Professional Documents
Culture Documents
TVET Cooperative Training Regulation ( )
TVET Cooperative Training Regulation ( )
መግቢያ
የውጤት ተኮር የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና በባህሪው በጣም ትላልቅ እና ውድ ማሽኖችን የሚሹ በመሆኑ
በማሰልጠኛ ተቋማት ውስጥ ብቻ ስልጠናውን በመሸፈን ጥራቱን የጠበቀ ስልጠና መስጠት ባለመቻሉ 30%ቱ ሙያ ነክ
ንደፈ ሃሰብ ማስጨበጫ ስልጠና እና የተግባር ስልጠና እጅ ማፍታቻ ልምምድ በማሰልጠኛ ተቋማት ውስጥ
በመስጠት፣70%ቱ ደግሞ የተግባር ስልጠና በልማት ድርጅቶች ውስጥ በትብብር ስልጠና የሚሸፈን ሆኖ የስልጠናውን
ጥራት ለማስጠበቅ ጉልህ ሚና እንደሚኖረው በመታመኑ፣
በተጨማሪ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ስርዓት ዋንኛው ዓላማ ለሁሉም ትኩረት ዘርፎች እና ለልማት ድርጅቶች
በመካካለኛ እና በዝቅተኛ ደረጃ ብቁ የሰው ሃይል ማፍራት ሲሆን የልማት ድርጅቶች ስልጠናው ላይ በመሳተፍ በቂ የሰው
ሃይል በማፍራት ረገድ የራሳቸውን ድርሻ መወጣት አለባቸው፡፡ ከሁሉም በላይ ሰልጣኞች በልማት ድርጅት ውስጥ ሲሰለጥኑ
እውነተኛ የስራ ቦታ በመሆኑ ለስራው የሚያስፈልገው እዉቀት፣ክህሎት እና አመለካከት በቀላሉ ሊቀስሙት የሚችሉበትን
እድል ስለሚፈጥር ተመራጭ ስለሚያድርገው ይህንን ተግባር በተገቢው ለመፈጸም የአሰራር ስርዓት መዘርጋት አስፈላጊ
በመሆኑ ይህንን መመሪያ ማውጣት አስፈልጓል፡፡
ክፍል አንድ
ጠቅላላ
1. አጭር ርዕስ
ይህ መመሪያ 'የፌዴራል የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና የትብብር ስልጠና መመሪያ' ተብሎ ሊጠቀስ ይችላል፡፡
2. ትርጓሜ
1. ‘የትብብር ስልጠና' ማለት ማሰልጠኛ ተቋማትና የልማት ድርጅቶች በትብብር የሚሰጡት የስልጠና ዘዴ ነው፡፡
2. ‘የልማት ድርጅት' ማለት በትብብር ስልጠና ማእቀፍ የሚሳተፍ ምርት ወይም አገልግሎት ለመስጠት በመንግስት፣
መንግስታዊ ባልሆነ አካል ወይም በግል የተቋቋመ ድርጅት ሆኖ ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዝንም
ይጨምራል፡፡
3. ‘ኤጀንሲ' ማለት የፌዴራል ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ኤጀንሲ ነው፡፡
4. 'ማሰልጠኛ ተቋም' ማለት የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና በመስጠት ላይ የተሰማራ በፌዴራል ደረጃ
የሚቋቋም ስልጠና ሰጪ ተቋም ነው፡፡
5. ‘የማሰልጠኛ ውስጥ አሰልጣኝ' ማለት በማሰልጠኛ ተቋም ውስጥ በማሰልጠን ስራ የተሰማራ ሰው ነው፡፡
