላትን የእውቀት፣ የግንዛቤ፣ አመራር፣ የክህሎት፣ አደረጃጀት፣አሰራር፣የቴክኖሎጂ
አጠቃቀም በየግዜው መፈተሸና ማሻሻል እንዲሁም ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅት መስራት፣
 የኅብረት ሥራ ማኅበራትን የፋይናንስ አቅርቦት ችግር ለመፍታት የአባላትን ቁጠባ ባህልን በማዳበር የውስጥ የፋይናንስ
አቅምን ለማሳደግ ቅድሚያ በመስጠት መስራት፤
 የኅብረት ሥራ ማኅበራትን ቀጣይነት ለማረጋገጥ እና የዜጎችን ተሳታፊነት እና ተጠቃሚነት ለማሳደግ ለወጣቶች እና
ሴቶች ልዩ ትኩረት መስጠት፣
 የኅብረት ሥራ ማኅበራት ዘመናዊ የቴክኖሎጂ ውጤቶችን እንዲጠቀሙ ሙያዊ ድጋፍ ማድረግ፣
 በየደረጃው በሚገኙ ፈፃሚ፣ ሌሎች አስፋፃሚና ባለድርሻ አካላት ላይ የሚታዩ የትኩረት፣ የቁርጠኝነት፣
የክህሎት፣የግብአት አቅርቦትና አሰራር ማነቆዎችን በመፈተሸና በማስተካከል ሁሉም የሚመለከታቸው የልማት
ኃይሎች ለስኬታማነቱ በተደራጀና በተቀናጀ አግባብ ሰፊ ርብርብ ማድረግ ትኩረት ሊደረግባቸው የሚገቡ ዋና ዋና
ጉዳዮች ናቸው፡፡

በክብረ በዓሉ ላይ የተገኙ ተሳታፊዎች ዝርዝር መረጃ


ተቁ ተሳታፊ አካላት የተሳታፊ አካላት ፆታ ድምር %
ዕቅድ ክንውን ወንድ ሴት
1. ከዩኒዬን 123 122 113 9 122 99
2. ከአዋጭ 13 13 8 5 13 100
3. ባንኮች 2 2 2 2 100
4. የኢ/ኅ/ሥራ ኮሚሽን 160 155 83 72 155 97
5. የክብር እንግዶች 15 7 6 1 7 47
6. የክልል ኅ/ሥራ ጽ/ቤት 14 10 8 2 10 71
7. ሌሎች 73 73 58 15 73 100
ድምር 400 382 278 104 382 95.5 %

ተግባር 4፡- ከሌሎች የሥራ ክፍሎች ጋር ለመስራት የሚያስችል አንድ የጋራ ዕቅድ ለማዘጋት ታቅዶ ተከናውኗል፣

4.2. በፕሮግራሞች እና ፕሮጀክት የተከናውኑ ተግባራት፡-

RUFIP III የተከናወኑ ተግባራት፡-

 የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራት በዲጂታል ኢኮኖሚ ትግበራ ዙሪያ ላይ ስልጠና መስጠት እና ከሌሎች

የፋይናንስ ተቋማት ጋር በድጅታል ማስተሳሰር የሚል ሲሆን ከፌዴራል እና ክልሎች የተውጣጡ የአደራጅ ተቋማት

18
ኃላፊዎችና ባለሙያዎች፣ ከኢትዮጵያ ብሐየራዊ ባንክ ጋር በመቀናጀት ከባንኮች፣ ገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ

ማህበራት እና ከኢትዮ ቴለኮም የተውጣጡ ተሳታፊዎች ተገኝቷል፡፡

በውይይቱ ላይ የቀረቡ ሰነዶች፡-

 የኅብረት ሥራ ማህበራት ጽንሰ-ሃሳብ እና የፋይናንስ አቅርቦት ነባራዊ ሁኔታ በኢትዮጵያ ኅብረት ሥራ ኮሚሽን
ቀርቧል፣

 የፋይናንስ አካታችነት፣ ዲጂታል ፋይናን አገልግሎት፣ የፋይናንሻል ክህሎት (Financial Literacy) እና የተጠቃሚዎች
የፋይናንስ ደህንነት ጥበቃ (Consumer Protection) ከሔራዊ ባንክ በመጡ 2 ከፍተኛ ባለሙያዎች ቀርቧል፣

