You are on page 1of 5

የተሰብሳቢ ስም

1. አቶ ትንሳኤ ይማም ፡-ዋና ስራ አስኪያጅ ሰብሳቢ


2. አቶ ሲሳይ አስፋው፡- ፋይናንስና አስተዳደር አገልግሎት ኃላፊ
3. አቶ ዳንኤል ታደሰ፡- ከፍተኛ የውስጥ ኦዲት ባለሙያ
4. አቶ አዱኛው ዘውዱ ፡- የፋይናንስ ባለሙያ
5. የስብሰባ ቀን:- 22/06/2015 ዓ.ም
የመውጪያ ስብሰባው አላማ፡-

 በኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን የቦሌ ለሚ ኢንዱስትሪ ፓርክ የ 2014 በጀት አመት ሂሳብ ኦዲት

ሲደረግ በተገኙት የውስጥ ቁጥጥር ድክመቶች ሌሎች ግድፈቶችን ለኢንዱስትሪ ፓርኩ ስራ አስኪያጅ ግንዛቤ

እንዲያገኙ ማድረግ፡፡

 በኦዲቱ ወቅት ግልጽ ያልተደረጉ ጉዳዮች ቢኖሩ ማብራሪያ እንዲሰጥባቸውና ያልቀረቡ ማስረጃዎችና ሰነዶች

ካሉ እንዲቀርቡ ማድረግ እና

 የኢንዱስትሪ ፓርኩ ስራ አስኪያጅ በቀጣይ ሊወሰዱ ስለሚገባው እርምጃ ግንዛቤ መፍጠር፡፡

የ 2014 4 ኛ ሩብ አመት የኦዲት ግኝቶች

1. በ BPV ቁጥር 20630 የሰልዳ ቁጥር ኮድ 3 - 54532 ET ተሸከርካሪ ጥገና እንዲጠገን ትእዛዝ የተሰጠበት
ጥገና እንደሚአስፈልግው የተጠየቀበት እና የክፍያ ትዕዛዝ የተሰጠበት ደብባቤ ሳይያያዙ ክፍያው ተከፍሎ ከላይ

በተጠቀስው BPV ቁጥር በቀን 23/04/2022 ብር 44,999.91 /አርባ አራት ሽህ ዘጠኝ መቶ ዘጠና ዘጠኝ ብር

ከ 91/100 / ክፍያ ተከፍሎና ተወራርዶ መገኘቱ በተደረገው ኦዲት ለማረጋገጥ ተችሏል፡፡

ከስራ ክፍሉ የተሰጠ ምላሽ :- ደብዳቤው ኮፒ ተያይዟል፡፡

ማኔጅመንቱ የሰጠው ሃሳብ ፡- የተሸከርካሪዎች ጥገና ሲደረጉ የጥገና አገልግሎት የሰጠው ድርጅት ጥገናዎችን
ሲአጠናቅቁ የክፍያ ጥያቄ በመጠየቅና የፋይናነስና አስተዳደር አገልግሎት ክፍል ጥያቄ ለተቋሙ የበላይ ኃላፊ
በማስፈቀድ ክፍያዎች እንዲከፈሉ፡፡ለክፍያውም አስፈላጊ የሚባሉ አስረጅ (ደጋፊ) ማስረጃዎችም
ተደራጅተው ከክፍያ ሰነዱ ጋር እንዲያያዙ ውሳኔ ተሰጥቶበታል፡፡
2. በቀን 09/06/2022 BPV ቁጥር 20680 ለተሸከርካሪ ፍላጎት በተቀመጠው Specification መሰረት ግዥ
ያልተፈጸመ መሆኑን ኢንዱስትሪ ፓርኩ ከ 2005 ሞዴል በላይ ግዥ እንዲፈጸም ፍላጎት ያለው ቢሆንም

ግዥው ከ 2003 ሞዴል በላይ ግዥ የተፈጸመ መሆኑን በተደረገው ኦዲት ለማረጋገጥ ተችሏል፡፡

በየካቲት 21/2014 በቁጥር ቦለኢፓ/002/128 በተሰበሰበው ፕሮፎርማ ለችግኝ መፍያ የሚአስፈልጉ

ግብአቶች በተሰበሰበው የዋጋ ማወዳደሪያ መሰረት በተራ ቁጥር 3 ላይ 96M3 Compost በቀረቡት ዋጋ
መሰረት ወንደሰን ከድርና ጓደኞቹ የጭግኝ ማፍሊያና ገጸ ምድር ህ/ስ/ማ ዝቅተኛ ዋጋ ያቀረቡ ቢሆንም በየነ

