You are on page 1of 6

1.

የስትራቴጂ እና ዓመታዊ እቅድ አፈጻጸም ስኬታማነትን በተመለከተ


 ከ 2016-2020 በተተገበረው ስትራቴጂክ እቅድ ላይ በ 2019 ብር 368,509,050.59 ከታክስ በኋላ
የሚገኝ የተጣራ ትርፍ ታቅዶ የነበረ ቢሆንም ብር 115,265,954 (31.23%) ብቻ ማከናወን መቻሉ
 ከ 2016-2020 በተተገበረው ስትራቴጂክ እቅድ ላይ በ 2020 በጀት ዓመት ብር 429,754,255.88
ከታክስ በኋላ የሚገኝ የተጣራ ትርፍ ታቅዶ የነበረ ቢሆንም ብር 116,216,679.69 (27.04%) ብቻ
ማከናወን መቻሉ
 ከ 2016-2020 በተተገበረው ስትራቴጂክ እቅድ በ 2019 በጀት ዓመት የብር 6,339,355,215 ሽያጭ
ለማከናወን የታቀደ ቢሆንም የብር 1,968,729,611 (31.01%) ብቻ ማከናወን መቻሉ
 ከ 2016-2020 በተተገበረው ስትራቴጂክ እቅድ በ 2020 በጀት ዓመት የብር 7,681,494,814 ሽያጭ
ለማከናወን የታቀደ ቢሆንም የብር 1,393,873,180.69 (18.15%) ብቻ ማከናወን መቻሉ
 በ 2021 በጀት ዓመት በኤክፖርት ሸቀጦች አቅርቦት ዘርፍ የብር 493,908,600.00 ግዥ ለመፈጸም
ታቅዶ የብር 291,047,198.85 ግዥ በማከናወን የእቅዱን 59% መፈጸም ተችሏል፡፡
 በ 2021 በጀት ዓመት የብር 13,000,000.00 እጣን ግዥ ለመፈጸም ታቅዶ የነበረ ቢሆንም አዲስ
ምርት ወደ ገበያ በሚገባበት ከሚያዚያ እስከ ሃምሌ ባሉት ወራቶች ቤንሻንጉል አካባቢ የተገኘነዉን
እጣን ለመግዛት የተለያዩ ጥረቶች ቢደረግም በግዥ ስርአቱ ፈጣን ዉሳኔ ችግር እና በጨረታ
በተሳተፈባቸው /ወልቃይትና የመተማ የአምራች ማህበራት ጨረታ/ በመሸነፉ ምክንያት ክንዉንም
የለም፡፡
 በ 2021 በጀት ዓመት ኩባንያው በበጀት ዓመቱ የብር 2,784,151,513.58 ሽያጭ ለመፈጸም አቅዶ
የብር 1,853,794,870.90 ሽያጭ በማከናወን የእቅዱን 66% የፈጸመ ሲሆን በኤክስፖርትና ኢምፖርት

ሽያጭ አፈጻጸም ሲታይ ደግሞ የኤክስፖርት ዘርፍ ሽያጭ በዓመቱ 535,895,472.40 ብር ሽያጭ
ለማከናወን ታቅዶ የብር 223,429,419.17 ሽያጭ በማከናወን የእቅዱን 42% የተፈጸመ ሲሆን