 ከኢትዮ ቴሌኮም ቴሌ ብር፣ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሲቢኢ-ብር፣ የኦሮሚያ ኅብረት ሥራ ባንክ፣ (Gize pay) አቢሲኒያ

ባንክ እና ዳሽን ባንክ ያሉዋቸውን አገልግሎቶችና ለገ/ቁ/ብ/ ኅ/ሥራ ማህበራት ሊያስገኙ የሚችሏቸውን ጥቅሞች

በጥልቀት አቅርበዋል፣

በስልጠናው ላይ የተገኙ ተሳታፊዎች፡-

 ከኢትዮጵያ ኅብረት ሥራ ኮሚሽን 11፣

 የክልል የኅብረት ሥራ ማስፋፊያ አካላት 48፣

 የኅብረት ሥራ ማህበራት የተውጣጡ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ከ 26 በድምሩ 88 ተሳታፊዎች ተሳታዎች ተገኝቷል፣

በስልጠናው የተነሱ ሃሳቦች፡


 Agent Banking አዋጭነት፣ የደንበኞች ጥበቃ፣ Agent Banking ከዚህ በፊት የፋይናንስ ተቋማት ከማይክሮ ፋይናንስ
ጋር ሲሰሩ የገጠሟቸው ችግሮች፣ አሁን ያለበት ሁኔታ፣ ለተለያዩ የኅብረት ሥራ ማኅበራት እንደሁኔታቸው የሚመቹ
አገልግሎቶች ከመለየት አንፃር፣ ከቅርጫፎች ጋር ማስተሳሰርን በተመለከተ፣ በ Digital Credit እና አነስተኛ ብድር
አቅርቦት አንፃር፣ Agent Banking አገልግሎት ለመጀመር የተቀመጡ ቅድመ-ሁኔታዎች የኅብረት ሥራ አዋጅ
985/2009 ጋር ለማጣጣም የሚደረጉ ሁኔታዎች፣ ከዚህ በፊት ከኅብረት ሥራ ማኅበራት ጋር Supper Agent ላይ
ተሞክሮ ስለመኖሩ፣ Financial inclusion Sustainable ለማድረግ ምን እየተሰራ እንዳለ ጥያቄዎች የተነሱ ሲሆን
የተሰጡ ምላሾች፡-
 Agent Banking በአብዛኛው የተለየ ትርፍ የሌለው ለአንዳንድ ባንኮች በወጪ ብቻ አገልግሎቱ እሰጡ የሚገኙ ሲሆን
በዋናነት አላማው የፋይናንስ አካታችነት ተደራሽ ማድረግ ሲሆን በሂደት ከሦስት አመት በኋላ ትርፍ ሊያመጣ ይችላል፡፡
የተገልገዮችና የደንበኞች ጥበቃ በጥንቃቄ የሚሰራ ተግባር እንደሆን የፋይናንስ ተቋማተ ማረጋገጥ ችለዋል፡፡ Agent
Banking አገልግሎት ለመጀመር የተቀመጡ ቅድመ-ሁኔታዎች የኅብረት ሥራ አዋጅ 985/2009 ጋር በማይጋጭ ሁኔታ
እና ለሁሉም በሚመች መልኩ ማስተካከል እንደሚቻል ከስምምነት ተደርሷል፡፡ ከዚህ በፊት Supper Agent Banking
አገልግሎት ጋር በተያያዘ ማሟላት የሚገባቸው የፖሊሲ ዶክመንቶች ጋር ባለማሟላት መቸገር ይታይ የነበረ ሲሆን
አሁን መሻሻእንዳለው ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ የተለያዩ የኅብረት ሥራ ዩኒዬኖች በተለይ በቡና ላይ የተሰማሩ ከተለያዩ