ሃብታሙና ጓደኞቹ የጭግኝ ማፍሊያና ገጸ ምድር ህ/ስ/ማ አሸናፊ እንዲሆኑ በማድረግ ኢንዱስትሪ ፓርኩ ብር

10,500 /አስር ሽህ አምስት መቶ/ በብልጫ ክፍያ የተከፈል መሆኑን በ BPV ቁጥር 20621 በቀን
18/04/2022 ክፍያ የተከፈለና የተወራረደ መሆኑን በተደረገው ኦዲት ለማረጋገጥ ተችሏል፡፡
ከስራ ክፍሉ የተሰጠ ምላሽ፡- በመጠይቁ ላይ በቃለ ጉባኤው የተሰራው በ 2005 እና ከዚያ በላይ በሚል ሲሆን

በስህተት በጅርጅቱ በኩል በ 2003 እና ከዚያ በላይ በሚል የተያያዘ በመሆኑ ነው፡፡ የዋጋ ውድድር የተደረገው

በአጠቃላይ የሚቀርቡት ዋጋ ስሌት በመሆኑ እና በተናጠል የማይንቀሳቀስ በመሆናቸው የጠቅላላ ዋጋ ቅናሽ

ያለውን ድርጅት ከአንድ ቦታ ግዥው እንዲፈጸም ተደርጓል፡፡

ማኔጅመንቱ የሰጠው ሃሳብ ፡- ኢንዱስትሪ ፓርኩ ባዘጋጀው ስፔስፊኬሽን መሰረት ስለመገዛቱ የሚአስረዱ

ማስረጃዎች በተገቢው መንገድ እየተደራጁ ክፍያዎች እንዲከፈሉ እና የፕሮፎርማ ግዥ ሲደረግ ኮሚቴዎች

ጥንቃቄ እንዲአደርጉ፡፡ የፕሮፎርማ ግዥ ሲከናወን ግዥው የሚፈጸመው በተናጠል ወይም በጥቅል

በሚአቀርቡት ዋጋ መሆኑን በሚገልጽ መልኩ እንዲሆን በተያያዘ መልኩ ማስረጃዎችንም በማደራጀት ከክፍያ

ሰነዱ ጋር ይያያዝ፡፡

3. በ BPV ቁጥር 20719 እና 20718 የአመት ፈቃድ ወደ ገንዘብ እንዲቀየር በተወሰነው መሰረት የአመት ፈቃድ
ወደ ገንዘብ ሲቀየር መንግስት ባስቀመጠው አሰላልን መሰረት ባለደረገ መልኩ ለመንግስት ገቢ መደረግ የነበረበት

የስራ ግብር ብር 1,500 ለእያንዳንዱ በድምሩ ብር 3,000 / ሶስት ሽህ ብር ከተጣራ ክፍያ ጋር ተደምሮ

የተከፈለ መሆኑን በተደረገው ኦዲት ለማረጋገጥ ተችለዋል፡፡

ከስራ ክፍሉ የተሰጠ ምላሽ፡- በሁለቱም የክፍያ ሰነዶች ላይ የስራ ግብር የተሰላው ከጠቅላላ ተከፋይ ሂሳብ ላይ
በመሆኑ ትክክለኛ ስሌት መሆኑን አረጋግጠናል ነገር ግን ገቢዎች የወጣ የአመት ፈቃድ ስሌት የተለየ በመሆኑ
በዚሁ እንዲስተካከል በሚሰራበት ወቅት ብር 48.58 ከአቶ ሲሳይ ብር 70.46 ከአቶ ትንሳኤ እላፊ ተከፍሏል
ይህም ገቢ እንዲደረግ ተደርጓል፡፡
ማኔጅመንቱ የሰጠው ሃሳብ ፡- አሰራሩ ከዋናው መስሪያ ቤት ጋር በማነጻጸር እንዲሁም የአመት ፈቃድ ወደ
ገንዘብ ሲቀየር የመንግስት መመሪያን መሰረት ባደረገ መልኩ መሆኑን መከናወኑንና መከፈሉን በጥልቀት
በመመርመር የአሰራር ጥሰት ካለው ገንዘቡ ተመላሽ ይደረግ፡፡
4. በ BPV ቁጥር 20640 በቀን 29/04/2020 የኢትዮጵያ ጎማ ቁጠባ ስራ ሃ/የተ/የግ/ ማህበር ብቸኛ አቅራቢ
መሆኑ ባልተረጋገጠበት መልኩና ማህበሩ በ 2014 በጀተ አመት የንግድ ፈቃድ ባልታደሰ መልኩ ግዥው