በኢምፖርትና አገር ውስጥ ሸቀጦች ሽያጭ ዘርፍ ደግሞ የብር 2,248,256,041.18 ሽያጭ ለማከናወን እቅድ

ተይዞ የብር 1,630,365,451.73 ሽያጭ በማከናወን የእቅዱን 73% ፈጽሟል፡፡

የችግሩ ዋና ዋና ምክንያቶች
 በስትራቴጅዉ መሰረት አፈጻጸምን እየገመገሙ ባለመሄዱ መሰረት አፈጻጸም ላይ አሉታዊ
ተጽእኖ ሚያሳድሩ የዉጭ ምንዛሬ እጥረት፣ ስራማስኬጃ ገንዘብ ችግሮችን በወቅቱ መፍታት
አለመቻል
 አመራሩ ፈጣን ዉሳኔ መስጠት ላይ ዉስንነት መኖር
 ሊያጋጥሙ የሚችሉ ችግሮችን አስቀድሞ በእቅድ ይዞ መፍትሄ ማፈላለግ ላይ ዉስንነት
መኖር
ችግሩ የሚያስከትለው ተጽእኖ
 ኩባንያዉ በስትራቴጅ ዘመኑ መጨረሻ ሊያሳካ ያሰበዉን ግብ ላይ አሉታዊ ተጽእኖ ያሳድራል
 ሊገኝ የታሰበዉ ተጨማሪ ገቢ ባለመሳካቱ የኩባንያዉ ተጨማሪ ማስፋፊያ ስራዎችና ላይ
ተጽእኖ ያሳድራል፡፡ እንዲሁም የስራ ማስኬጃ ገንዘብ እጥረቱ እንዳይቀረፍ ያደርጋል፡፡
ሊወሰድ የሚገባው የመፍትሄ ሀሳብ
 እቅድ በሚዘጋጅበት ወቅት ተጨባጭ አቅምን እና በተጨባጭ ሊፈጸም የሚችል መሆኑን
በማረጋገጥ ወደ ትግበራ መግባት
 እቅድ አፈጻጸም ላይ ሊያጋጥሙ የሚችሉ ተግዳሮቶችን አስቀድሞ ለመፍታት አቅዶ
መስራት
 የአመራር ዉሳኔ ቅልጥፍና ያለዉ እንዲሆን ማድረግ እንዲሁም እንቅፋት የሚሆኑ የአሰራር
ስርዓቶችን በፍጥነት ማሻሻል
2. ከደንበኞች እና ከባለ ድርሻ አካላት ጋር ያለውን ግንኙነትን ቅሬታ በማይፈጥር መንገድ እያከናወነ