6. ‘የልማት ድርጅት ውስጥ አሰልጣኝ' ማለት በልማት ድርጅት ውስጥ የሚሰራ ባለሙያ ተመዝኖ ብቁ በመሆን
የማሰልጠን ስነ ዘዴ ወስዶ በትብብር ስልጠና ሰልጣኞችን የሚያሰለጥን ሰው ነው፡፡
1
7. ‘ሰልጣኝ' ማለት ሙያ ለመቅሰም ወይም ያለውን ችሎታ ለማዳበር ሲል በፌዴራል መንግስት የሚተዳደሩ
ማሰልጠኛ ተቋሞችና በልማት ድርጅቶች ትብብር በሚሰጥ የስልጠና መርሃ ግብር ውስጥ ስልጠና የሚከታተል
ግለሰብ ነው።
8. ‘የሙያ ብቃት ምስክር ወረቀት' ማለት በኤጀንሲው ስም በብቃት ማዕከላት የሚሰጥ ብሄራዊ የምስክር ወረቀት
ሲሆን የሰነዱ ባለቤት በሙያ ብቃት ምዘና ሥርዓት ተመዝኖ ብቃቱ የተረጋገጠ መሆኑን የሚያስረዳ ሰነድ ነው፤
9. ‘የሙያ ደረጃ' ማለት በሥራ ዓለም በሚገኙ ሙያተኞች የሚዘጋጅ የሙያ ደረጃ ሲሆን ሰዎች በሥራ ዓለም
ውጤታማ ይሆኑ ዘንድ ሊኖራቸው የሚገባውን ብቃት የሚያመለክት ነው፡
10. ‘የሙያ ብቃት ምዘና ማለት በትብብር ስልጠና ወቅት ተገቢውን የሙያ ብቃት ላይ የደረሰ ስለመሆኑ
የማረጋጥ ሂደት ነው፡፡
11. ‘ብቃት አሃድ ማለት የተወሰነ ስራ ለማከናወን ለስራ ቦታ የሚገባውን ክህሎት፣ እውቀት እና አመለካከት
የያዘና መተግበር የሚያስችል ነው ፡፡
12. 'ኢንዱስትሪ' ማለት የሙያ ብቃት ምዘና መስጫ ማዕከል በመሆን ሙያ ብቃት ምዘና ላይ የሚሳተፉ
ምርት ወይም አገልግሎት ለመስጠት በመንግስት ፣መንግስታዊ ባልሆኑ አካል ወይም በግል የተቋቋመ ድርጅት ሆኖ
ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፐራይዞች ይጨምራል፤
13. 'የሥራ አመራር ቦርድ' ማለት በፌዴራል ደረጃ የሚቋቋም ማሰልጠኛ ተቋማት በበላይነት የሚመራ አካል
ነው፤
14. በማንኛውም በወንድ ፆታ የተገለጸው አገላለጽ ሴትንም ይጨምራል፡፡
3. የተፈፃሚነት ወሰን
ይህ መመሪያ በማንኛውም ' የልማት ድርጅት ' እና ' በፌዴራል ደረጃ የተቋቋሙ ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና
ማሰልጠኛ ተቋማት' እንዲሁም ሰልጣኞች ላይ ተፈፃሚነት ይኖረዋል፡፡
4. ዓላማ
በፌዴራል መንግስት የተቋቋሙ ማስልጠኛ ተቋማት እና በልማት ድርጅቶች ውስጥ የሚካሄደውን ትብብር ስልጠና
በተቀናጀና ጥራቱን በጠበቀ መንገድ እንዲመራ ለማድረግ የአስራር ስርዓት ለመዘርጋት በማስፈለጉ ይህ መመሪያ
ተዘጋጅቷል፡፡
ክፍል ሁለት
የትብብር ስልጠና ስረዓት ሂደት
5. የትብብር ስልጠና ደረጀዎች
2
የትብብር ስልጠና አንዱ የውጤት ተኮር ስልጠና አሰጣጥ ሥነ ዘዴ ሲሆን የሚካሄደው በማስልጠኛ ተቋም እና በልማት
ድርጅት መካከል ነው፤ትብብር ስልጠናን ውጤታማ ለማድረግ የሚከተሉትን ቅድመተከተል ጠብቆ ማስኬድ
ያስፈልጋል፤
1. በማሰልጠኛ ተቋም ውስጥ የሚሰጡ ሙያና ደረጃ መሠረት ለትብብር ስልጠና የሚሆኑ ልማት ድርጅቶችን
መለየት፣ማጥናት፣መምረጥ፤
2. የትብብር ስልጠና የጋራ እቅድ ማቀድ፤
