You are on page 1of 32

በመንግሥት ፋይናንስ አስተዳደር ሕግ ማዕቀፎች ዙሪያ

ከዞን/ወረዳ ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት መምሪያ/ጽ/ቤት


ለተወጣጡ ባለሙያዎች የአቅም ግንባታ ሥልጠና
ለመስጠት የተዘጋጀ የሥልጠና ሰነድ

ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ


ጥር 2010 ዓ/ም
የአቀራረብ ይዘት
1. መግቢያ
2. የመንግሥት ፋይናንስ አስተዳደር የህግ ማዕቀፎች
የቀጠለ …
መግቢያ
• የመንግሥት ወጪ አስተዳደርና ቁጥጥር ሪፎርም ፕሮግራም ከሲቪል
ሰርቪስ ማሻሻያ አምስት ንኡሳን ፕሮግራሞች አንዱ ሆኖ በመንግሥት
የፋይናንስ አስተዳደርና ቁጥጥር ዙሪያ የማሻሻያ ሥራዎችን ለመተግባር
በገ/ኢ/ል/ሚኒስቴር ሥር የመንግሥት ወጪ አስተዳደርና ቁጥጥር
ማሻሻያ ፕሮግራም ማስተባባሪያ ዳይሬክቶሬት ተዋቅሮ የፌዴራል፣
የክልል መንግሥታትና የከተማ አስተዳደሮች የሚመሩበትን የፋይናንስ
ዲስፒሊን ለማስፋን እንዲሁም አዳዲስ አሰራሮችን ለመዘርጋት
የሚያስችል እንቅስቃሴዎችን በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡
የቀጠለ…..
• ቢሮ የክልሉን የመንግሥት ፋይናንስ አስተዳደር አፈጻጸም አሁን
ከለበት ወደ ተሸለ ደረጃ ለማድረስ በሁሉም አስተዳደር እርከን
የሚስተወሉ የመንግሥት ፋይናንስ አስተዳደር የአፈፃፀም
ክፍተቶች ላይ የማስተካከያ እርምጃ በመዉሰድ ዘላቂ የሆነ
ሥርዓት እንዲሰፍን የፈጸሚ አካላትን የሥራ አፈፃፀም አቅምና
ብቃት ለማሰደግ ተፈጻሚ የሚደረጉ በርከታ የሥራ
ዕቅዶችን/ተግባራት የአፈፃፀም መርሃ ግብር በማስቀመጥ
ከፍተኛ እንቅስቃሴ በማድረግ ላይ የሚገኝ ቢሆንም በህግ
ማዕቀፎች አፈፃፀም ላይ ጎልቶ የሚታዩ ክፍተቶች ይገኛል፡፡
1. ስለ መንግሥት ፋይናንስ አስተዳደር የህግ ማዕቀፎች.