ስለመሆኑ፤
 ኩባንያው በ 2016 በጀት ዓመት ከሲውዲን አገር ካስመጣው 12 ሺህ ሜ/ቶን የቢራ ገብስ ጋር በተያያዘ
የተከሰተውን የመርከብ ዲሜሬጅ USD 664,000 ከኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ
አገልግሎት ድርጅት ጋር እልባት ባለመስጠቱ ለኮንቴነር ማስያዣ ዲፖዚት የተደረገው ብር
20,220,141.89 የተያዘ መሆኑ፤
 ኩባንያው ለአዲስ አበባ ዉሀ ስራዎች ድርጅት ካቀረበው የዲሲአይ ቧንቧና የዉሀ ፓምፕ ጋር በተያያዘ
የተፈጠረውን አለመግባባት በወቅቱ ባለፈታቱ ያልተተሰበሰበ ከ 6 ሚሊዮን ብር በላይ ቀሪ ክፍያ ያለ
መሆኑ፤
 ኩባንያው ከፌቤላ ዘይት ፋብሪካ እንዲያሰራጭ ውክልና የተሰጠው ቢሆንም የተወሰኑ ቦታዎችን ለሌላ
አከፋፋይ የተሰጠ መሆኑ፤
 የስሚንቶ ምርት ክምችት መኖሩ ሳይረጋገጥ በባንክ ገቢ ላደረጉ ደንበኞች የሽያጭ ደረሰኝ እየተቆረጠ
የሚሰጥበት ሁኔታ ጎልቶ መታየቱንና በደንበኞች ዘንድ ቅሬታ መፍጠሩ፤
 ኩባንያው ለአማራ መንገድ ስራዎች ድርጅት የአስፋልት ቤትመንት (ሬንጅ) ለማቅረብ ውል የያዘ
ቢሆንም በወቅቱ ባለማቅረቡ በደንበኛው ዘንድ ቅሬታን የፈጠረ መሆኑ፤
 ኩባንያው በ 2021 በጀት ዓመት ከውጭ እያስመጣ ካከፋፈለው የፓልም ዘይት ውስጥ በመንግስት
ከተደረገ 15% የውጭ ምንዛሬ ማስተካካያ ለኩባያው የሚሰጥ የማካካሻ ክፍያ ከ 4 ኛ-6 ኛ ዙር
ለተሰራጨው ብር 98,768,585.64 ያለ ቢሆንም ከንግድ ሚኒስቴር ያልተሰበሰበ መሆኑ፤
 ከአማራ ዉሃ ስራዎች ኮንስትራክሽን ድርጅት ጋር ባለዉ የጀነሬተር እና የዉሃ መሳቢያ ፓምፕ
ግብይት የተፈጠረ አለመግባባት እልባት አለማግኘቱ፤
 ኩባንያው ለአማራ መልሶ መቋቋምና ልማት ድርጅት (ዓመልድ) የግሪን ሀውስ ግንባታ ማቴሪያል ከ 2
ዓመት በፊት ያቀረበ እና ተከላውን ለማሰራት ከቻይና ባለሙያ ያስመጣ ቢሆንም በአመልድ በኩል
የፋውንዴሽን ስራ ባለመጠናቀቁ ስራው ሳይከናወን ባለሙያው መመለሱ፤
 ኩባንያው የሽያጭ መመዝገቢያ መሳሪያዎችን ሽያጭ በተመለከተ የደንበኞችን መረጃ አደራጅቱ
ባለመያዙ ኢትዮ ቴሌኮም ጋር በሚፈጠር የመረጃ ክፍተት ውዝፍ የአየር ስዓት ክፍያ በሚል ከ 2017
እስከ ፌብሩዋሪ 2022 ድረስ አጠቃላይ ቫትን ጨምሮ ብር 37,364,342.85 ውዝፍ ክፍያ የተጠየቀ
መሆኑ፤
 ኩባንያው በአዋሳና አዳማ ሽያጭ ጣቢያ የሽያጭ መመዝገቢያ ማሽን ሽያጭ ከ 5 ዓመት በፊት ያቆመ