3. ትብብር ስልጠና ለማከሄድ እና ውጤታማ ለማድረግ በማስልጠኛ ተቋም እና በልማት ድርጅት መካከል መግባቢያ
ስምምነት ሰነድ መፈራረም ፤
4. በተቋም እና በልማት ድርጅት ውስጥ ትብብር ሥልጠና የሚሰጥባቸውን ቦታዎችን ማዘጋጀት፤
5. ስልጠና የሚሰጡ የማሰልጠኛ ተቋማት እና የኢንዱስትሪ ውስጥ አሰልጣኞችን መመደብ፤
6. በእቅዱ መሠረት ስልጠናውን መስጠት፤
7. የሥልጠናውን ሂደት መከታተል/በትብብር ሥልጠና ቦታዎች ላይ በመገኘት ቁጥጥር ማድረግ፤
8. የሰለጠኑበትን ብቃት አሃድ ወይም ደረጃ ላይ ሙያ ብቃት ምዘና ማከናወን፤
9. የትብብር ስልጠና እና የምዘና ውጤት ሪፖርት ማድረግ፤
ክፍል ሦሥት
የሚመለከታቸው አካላት ተግባር እና ኃላፊነት
5
1. የትብበር ስልጠና ስራን በጋራ ለመስራት ከፌዴራል ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ ጋር
የስምምነት ሰነድ መፈራረም፤
2. የትብበር ስልጠናን ስራ አፈጻጸምን በተመለከተ የጋራ እቅድ ማቀድ፤
3. ከፌዴራል ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ ጋር በመተባባር ለልማት ድርጅቶች ትብብር ስልጠና
ላይ ግንዛቤ ማስጨበጫ ስራ መስራት ይኖርበታል፡፡
7
ክፍል አራት
የዲሲፕሊን አፈጻጸምና የቅሬታ አቀራረብ ስነስርአት
24. ዲሲፕሊን
1. ሰልጣኞች በተመለከተ
1.1. ለአንድ አመት ከስልጠና የሚያሳግድ የዲሲፕሊን ግድፈት
ሀ. ማንኛውንም የሥራ ሚስጥር አለመጠበቅ ፣
ለ. በትብብር ስልጠና ቦታ አምባጓሮ መፍጠር፣
ሐ. ሆን ብሎ የመሰልጠኛውን መሳሪያ ለጥፋት የዳረገ ፣የሰረቀና ያሰረቀ
1. በስልጠና ወቅት የሚቀርቡ ማንኛውም ቅሬታ ቅሬታው በተፈጠረ በ 5 ቀናት ውስጥ መቅረብ ያለበት ሆኖ
ቅሬታው የሚስተናገደው የትብብር ስልጣና በሚሰጥበት የልማት ድርጅት ይሆናል፡፡
2. በዚህ አንቀጽ ንኡስ አንቀጽ 1 የተጠቀሰው እንደተጠበቀ ሆኖ ቅሬታው የቀረበለት የልማት ድርጀት በዚህ
መመሪያ መሰረት በ 5 ቀን ባልበለጠ ጊዜ ተገቢውን ምላሽ መስጠት አለበት ፡፡
3. ነገርግን የቀረበው ጉዳይ ከአቅሙ በላይ ከሆነና የቀረበው ቅሬታ አግባብነት ያለው ከሆነ ቅሬታውን ወደ
ማሰልጠኛ ተቋም በማቅረብ ጉዳዩን ተከታትሎ የመጨረሻውን ውጤት ለቅሬታ አቅራቢው በ 10 ቀናት ውስጥ
ማሳወቅ አለበት፡፡
8
4. ቅሬታ አቅራቢው በልማት ድረጅቱ የተሰጠው ምላሽ ያላረካው ከሆነ በቀጥታ ለማሰልጠኛ ተቋሙ ማቅረብ
የሚችል ሆኖ ማሰልጠኛ ተቋሙ ቅሬታውን መርምሮ በ 5 ቀን ውስጥ ውሳኔውን ለቅሬታ አቅራቢው ማሳወቅ
ይኖርበታል፡፡
5. በውሳኔው አጥጋቢ መልስ ካላገኘ ቅሬታውን እስከ 10 ቀናት ለስራ አመራር ቦርድ ማቅረብ አለበት፣ ለስራ
አመራር ቦርዱ የቀረበለትን ቅሬታ በ 30 ቀናት ውስጥ ውሳኔ ይሰጣል ፣ ውሳኔ የመጨረሻ ይሆናል፡፡
ክፍል አምስት
ልዩልዩ ድንጋጌዎች