የተከናወነ መሆኑን በተደረገው ኦዲት ለማረጋገጥ ተችሏል ፡፡


ከስራ ክፍሉ የተሰጠ ምላሽ፡- የቀጥታ ግዠ የረበር ኩፕሊንት ሲል የሚሰራ ብቸኛ የጎማ አምራች ድርጅት

ከሆነው ከኢትጵያ ጎማ ቁጠባ በመሆኑ እና ከ 10,000 ብር በታች በመሆኑ በቀጥታ ግዥ የተስተናገደ ሲሆን

የግዠ ኤክስፐርቶች ሌላ ድርጅት አለማግኘታቸውን በጹሁፍ አቅርበዋል፡፡

ማኔጅመንቱ የሰጠው ሃሳብ ፡- አቅራቢ ድርጅቱ የመንግስት የልማት ድርጅት ሲሆን የንግድ ፈቃዱ ያልታደሰ
መሆኑን የሚአረጋግጥ ማስረጃዎች ተመርምረው ቀጣይ የሚከናወኑ ግዥዎች ላይ በጥንቃቄ ይከናወኑ ፡፡
5. ኢንዱስትሪ ፓርኩ ከሃዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ የሚመጡትን ስላጅ የኢንዱስትሪ ፓርኩ የፋሳሽ ማጣሪያ

ማእከል ከሃዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ የሚመጡትን ስላጅ ዝርዝር መረጃ ሪፖርት አለማድረግና ከሃዋሳ ኢ/ፓ

የላኩትን ደብዳቤ ከሰነዱ ጋር የማይያያዝ መሆኑን በተደረገው ኦዲት ለማረጋገጥ ተችሏል፡፡

ከስራ ክፍሉ የተሰጠ ምላሽ፡- ከሐዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ በየጊዜው የሚጻፍ ደብዳቤ የለም ሆኖም ለዚህ

ማስረጃ ከጉሙሩክ የሚላክ የመኪናውን የጭነት ልክ በኪሎ ግራም ተመዝኖና ተረጋግጦ ሁለት ኮፒ ይላካል

በፓርኩ በኩል አንድ ኮፒ ቀሪ ሆኖ ሌላው መድረሱን አረጋግጠን ለማወራረድ ለሐዋሳ ይላካል፡፡

ማኔጅመንቱ የሰጠው ሃሳብ ፡- ከሐዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ የሚመጡ ስላጆች በጥንቃቄ ማስረጃዎች
እንዲያያዙና ከዚህ ጋር ተያይዞ የሚመጡ ማንኛውም ወጪ የሐዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ እንዲሸፍን ጥብቅ
ቁጥጥርና ክትትል ይደረግ፡፡

6. በ 2014 በጀተ አመት የበጀት አጠቃቀም በተመለከተ በቅርንጫፍ ኢንዱስትሪ ፓርኩ 68.54% በጀት
የተጠቀምን ሲሆን ያልተጠቀምንበት በጀት 31.46 % መሆኑን በወርሃዊ ሪፖርት ለማረጋገጥ ተችሏል፡፡

በዝርዝር

በጀት ወራቶች አፈጻጸም %


49,866,030.67 ሐምሌ 1,556,240.43
41,662,249.00 ነሐሴ 2,672,037.45
45,035,545.43 መስከረም 2,690,775.73
ጥቅምት 1,771,938.13
ህዳር 1,772,813.71
ታህሳስ 2,151,106.99
ጥር 2,104,531.35
የካቲት 1,525,907.63
መጋቢት 2,788,654.83
ሚያዝያ 4,209,620.89
ግንቦት 1,906,055.27
ሰኔ 5,715,461.04
ጠቅላላ ድምር 30,865,143.45 68.54 %
ያልተጠቀምንበት በጀት በ ፐርሰንት 31.46 %
ከስራ ክፍሉ የተሰጠ ምላሽ፡- ያልተጠቀምነው በጀት በተለይ በእቃዎች ግዥ በአገልግሎት ክፍያዎች እልባት አለማግኘት