ቢሆንም ከገቢዎች ሚኒስቴር ጋር ተወያይቶ ያሉትን 703 የደንበኛ ማሽኖች እንዲወግዱ ባለመደረጉ
ለሰራተኛ ደመወዝና ለቤት ኪራ ወጪ የተዳረገ መሆኑ፤
 ኩባንያው ለኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዋና/መቤት ጀነሬተር ለማቅረብ ዉል የያዘ ቢሆንም የማስረከቢያ
ጊዜው 31 ቀናት ዘግይቶ በማቅረቡ ለብር 140,853.29 መቀጫ የተዳረገ መሆኑ፤
 ኩባንያው ለ 2013/2014 የምርት ዘመን የሚውል ጸረ አረም፤ ጸረ ተባይና ጸረ ፈንገስ ኬሚካል የውጭ
ምንዛሬ በልዩ ሁኔታ አስፈቅዶ ያስመጣ ቢሆንም ዩኔኖች፤ መሰረታዊ ማህበራ እና በኤቲኤ በኩል
የተደራጁ አካላት ፍላጎታቸውን ባለማሳወቃቸው ለስርጭት መቸገሩን ለአብክመ ግብርና ቢሮና
ለህ/ስ/ማህበራት ማስፋፊያ ኤጀንሲ ማሳወቁ፤
 የጥቁር አባይ ትራንስፖርት አሽከርካሪ በሰሌዳ ቁጥሩ 50948/17140 የሆነ መኪና ከደርባ ሲሚንቶ
ፋብሪካ ወደ ጎንደር የጫነውን ፒፒሲ ሲምንቶ ለባለቤቱ ሳያደርስ መንገድ ላይ የሸጠው መሆኑ፤
 በከልቻ ትራንስፖርት አ.ማ 1 ባለ 20 ፊት ኮንቴነር ከጅቡቲ ወደ ቃሊቲ በ 23/08/2020 እንዲጭን
የታዘዘ ቢሆንም የኮንቴነሩ መዳረሻ አ/አበባ መባል ሲገባው መቀሌ በመባሉ በበከልቻ ላይ አላስፈላጊ
ወጪ ማስከተሉ፤
 ጥቁር አባይ ሌሎች ትራንስፖርት ድርጅቶች ከሚያቀርቡት ዋጋ የተጋነነ ከመሆኑ በተጨማሪ በገባው
ውል መሰረት በወቅቱ ተሸከርካሪ የማያስገባ መሆኑ፤
 ቡሬ ከተማ ከሚገኘው ፊቤላ የዘይት ፋብሪካ ለሰሜን ሸዋ ዞን ወረዳዎች ስርጭት የሚውል ዘይት ወደ
አዲስ አበባ ሲያጓጓዝ በኦሮሚያ ክልል ግራር ጃርሶ ወረዳ ህገወጥ ጭነት ነው በሚል በፖሊስ ተይዞ
ከ 15 ቀን በላይ እንዲጉላላ በመደረጉ በኩባያው ላይ የጊዜና የወጪ ብክነት ማስከተሉ፤
 የኩባንያውን ስሚንቶ የሚያጓጉዙ የሀገር ውስጥ የደረቅ ጭነት ማመላለሻ ትራንስፖርት ድርጅቶች
በክልሎች መውጫና መግቢያ ኬላዎች የሚከፈሉ የኮቴ ክፍያዎች በአምባሰል እየተተካ የነበረ ቢሆንም
በራሳቸው እንዲሸፍኑ በመወሰኑ ቅሬታ እያቀረቡ መሆኑ፤
የችግሩ ዋና ዋና ምክንያቶች
 ኩባንያዉ ከደንበኞች እና አጋር አካላት ጋር ያለዉን ግንኙነት ቅሬታ በማይፈጥር መልኩ
እንዲሆን የሚያስችል አሰራር ተግባራዊ አለማድረግ
 ኩባንያዉ የሸቀጥ አቅርቦትና ስርጭት ከደንበኞች ጋር በገባዉ ስምምነት መሰረት ሆኖ
አለመገኘት
 የሚመለከተዉ የስራ ሃላፊና ባለሙያዎች ስራቸዉን በቅልጥፍና እና በሃላፊነት መንፈስ
አለመፈጸም