19
የፋይናንስ ተቋማት ብድር በማግኘት ላይ ናቸው፡፡ CBO በኩል Innovation HaB የሚባል የተደራጀ ክፍል ሁሉንም
አገልግሎቶች የሚገመግም፣ የሚያሻሽልና አዳዲስ አገልግሎቶችን የመፍጠር ሥራ ያከናውናል፡፡
የተሰጡ አስተያየቶች፡-
 በምርት ወቅት ገበሬው ገንዘብ ተሸክሞ ወደ ቤት በሚሄድበት ወቅት የመሰረቅና ለአደጋ የሚያጋልጥ በመሆኑ በቅርበት
ገንዘብን ለመሰብሰብ ስለሚያስችል በፍጥነት ወደ ስራ ቢገባ፡፡
 ባንኮች ኅብረት ሥራን የሚያስተናግዱበት ዲፓርትመንት ወይንም አሰራር ቢኖራቸው፡፡
 Agent Banking አገልግሎት ተከታታይነት ያለው ተጠያቂነት፣ ኃላፊነት የሚፈልግ ስራ እንደሆነና በጥንቃቄ ሊያዝ
የሚገባው ነው፡፡
 በተበጣጠሰ መልኩ የምንሰማቸው የፋይናንስ ተቋማት የአገልግሎት ዓይነቶች ሰብሰብ ባለ በልኩ መቅረባቸው በቂ

ግንዛቤ እንዲኖረን አድርጓል፡፡

 በተጠናከረ መልኩ ወደ ስራ ለመግባት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እና የኢትዮጵያ ኅብረት ሥራ ኮሚሽን አሰራር

ቢያበጁለት፣ የሚሉ አስተያየቶች ተሰጥተዋል፡፡

 በመጨረሻም የድርጊት መርሃ ግብር የተቀረጸ ሲሆን ተግባራት በዝርዝር ቀርበው መችና ማን እንደሚያከናውናቸው

በግልጽ ተቀምጠዋል፡፡

 በማጠቃለያም ኅብረት ሥራዎች ለጠቅላላ ጉባኤ፣ ለቦርድ እና ለመሠረታዊ ኅብረት ሥራ ማኅበራት የማሳወቅ ስራ

እንዲያጠናቅቁ፣ ለባንኮች Product segmentation ከኅብረት ሥራ አንፃር ለይተው እንዲያጠናቅቁ፣ ከክልል ኅብረት

ሥራ ኤጀንሲ ኃላፊና ባለሙያዎች የመከታተል እና የመቆጣጠር፣ በተጨማሪ አቅማቸውን በመለየት ተጨማሪ

የኅብረት ሥራ በግባት ካለባቸው መለየት፣ በብሔራዊ ባንክ በኩል ተጨማሪ ባንኮች መካተት ከፈለጉ እንዲካተቱ

የማድረግ ሥራ እንዲከናወን በመግባባት ስልጠናው ተጠናቋል፡፡

በቆላማ አከባቢ ማህበረሰብ የኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክ (LLRP)

 ፕሮጀክቱ ክልሎች የሆኑት አፋር፣ ሶማሌ እና ጋምቤላ ክልሎች ውስጥ የሚገኙ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ
ማህበራትን የማጠናከር ተግባር ተከናውኗል፣

 በፕሮጀክቱ በተያዘው በጀት በሬጉላቶሪ እና በኦዲት የሥራ ክፍሎች ለኢንስፔክሽ እና ለኦዲት ባለሙያዎች የአሰልጣኞች
ስልጠና ተሰጥቷል፣