ለምሳሌም የጥበቃ ድርጅት ክፍያዎች የጥገና ስራዎች ላይ ግዥዎች አለመከናወናቸው ይህም የግልጽ ጨረታ ተከፋይ

አለማግነኘቱና ተሳታፊዎች አለመቅረባቸው ግዥው ውጤታማ እንዳይሆን በመደረጉ ነው፡፡

ማኔጅመንቱ የሰጠው ሃሳብ ፡- በ 2015 ያለን የበጀት አጠቃቀም ስኬታማ እንዲሆን እንዲሰራ አስተያየት የተሰጠ ሲሆን
የ 2014 በጅ አጠቃቀም ያጋጠሙ ችግሮች የፋይናንስና አስተዳደር ክፍል ያስቀመጣቸው ሃሳቦች በዚህ በጀተ አመት

እንዳያጋጥሙ በትኩረት ስራዎች ይከናወኑ የሚል አስተያየት ተሰጥቶበታል፡፡

7. የኢንደስትሪ ፓርኩ የጥቃቅን ግዥ ሲከናወን ጥብቅ ቁጥጥርና ክትትል እየተደረገ መሆኑን ለማረጋገጥ ኦዲት
ሲደረግ ኢንዱስትሪ ፓርኩ የግዥ ባለሙያዎች ተመላሽ ገንዘብ ስለማድረጋቸው ምንም አይነት ማረጋገጫ
አለመኖሩን በተደረገው ኦዲት ለማረጋገጥ ተችሏል፡፡

ከስራ ክፍሉ የተሰጠ ምላሽ፡- በጥቃቅን ግዥ ሲደረግ ለእቃው የሚአወጣው ዋጋ ግምት ተወስዶ በቅድሚያ
መጠየቂያ ሰነድ ወጪ ይሆንና እቃውን ገዝተው በሚአስረክቡበት ወቅት የቅድሚያ መጠየቂያው ተሰርዞ
(አገልግሎቱን ጨረሰ )ተመላሽ ሂሳብን ለገንዘብ ያዥ ገቢ ይደረጋል ይህ ገንዘብ ከመመለስ የተሸለ አሰራር በመሆኑ
ነው፡፡

ማኔጅመንቱ የሰጠው ሃሳብ ፡- ተመላሽ ሂሳቦች መመለሳቸውን በሚገልጽ መልኩ ማስረጃዎች ይያያዙ
መመሪያዎችን በማይጥሱ መልኩ ፈጣን እና ቀልጣፋ አሰራር ካለ ስራው እንዲተገበር አስተያየት ተሰጥቶበታል፡፡

በመጨረሻም የኢንዱስትሪ ፓርኩ ዋና ስራ አስኪያጅ በሰጡት ማጠቃለያ መሰረት የመረጃ ክፍተት ያለባቸው
የክፍያ ሰነዶች የክፍያውን ሂደት ሊአስረዱ የሚችሉ ደጋፊ ማስረጃዎች እየተደራጁና ከክፍያ ሰነዱ ጋር እንዲያያዙ
ለዚህም ቁጥጥሩና ክትትሉ ተጠናክሮ እንዲቀጥል፡፡ በፕሮፎርማ የሚገዙ ግዥዎች አቅራቢዎች የሚወዳደሩት
በጥቅል ወይም በተናጠል መሆኑን የሚገልጹ ሃሳቦች በማወዳደሪያው ላይ እንደአስፈላጊቱ የሚገለጹበት መንገድ
ይመቻች፡፡ ማስተካከያ ያልተወሰደባቸው የኦዲት ግኝቶች ትኩረት በማድረግ የማሽተካከያ ስራዎች እንዲሰሩ
የኦዲት ባለሙያውም የኦዲት ግኝት መወቅቱ ምላሽ እንዲሰጣቸውን ድጋፍ እንዲደረግላቸው በማለት የእለቱ
የኦዲት የመውጪያ ስብሰባ ተጠናቋል፡፡
የአመት ፈቃድ ወደ ገንዘብ ሲቀየር አሰላል

You might also like