ችግሩ የሚያስከትለው ተጽእኖ


 ኩባንያዉ ለተጨማሪ ወጭዎች ይዳረጋል
 የኩባንያዉ መልካም ስም ላይ ተጽእኖ ያሳድራል
 የገበያ ተደራሽነትን ይቀንሳል
ሊወሰድ የሚገባው የመፍትሄ ሀሳብ
 ኩባንያዉ ለደንበኞች የሚያቀርባቸዉን የተለያዩ ሸቀጦች በተደረገዉ ስምምነት መሰረት
በቅቱን ጠብቆና በሚፈለገዉ የጥራት ደረጃ መሰረት ማቅረብ እንዲሁም ለሚፈጠሩ
ቅሬታዎች ቶሎ ምላሽ ሊሰጥ የሚችል የአሰራር ስርዓት መዘርጋት ላይ መስራት ያሻል፡፡
3. የኩባንያው ሰራተኞች ህጋዊ አሰራርን ተከትለው እየሰሩ ስለመሆኑ፤
 በስሚንቶ አቅርቦት የገቢና ወጪ ሰነዶች አጠቃቀም ላይ የሚከተሉት ችግሮች መገኘታቸው
 ኩባንያዉ ለደርባ ስሚንቶ በከፈለዉ እና ፋብሪካዉ በቆረጠዉ ሽያጭ ሰነድ መካከል ልዩነት
መታየት፤
 በ MRV ገቢ ሳይደረግ መሸጥ
 በ MTOV ወጭ ተገርጎ የተላከ ስሚንቶ MTIV ገቢ አለማድረግ
 ስሚንቶዉ ወጭ የተደረገበት ቀን ዋጋ በወቅቱ ከነበረዉ የዋጋ ዉሳኔ ጋር ልዩነት መኖር
 በሽያጭ ሰነድ ደርባ ስሚንቶ እንደተሸጠ ተገልጾ የዋጋ ማስተካከያ ሳይደረግ የዳንጎቴ ስሚንቶ
ወጭ አድርጎ ማስረከብ፤
 በደቡብ አቸፈር የኮንትራት ፋርሚንግ ውል ለያዙ አርሶ አደሮች ያለወጪ ሰነድ 408 ማጭድ የተሰጠ
በመሆኑ የማጭዱን ገንዘብ ለመሰብሰብ ማስቸገሩ፤
 ከኩባንያው 2000 ኩ/ል ስሚንቶ የገዛ ጌታሰዉ አያሌዉ የተባለ ደንበኛ የግንባታ ሳይቱ ካለበት ባህርዳር
ቅርንጫፍ ገቢ ሰነድና ሽያጭ ሰነድ ሳያስቆርጡ ቀጥታ ሳይታቸዉ ላይ ያራገፉ መሆኑ፤
 በደሴ ቅርንጫፍ በአንድ የባንክ ስሊፕ 2 የሽያጭ ደረሰኝ ተቆርጦ መገኘት፤
 ከደብረ ማርቆስ ሽያጭ ጣቢያ 4 ፓምፕ፤ 300 ሜትር ደሊቨሪ ሆዝ እና 32 ሜትር ሳንክሽን ሆዝ
በሰነድ ወጪ ሳይደረግ መሸጡ፤
 የሽያጭ መመዝገቢያ መሳሪያ በገቢዎች ሚኒስቴር ሳይመዘገብና መለያ ቁጥር ሳይሰጠው በመሸጡ
ሚኒስትር መ/ቤቱ ቅሬታ እያቀረበ መሆኑ፤
 ኤሌክትሮኒስ የሽያጭና ደንበኛ አገልግሎት ሰራተኛ ከቴክኒክ ክፍል ተጠግነው የተጠናቀቁ
HEA001755 እና HEA003878 የተባሉ 2 የሽያጭ መመዝገቢያ ማሽኖችን ከተረከቡ በኋላ
ማጥፋታቸው፤
 የጎንደር በአገልግሎት የ 2020 ዓመታዊ የንብረት ቆጠራ ሲደረግ ቆጠራ ኮሚቴው በመጋዘን ያለውን
ሳይቆጥር የቢን ካርድ ባላንስ በመውሰድ ቆጠራዉን እንዳደረጉ በማስመሰል ሪፖርት ማቅረባቸው፤
 በጎንደር ፕሮሰሲንግ አገልግሎት በ 2020 በጀት ዓመት ለዉጭ ሃገር አቅርቦት የሚዉል 7,500 ኩ/ል
ሰሊጥ ለብጠራ ገቢና ወጪ ሲደረግ በሰነድ ገቢና ወጪ እየተደረገ ባለመሰራቱ በፋይናንስ ምዝገባ ላይ
ችግር መፍጠሩ፤
 በጎንደር ፕሮሰሲንግ የደለሎ እርሻ ልማት ሰራተኛ 557.3 ኩ/ል ማሽላ በዋጋ ብር 200,168፤ የሰሊጥ
ምርጥ ዘር 50 ኩ/ል በዋጋ ብር 77,726፤ ያልተጣራ አኩሪ አተር 0.56 ኩ/ል በዋጋ ብር 1,918 አጉድለው
መገኘታቸው፤
 ከሮቤራ ማበጠሪያ ቤት በቡና ብጠራ አገልግሎት ወቅት በንብረት ሰራተኛዋ በወ/ሮ ንግስት ታደሰ ስም
1.29 ኩ/ል ቡና በጉድለት መታየቱ፤
 ከ ECX (ኮምቦልቻ ምርት ገበያ) በተለያየ ጊዜ እ.ኤ.አ ከጁን 27 እስከ ጁላይ 25/2020 ጊዚያት ውስጥ
በወ/ሮ የትምወርቅ ክብረት ስም ከምርት ገበያ በቀጥታ ወደ ማበጠሪያ ቤቱ ሲገባ የጎደለ 8.71 ማሾ
የታየ መሆኑ፤
 ከኮምቦልቻ ምርት ገበያ በአቶ ሽመልስ ተመስገን ስም 2.89 ኩ/ል ማሾ በጉድለት የታየ መሆኑ፤
 ከጎንደር ፕሮሰሲን ማይካድረ ላይ በግዥ ኮሚቴ ተገዝቶ በ MRV ገቢ የተደረገ 7,128.95 ኩንታል