5. ከሌሎች ተቋማት ጋር በቅንጅት የተሰሩ ተግባራት፡-


 የወለድ አልባ የፋይናንስ አገልግሎትን ወደ ክልሎች ለማስፋፋት በምናደርገው ጥረት ከኢትዮጵያ እስልምና
ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ጋር ቅንጅታዊ አሰራር ለመፍጠር ተቋማዊ ግንኙነት ጀምረናል፡፡

 በአዋጭ ኃላፊነቱ የተወሰነ መሰረታዊ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበር የወለድ አልባ የፋይናንስ
አገልግሎትን ለማስጀመር መነሻ-ሀሳብ (PROPOSAL) ተዘጋጅቶ ተልኳል፡፡

20
 በ GIZ ፕሮጀክት ከታቀፉ ክልሎች መካከል በኦሮሚያ ክልል ውስጥ ለሚገኙ ለ 3 ሴት እና 4 ወንድ በድምሩ ለ 7
የዘር ብዜት ህብረት ሥራ ማህበር ለዩኒየን ሥራ አስኪያጆችና ለባለሙያዎች የፋይናንስ ክህሎት ማሳደጊያ እና
የአነስተኛ መድን ዋስትና ስልጠና ላይ ለ 3 ተከታታይ ቀናት የፋይናንስ ክህሎት ማሳደጊያ ስልጠና ተሰጥቷል፡፡

 የአዲስ አበባ ኅብረት ሥራ ኤጀንሲ በአዘጋጂነት ስልጠና ላይ 2 ባለሙያዎችን በማሳተፍ ከ 11 ከፍለ ከተሞች
ለተውጣጡ ለ 31 ወንድ እና ለ 11 ሴት በድምሩ ለ 42 የገንዘብ ቁጠባና ብድር ባለሙያዎች በቁጠባና ብድር፤
በስጋት አስተዳደር እና በአነስተኛ መድን ዋስተና ለ 5 ቀናት ስልጠና ተሰጥቷል፡፡

6. የበጀት ዓመቱ ጠንካራ ጎኖች፣ ያጋጠሙ ችግሮችና የተወሰደ መፍትሄ

6.1. የታዩ ጠንካራ ጎኖች

 የ 2016 በጀት አመት እቅድን አራቱም ዴስኮች በመናበብ በጋራ ማዘጋጀታቸው፣

 የ 2016 በጀት ዓመት ዕቅድ ሲዘጋጅ ከሚመለከታቸው ክፍሎች ጋር በመናበብ የጋራ ለማድረግ ጥርት መደረጉ፣

 የታቀዱ ተግባራትን በዕቅዱ መሰረት ለማከናወን ጥረት መደረጉ፣

 የተሰጡ ሥልጠናዎች የተቀናጁ እና ወቅታዊ መሆናቸው፣

 አገልግሎቱን ለማግኘት የሚመጡ ተቋማትና ግለሰቦች በሚጠይቁት ጥያቄ መሰረት ግንዛቤ መስጠት መቻሉ፣

 የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራትን የማጠናከር ተግባር በጥራትና በወቅቱ ማከናወን መቻሉ፣

