You are on page 1of 4

የፌደራል ዋና ኦዲተር መ/ቤት 2010

የኦዲት ማስታወሻ

ኦዲት ተደራጊው መ/ቤት ፡ ኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ

ኦዲት የሚደረገው ሂሳብ በጀት ዓመት፡- 2010

ኦዲት ሥም የኃላፊነት ደረጃ ቀን ፊርማ

ያዘጋጀው እንዳለ ወ/ጊዮርጊስ ኦዲተር 03/11/10

የከለሰው ሰኢድ አ/ቃድር ከፍተኛ ኦዲተር 05/11/10

የከለሰው ሲሳይ ተክሉ የኦዲት ስራ አስኪያጅ

የከለሰው ሰይፉ ከበደ የኦዲት ዳይሬክተር

ለአቶ ሀይሉ ታደሰ የፋይናንስ ግዥና ንብረት አስተዳደር ዳሬክተር


ማስታወሻው የተሰጠበት ቀን፡- 06/11/10

የኦዲት ማስታወሻ ቁጥር፡- 16

የኦዲት ማስታወሻው አርዕስት ፡- ከመደበኛ በጀት ለካፒታል በጀት የተከፈለ

የሂሣቡ መደብ ፡- 6244

የገንዘብ መጠን ፡- 1,053,535.11

የሂሳቡ ዝርዝር ሁኔታ፡- ለግንባታ ከመደበኛ በጀት ለካፒታል በጀት ተከፍሎ የተገኘ

የግኝቱ መግለጫ

 የፌዴራል መንግስት የፋይናንስ ኃላፊነት መመሪያ ቁጥር 6/2003 ክፍል ሁለት የፋይናንስ ኃላፊነት የመንግስት
መ/ቤቶች የበላይ ኃላፊዎች ቁጥር 6(ለ) የፋይናንስ አስተዳደር አዋጅ እንዲሁም አዋጁን ለማስፈፀም በወጣው
የፋይናንስ አስተዳደር ደንብ ላይ በመመርኮዝ የወጡት መመሪያዎች በመ/ቤቱ ውስጥ በተሟላና ተገቢ በሆነ መንገድ ሥራ
ላይ መዋላቸውን በማረጋገጥ ረገድ ላይ ተጠያቂነት እንዳለባቸው ይገልፃል :: የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር
190/2002 ስለፌዴራል መንግስት የፋይናስ አስተዳደር የወጣ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ክፍል ሦስት
የመንግስት ገንዘብ ክፍያ አንቀጽ 12 የመንግስት ገንዘብ ክፍያ ሊፈፀም ወይም ወጪ ሊደረግ የሚችለው የተፈቀደ
በጀት ሲኖር ብቻ እንደሆነ ይገልጻል ፡፡ ይሁን እንጂ ዩኒቨርሲቲው ለካፒታል የተፈቀደ በጀት ሳይኖር በተለያየ ቀን
ለተለያዩ ፕሮጀክት በድምሩ ብር 1,053,535.11 ከመደበኛ በጀት ተከፍሎ ተገኝቷል፤ ዝርዝሩ እንደሚከተለው
ቀርቧል፡፡
 በቀን 15/03/10 በባንክ ወጪ ማስመስከሪያ ቁጥር 477468 በሂሳብ መደብ 6244 ብር 188,392.98 ከአዲሱ
አበራ ጠቅላላ ስራ ተቋራጭ ውል በመግባት ለአራት ሽንት ቤት እና ሻወር ቤት ግንባታ በሚል ከመደበኛ በጀት ለካፒታል
በጀት የተከፈለ መሆኑ
 በቀን 9/4/10 በባንክ ወጪ ማስመስከሪያ ቁጥር 477653 በሂሳብ መደብ 6244 ብር 408,590.03 ከአዳነች እና
እዮብ ውል በመግባት የፊኒሽንግ ስራ በሚል ከመደበኛ በጀት ለካፒታል በጀት የተከፈለ መሆኑ

AQ Page 1
የፌደራል ዋና ኦዲተር መ/ቤት 2010

 በቀን 08/04/10 በባንክ ወጪ ማስመስከሪያ ቁጥር 477645 በሂሳብ መደብ 6244 ብር 176,433.92 ከአዲሱ
አበራ ጠቅላላ ስራ ተቋራጭ ውል በመግባት ለአራት ሽንት ቤት እና ሻወር ቤት ግንባታ በሚል ከመደበኛ በጀት ለካፒታል
በጀት የተከፈለ መሆኑ
 በቀን 22/03/10 በባንክ ወጪ ማስመስከሪያ ቁጥር 477536 በሂሳብ መደብ 6244 ብር 208,804.04 ከአዳነች እና
እዮብ ውል በመግባት የፊኒሽንግ ስራ በሚል ከመደበኛ በጀት ለካፒታል በጀት የተከፈለ መሆኑ
 በቀን 06/04/10 በባንክ ወጪ ማስመስከሪያ ቁጥር 477646 በሂሳብ መደብ 6244 ብር 71,314.14 ከአዲሱ አበራ
ጠቅላላ ስራ ተቋራጭ ውል በመግባት ለአራት ሽንት ቤት እና ሻወር ቤት ግንባታ በሚል ከመደበኛ በጀት ለካፒታል በጀት

ተብሎ በአጠቃላይ በድምሩ ብር 1,053,535.11 ተከፍሎ የተገኘ መሆኑ በኦዲት ወቅት ተረጋግጧል።
 ወጪው ብር 1,053,535.11 በሂሳብ መደብ 6324 መመዝገብ ሲገባው በሂሳብ መደብ 6244 ተመዝግቦ ሪፖርት

የተደረገ መሆኑ ታውቋል።

ስጋት

የመንግስትን በጀት ከደንብና መመሪያ ወጪ መጠቀም የመንግስት መመሪያን ከመጣሱም በላይ ለምዝበራና ለብክነት
ሊያጋልጥ ይችላል ፡፡

ደንብና መመሪያ ተፈጻሚ እንዳይሆን ከማድረጉ በተጨማሪ የሂሳቡን ትክክለኛ ገጽታ እንዳያሳይ ሊያረግ ይችላል፡፡

የበጀት አጠቃቀም ላይ አሉታዊ ተጽኖ ሊያመጣ ይችላል፡፡

በፋይናንስ ግዥና ንብረት አስተዳደር ዳሬክተር መወሰድ ያለበት የማሻሻያ እርምጃ፤

ወደፊት መሰል ተግባር እንዳከሰት ተገቢውን ጥንቃቄና ክትትል ሊወሰድበት ይገባል፡፡

የከፍተኛ ኦዲተሩ ፊርማ --------------------

የኦዲት ማስታወሻው መመለስ ያለበት ጊዜ፡-----

የፋይናንስ ግዥና ንብረት አስተዳደር ዳሬክተር ምላሽ፣

AQ Page 2
የፌደራል ዋና ኦዲተር መ/ቤት 2010

የፋይናንስ ግዥና ንብረት አስተዳደር ዳሬክተር

ፊርማ ----------------

ቀን ፡- --------------------

የኦዲተሩ አስተያየት፣

ፊርማ ----------------

ቀን ፡- --------------------

AQ Page 3
የፌደራል ዋና ኦዲተር መ/ቤት 2010

AQ Page 4

You might also like