ሰሊጥ ሲሆን ኮሚቴው በ MTOV ወጪ አድርጎ ወደ ጎንደር ፕሮሰሲንግ የላከው 7,085.97 ኩንታል

በመሆኑ 42.98 ልዩነት ማሳየቱ፤ ጎንደር ሲደርስ በ MTIV የገቢ ሰነድ የተመዘገበው 7,125.91 ኩንታል

ሲሆን በምድር ሚዛን ሲመዘን ደግሞ 7,107.80 ሆኖ መገኘቱ፤


 ከዳንጎቴ ሲሚንቶ ፋብሪካ በተ/ሃይማኖት ትራንስፖርት ድርጅት ወደ ደብረ ብርሃን ሽያጭ ጣቢያ
የተላከ ስሚንቶ 41 ከረጢት የጎደለ ቢሆንም የስቶር ሰራተኛ በሙሉ እንደተረከበ አድርጎ ሰነድ
አዘጋጅቶ መገኘቱ፤
 የጎንደር ቅርንጫፍ የዘይት መጋዝን ሰራተኛ በሆኑት ወ/ሮ ጥሩወርቅ መለሰ፤ አቶ እያዩ አዲስ፤ አቶ
አሸናፊ ገዳሙ እና አቶ አዲሱ ቸኮል በድምሩ ብር 652,148.82 የሚገመት ንብረት ያጎደሉ መሆኑ፤
 የሲሚንቶ ግብይት አጣሪ ኮሚቴዎች የስሚንቶ ግብይት ስራ ከጀመረበት ጁን 2020 እስከ ሜይ
31/2021 ድረስ ከሶስቱም ፋብሪካዎች የተገዛ ስሚንቶ ፤ ክምችት እንቅስቃሴ እና ሽያጭ
እንዲያስታርቁ አቅጣጫ የተሰጠ ቢሆንም ከስሚንቶ ተረካቢ ሰራተኛ ለጣቢያዎች የተላከ 4,400 ኩ/ል
ሲሚንቶ ወደተላከበት ጣቢያ መድረሱ ያልተረጋገጠ በመሆኑ የስሚንቶ ማስታረቅ ስራው ሙሉ
በሙሉ ያልተጠናቀቀ መሆኑ፤
የችግሩ ዋና ዋና ምክንያቶች
 የሚመለከታቸዉ ሰራተኞች የኩባንያዉን አሰራር ስርዓት አክብረዉ አለመስራት
 በአንዳንድ ሰራተኞች ላይ ስነምግባር ግድፈቶች መኖር
 የሸቀጥ ገቢ እና ወጭ የቁጥጥር ስርዓቱ ደካማ መሆን
ችግሩ የሚያስከትለው ተጽእኖ
 ኩባንያዉን ለአላስፈላጊ የሃብት ብክነት ይዳርገዋል
 የኩባንያዉን መልካም ስም ያበላሻል
 ከደንበኞች ጋር የቅሬታ ምንጭ ይሆናል
ሊወሰድ የሚገባው የመፍትሄ ሀሳብ
 የወጭና ገቢ ሸቀጦች አሰራር ስርዓት ላይ ለሚመለከታቸዉ ባለሙያዎች የግንዛቤ
ማሳደጊያ ስራዎች መስራት
 ችግሮች ከመፈጠራቸዉ በፊት ወቅታዊ የክትትልና ቁጥጥር ስራዎች መስራት
 ሃላፊነታቸዉን በማይወጡ ሰራተኞች ላይ አስተማሪ የሆነ የእርምት እርምጃ መዉሰድ

You might also like