6.2. ያጋጠሙ ችግሮች

 የ 2016 በጀት ዓመት ዕቅድ ዝግጀት ረጅም ጊዜ መውሰዱ በመጀመሪያ ሩብ ዓመት የታቀዱ ሥራዎችን ማዘግየቱ፣

 ከክልሎች ወቅታዊና የተቀናጀ መረጃ ማግኘት አለመቻል፣

 በፕሮግራምና ፕሮጀክት የታቀዱ ተግባራት በሚመለከታቸው አካላት ፀድቆ አለመምጣትና ከተጠየቀው በጀት በታች

መፈቀዱ፣

6.3. የተወሰዱ መፍትሄ

 መረጃዎችንና ወቅታዊ ሪፖርቶችን ከሁሉም ክልሎች ማግኘት እንዲቻል የተለያዩ ፎርማቶችን በማዘጋጀት

ተከታታይና ጠናካራ ግንኙነት መፍጠር፣

 የአደረጃጀት መመሪያዎች፣ አዋጅና ማስፈፀሚያ ደንቦች ወቅታዊ ማሻሻያ የሚደረግባቸውን ነጥቦች በመለየትና

በመገምገም ለሚመለከተው አካል በማቅረብ ጠንካራ ክትትል ማድረግ፣

6.4. የትኩረት አቅጣጫዎች

 በሪፎርም የተያዙ ተግባራት መረጃ ማጥራት፣ በደረጃ መለየት እና የውህደት ተግባራትን በትኩረት መስራት፣

21
 የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራትን ማጠናከር፣

 አገራዊ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራት ፌዴሬሽን ማቋቋም፣

 የተጀመረውን የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራት የመረጃ ቴክኖሎጅ ዝርጋታን ተግባራዊ ማድረግ፣

 የወለድ አልባ የፋይናንስ አገልግሎት ለማስፋፋት በትኩረት መስራት፣

22
የ 2016 የመጀመሪያ ሪብ ዓመት በጀት ዓመት የፕሮግራም በጀት ዓመታዊ ዕቅድ ክንውን ሪፖርት ከሐምሌ 01/2015 እስከ መስከረም 30/2016 ዓ.ም.
የሩብ ዓመት ዕቅድ ክንውን አፈፃፀም ንፅፅር በ%
ዝርዝር ተግባራት መለኪያ የዓመቱ
ዕቅድ በዚህ ሩብ እስከዚህ በዚህ ሩብ እስከዚህ ሩብ የዚህሩብ እስከዚህ ሩብ ምርመራ
ዓመት ሩብ ዓመት ዓመት ዓመት ዓመት ዓመት

ፕሮግራም በጀት
ግብ 1፡- የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራት አደረጃጀትን ማሻሻል
ማዘመን
በፌደራል ለተደራጁ 4 የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅ/ሥ/ማህበራትን ማጠናከር እና ድጋፋዊ በቁጠር 4 4 4 3 3 75 75
ክትትል ማድረግ፤
በክልል ለተደራጁ 116 የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅ/ሥ/ማህበራትን ማጠናከር እና ለአደራጅ በቁጠር 116 36 36 40 40 111 111
ተቋሙ ሙያዊ ድጋፍ መስጠት፤
በፌዴራል ደረጃ የተቋቋሙ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅ/ሥ/ ማህበራትን በማጠናከር
የፈሩ አባላት
የፈሩ አባላት በጥቅል ቁጥር 40,000 8,000 18,00 16,815 16,815 93 93
ወንድ ቁጥር 20,000 4,000 09,000 11,220 11,220
ሴት ቁጥር 20,000 4,000 9,000 5,595 5,595
ግብ 2፡ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራትን አገልግሎት አሰጣጥ
በሚሰጡትን አገልግሎት ላይ ለአባላት ግንዛቤ እንዲፈጥሩ ለ 4 የገንዘብ ቁጠባና
ማሻሻል፣ ቁጥር 4 4 4 3 3
ብድር የኅብረት ስራ ማህበራት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ፣
75 75
ግብ 3፡- የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራትን አመራር ስርዓት ማሻሻል፣

በሥራ አመራራቸው ውስጥ የአማካሪ ባለሙያዎችን እንዲያካትቱ የገንዘብ ቁጠባና ቁጥር 2 2 2 2 2 100 100
ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራት ድጋፍና ክትትል ማድረግ
ጠቅላላ ጉባዔአቸውን በውክልና አሰራር እንዲመሩ ለ 2 የገንዘብ ቁጠባና ብድር ቁጥር 2 2 2 2 2 100 100
ኅብረት ሥራ ማህበራት ድጋፍና ክትትል ማድረግ፣

ግብ 4፡- በሪፎርም የትግበራ አሰራር የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ


ማህበራትን ማደራጀት

ቁጥር 1 0.25% 0.25 አልተጀመ


1 አገር አቀፍ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራት ፌዴሬሽን ማደራጀት % ረም

በሚቀርበው የመደራጀት ጥያቄ መሠረት በፌዴራል ደረጃ አዳዲስ የገንዘብ ቁጠባና ብድር በጅምር
ቁጥር 3 1 1 50% 50% 50
ኅብረት ሥራ ማህበር ማደራጀት

1
ግብ 5፡ የኅብረት ሥራ ማስፋፊያ አካላት እና የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ
ማህበራትን የማስፈፀም እና የመፈፀም አቅም ማሳደግ
ለክልሎች፣ ለገ/ቁ/ብ/ማ ዩኒዬኖች እና ለፌዴሬሽኖች ባለሙያዎች በአነስተኛ-ኢንሹራንስ ላይ በዙር 1 1 1 አልተከናወ
አንድ ዙር ስልጠና መስጠት፣ ነም
ለክልሎች፣ ለገ/ቁ/ብ/ኅ/ሥ/ማ ዩኒዬኖች እና ለፌዴሬሽኖች ባለሙያዎች የፋይናንስ ግብይት በዙር 1 1 1 አልተከናወ
(Financial Marketing) አንድ ዙር ስልጠና መስጠት ነም
የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማኅበራት እንዲጠቀሙበት የተዘጋጀውን ሶፍት-ዌር
ጥቅም ላይ እንዲውል ለ 50 የገ/ቁ/ብ/ኅ/ሥ/ማኅበራት ሁለት ዙር ሥልጠና መስጠት፣ በዙር 2 1 1 2 2 100 100

የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራት በሶፍትዌር አጠቃቀም ላይ ለ 50 በቁጠር 50 50 50 40 40 80 80


የገ/ቁ/ብ/ኅ/ሥ/ማኅበራት ሙያዊ ድጋፍ ማድረግ
ለፌዴራል አስፈፃሚ አካላት የፋይናንስ አገልግሎት አሰጣጥ ላይ የአሰልጣኞች ስልጠና መስጠት 1
በዙር 1 1 1 1 100

ግብ 6፡- የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራት የመረጃ አቅርቦት


ተደራሽነትን ማሳደግ
የዘርፉን ዕቅድና ሪፖርቶች ማዘጋጀት፣ በቁጥር 6 3 3 3 3 100

መሠረታዊ መረጃዎችን በማሰባሰብ፣ በመተንተንና በማደራጀት በተሟላ ሁኔታ (100%) 100 100 100 100
በመቶኛ 100 100 100
ለተጠቃሚዎች ተደራሽ ማድረግ

የክልሎች አንድ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅ/ሥ/ማ ሪፖርት ማቅረቢያ ፎርማቶችን ማሻሻል ሰነድ 1 1 1 1 1 100 100

ግብ 7፡- የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራት የቁጠባ መጠን ማሳደግ


በፌዴራል ደረጃ ለተደራጁ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራት በቢሊየን 3 1.3 1.3 1,664,317,5 1,664,317,
>100
በማጠናከር ቁጠባ እና ካፒታል ማሰባሰብ ብር 89 589
በፌዴራል ደረጃ ለተደራጁ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራት በሚሊዮን 20 9 9 7,785,488 7,785,488 85.5 85.5
በማጠናከር ከህፃናት ቁጠባ ማሰባሰብ ብር

ግብ 8፡- የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራት የብድር አቅርቦት ማሳደግ

በፌዴራል ደረጃ ለተደራጁ የገ/ቁ/ብ/ኅ/ሥ/ማህበራት በማጠናከር ያሰራጩትን የብድር መረጃ በቢሊየን 5 2,094,031,79 2,094,031,7
2.5 2.5 83.6 83.6
ማደራጀት፤ ብር 8 98

በፌደራል ደረጃ የተቋቋሙ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራት ለአባለት በመቶኛ 99.5 99.5 99.5 99 99
ከተሰራጨ ብድር ውስጥ የመመለሻ ጊዜው የደረሰ የብድር አመላለስ መረጃ ማሰባሰብና
ማደራጀት፤

2
ግብ 9፡- የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራት የአደጋ ስጋትን መቀነስ

በፌደራል ደረጃ ተቋቋሙ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራት በብር 50 25 25 57,469,708 57,469,708
>100 >100
የአነስተኛ ብድር መድህን ዋስትና አገልግሎት በመስጠት አረቦን ማሰባሰብ

ግብ 10፡- በገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራት የሚሰጠውን የወለድ


አልባ የፋይናንስ አገልግሎት ማስፋፋት፣
በፌዴራል የተደራጁ 2 የገንዘብ ቁጠባና ብድር የኅ/ሥ/ማህበራት የወለድ አልባ የፋይናንስ
በቁጥር 4 2 2 2 2
አገልግሎትን መስጠት እንዲጀምሩ ድጋፍ እና ክትትል ማድረግ፤ 100 100

በአማራ ክልል 2፣ በኦሮሚያ ክልል 4 በድምሩ 6 የገንዘብ ቁጠባና ብድር የኅ/ሥ/ማህበራት


ዩኒዬኖች የወለድ አልባ የፋይናንስ አገልግሎትን መስጠት እንዲጀምሩ ከክልሎች ጋር በጋራ በቁጥር 6 3 3 1 1
33.3 33.3
በመሆን ድጋፍ እና ክትትል ማድረግ፤

የወለድ አልባ የፋይናንስ አገልግሎት የሚሰጡ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅ/ሥ/ማህበራትን በቁጥር 40 20 20 11 11
55 55
ማጠናከር እና ለክልሎች ድጋፋዊ ክትትል ማድረግ፤
ለወለድ አልባ የብድር አገልግሎት የሚውል ተዘዋዋሪ ፈንድ የሚያቀርቡ እና ለዘርፉ ሌሎች
ድጋፎችን የሚያደርጉ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን፣ ፕሮጀክቶችንና
ሰነድ 1 1 1 0 0
ፕሮግራሞችን መለየት አንድ ሰነድ ማዘጋጀት፤ 0 0

ግብ 11፡- በገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራት የሴቶችን እና ወጣቶችን


ተጠቃሚነት ማሳደግ
በፌዴራል ደረጃ የተደራጁ 4 የገ/ቁ/ብ/ኅ/ሥራ ማህበራት የሴቶችን ተሳትፎ በአባልነት
በቁጥር 4 4 4 3 3
20,000፣ በአመራርነት 13 እና 2 ቢሊዮን ብር ብድር ለሴቶች በመስጠት ተጠቃሚ 75 75
እንዲያሳድጉ ድጋፍ እና ክትትል ማድረግ፣
በፌዴራል ደረጃ ከየተደራጁ 4 የገ/ቁ/ብ/ኅ/ሥራ ማህበራትን በማጠናከር የወጣቶችን ተሳትፎ በቁጥር 4 4 4 3 3
75 75
በአባልነት 8,000፣ ድጋፍ እና ክትትል ማድረግ
ግብ 12፡- የበጀት አጠቃቀም ውጤታማነትን ማሳደግ
ለፋይናንስ ኅብረት ሥራ ልማት መሪ ሥራ አስፈፃሚ የተመደበ መደበኛ በጀትን ውጤታማ 100 100 100 100
በሆነ መንገድ ሙሉ በሙሉ 100% መጠቀም፤ በመቶኛ

በፕሮግራሞችና ፕሮጀክት ለዘርፉ የተመደበ በጀትን ውጤታማ በሆነ መንገድ ሙሉ በሙሉ 100 100 100 100
100% መጠቀም፤ በመቶኛ

3
ግብ 13፡- የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራት የዲጂታል ኢኮኖሚ
ትግበራን ማሳደግ

በፌደራል የተደራጁ 3 የገ/ቁ/ብ/ ኅ/ሥራ ማህበራት የዲጂታል ኢኮኖሚ ትግበራ ውስጥ 3 3 3 1


1
ማስገባት፤ በቁጥር 33.3 33.3

በፌደራል የተደራጁ 3 የገ/ቁ/ብ/ ኅ/ሥራ ማህበራት የፋይናንስ መረጃ ቋት እና ዘመናዊ የሂሳብ 3 3 3 1


1
አያያዝ ትግበራ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ድጋፍ ማድረግ፣ በቁጠር 33.3 33.3

የገ/ብ/ቁ/ኅ/ሥ/ ማህበራት ወኪል የኢ-ብር/ኤሌክትሮኒክ የፋይናንስ አገልግሎት ለማስጀመር 1 1 1 አልተከናወ


መረጃ በማሰባሰብና በማደራጀት አንድ ሰነድ ማዘጋጀት በቁጥር ነም

የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራት ላይ ተዘርግቶ የነበረውና የተሻሻለውን 50 50 50 አልተከናወ


software ለ50 ለገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራት መጫን፤ ነም
በቁጥር

ግብ 14፡- በገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራት የስራ እድል ፈጠራን


ማሳደግ
በፌደራል ደረጃ የተመዘገቡ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራት 400 ሰዎች የሥራ 400 200 200
ዕድል እንዲፈጥሩ መደገፍ በቁጥር

ግብ 15፡- የገ/ቁ/ብድር ኅ/ሥራ ማህበራት አሰራር ስርዓት ማሻሻል፣


አንድ የገ/ቁ/ብድር ኅ/ሥራ ማህበራት የፋይናንስ አገልግሎት አሰጣጥ መመሪያ 1 1 1 1 1
ማጠናቀቅ በቁጥር 100 100

በአገር አቀፍ ደረጃ ለሚቋቋም የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራት 1 1 1 0 0 አልተከናወ
በቁጥር 0 0
ፌዴሬሽን ቅድመ-ሁኔታ ጥናት ማካሄድ፣ ነም
የዓይነት ቁጠባ በሚያካሂዱ ኅብረት ሥራ ማህበራት ላይ የዳሰሳ ጥናት በማድረግ አንድ ሰነድ 1 1 1 0 0 አልተከናወ
ማዘጋጀት በሰነድ 0 0
ነም
አንድ የፋይናንስ አገልግሎት ውጤታማነት መገምገሚያ እና መመዝገቢያ ማኑዋል 1 1 1 አልተከናወ
ማዘጋጀት ሰነድ ነም
የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራት ህጋዊ ሰውነት እድሳት ማስፈጸሚያ 1 1 1 1 1
አንድ ማኑዋል ማዘጋጀት ሰነድ 100 100

የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራት አንድ የውህደት አሰራር ማዘጋጀት፤ 1 1 1 1 1


ሰነድ 100 100
ግብ 16፡- ቅንጅታዊ አሰራርን ማሳደግ
በፋይናንስ ግብይት ትስስር ላይ ወርክ ሾፕ ማካሄድ እና የተሞክሮ ልውውጥ አንድ ዙር በዙር 1 1 1 0 0
0 0
ማዘጋጀት፣

4
አለማቀፍ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅ/ሥ/ማ አመታዊ በዓል አንድ ዙር ማክበር በዙር 1 1 1 1 1
100 100

ከክልል የዘርፉ አስፈፃሚ አካላት ጋር ሥራዎችን በጋራና በትብብር ለመስራት እንዲቻል በበጀት በዙር 2 1 1 0 0
ዓመቱ 2 የጋራ ምክክር መድረክ ማካሄድ፤
ከሌሎች የሥራ ክፍሎች ጋር ለመስራት የሚያስችል የጋራ ዕቅድ ማዘጋት በቁጥር 1 1 1 100 100

You might also like