1. በፋይናንስ አስተዳደር አዋጅ 128/2002
የተመለከቱ
• አንቀጽ 5፡- ኃላፊነትና ተጠያቂነት
እያንዳንዱ የመንግስት መስሪያ ቤት የበላይ ኃላፊ፤
የዚህ አዋጅና በአዋጁ መሠረት የወጡትን ደንቦችና ድንጋጌዎች
በኃላፊነት በሚመራዉ መስሪያ ቤት ዉስጥ ሙሉ በሙሉና
በተገቢዉ መንገድ ተግባራዊ መሆናቸዉን የማረጋገጥ
ኃላፊነት አለበት ይላል፡፡
ስለ መንግሥት ፋይናንስ አስተዳደር የህግ ማዕቀፍ
የቀጠለ….
• አንቀጽ 7፡- የመንግስት መስሪያ ቤቶች የበላይ ኃላፊዎች
ኃላፊነት
1. የመንግስት መስሪያ ቤቶች የበላይ ኃላፊዎች በኃላፊነታቸዉ ሥር
የሚገኘዉ የመንግስት ሀብት ለተገቢ እና አግባብ ባለዉ የመንግስት
አካል ለጸደቀ ዓላማ ብቻ መዋሉን እንዲሁም አጠቃቀሙ ቁጠባን፣
ብቃትን እና ዉጤታማነትን በከፍተኛ ደረጃ ሊያስገኝ በሚችል
መንገድ መፈጸሙን የማረጋገጥ ኃላፊነት አለባቸወ፡፡
. በፋይናንስ አስተዳደር አዋጅ 128/2002 የበላይ ኃላፊዎችየቀጠለ…
1. ቢሮዉ የዘረጋዉ የፋይናንስ አስተዳደር ሳይጣስ በየመስሪያ ቤቱ
የፋይናንስ አስተዳደር ሥርዓት መዘርጋትንና በትክክል የሚሠራ
መሆኑን የማረጋገጥ፣
2 . በመ/ቤቱ በተዘረጋዉ በዉስጥ ቁጥጥር ሥርዓት እያንዳንዱ
ሰራተኛ ኃላፊነቱን ላይቶ ማከናወን የሚያስችል አስፈላጊ የሥራ
ክፍፍል የተደረገበት መሆኑን ያረጋግጣል፣
የኃላፊዎች ኃላፊነቶች የቀጠለ…
3. ወቅታዊና አግባብ ያለዉ አስተማማኝ የፋይናንስ መረጃና ትንታኔ
መዘጋጀቱንና መሠራጨቱን ማረጋገጥ፣
4. የመስሪያ ቤቱ የሂሳብ ሪፖርት በጊዜ ሰሌዳዉ መሠረት ለፋይናንስና
ኢኮኖሚ ልማት መምሪያ/ ቢሮ መላኩን የማረጋገጥ፣
5. የመ/ቤቱ ሠራተኞች የፋይናንስ አስተዳደር አዋጁን፣ አዋጁን መሠረት
በማድረግ የሚወጣዉን ደንብና መመሪያዎች እንዲሁም የተዘረጋዉን
የአሰራር ሥርዓት በመከተል ተግባራቸዉን ማከናወናቸዉን፣ የዉስጥ
ኦዲት ጊዜዉን ጠብቆ መፈፀሙን ያረጋግጣሉ፣
በፋይናንስ አስተዳደር አዋጅ 128/2002 ...
6. በቢሮዉ በሚወጣዉ መመሪያ መሠረት መ/ቤቶች ዓመታዊ
በጀታቸዉን አዘጋጅቶ ማቅረባቸዉን ያረጋግጣሉ፣
7. የመ/ቤቱን/የወረዳዉን/የዞን የሥራ ፕሮግራም በመገምገም የጥሬ
ገንዘብ ፍላጎትና ፍሰት ዕቅድ ያቀርባሉ፣
8. በዉስጥ ኦዲት ሪፖርት በተመለከተዉ መሠረት በኦዲት ግኝቶች
ላይ አስፈላጊ እርምጃ መዉሰድ፣
አዋጁን ተግባራዊ ለማድረግ የሚያግዙ በቢሮዉ የወጡ ዝርዝር
ተግባራትን የያዙ መመሪያዎች በሥራ ላይ የዋሉ አሉ፡

1. የተሻሻለ የበጀት አስተዳደር መመሪያ፣


2. የመንግሥት መ/ቤቶች የሂሳብ አያያዝ መመሪያ፣
3. የጥሬ ገንዘብ አስተዳደር መመሪያ፣
4. የመንግሥት ገንዘብ ክፍያ መመሪያ፣
5. የጋራ አገልግሎት አሰጣጥና አደረጃጀት ሥርዓት መመሪያ፣
6. የእንስፔክሽንና የዉስጥ ኦዲት አፈጻጸም እና የሙያ ሥነ ምግባር መመሪያ፣
7. የምንግሥት መስሪያ ቤቶች የደረሰኞችና የሌሎች የህትመት አያያዝና
አስተዳደር መመሪያ ቁጥር 27/2010
8. የመስተንግዶ በጀት አመዳደብና አጠቃቀም መመሪያ
9. የመንግሥት መ/ቤቶች የበጀት አመዳደብና የወጪ ቅነሳ አጠቃቀም መመሪያ፣
1. የተሻሻለ የበጀት አስተዳደር መመሪያ፣
የዚህ መመሪያ ዓላማ
1. በአንድ ዓመትና በመካከለኛ ጊዜ ዘመን መንግስት ለሚያከናወናቸዉ፣ለአስተዳደርና
ጠቅላላ አገልግሎት፣ ለኢኮኖሚ፣ለሶሻል እና ለልዩ ልዩ አገልለሎትና ለልማት
ሥራዎች በሚያስፈልገዉ ወጪ ቀልጣፋና ዉጤታማ በሆነ ሁኔታ፣
1. የበጀት ድልድል ለማድረግ፣
2. የበጀት አፈጻጸሙን ለመከታታልና ለማስተዳደር
እንዲያስችል፣
3. በጀቱ ለታለመለት ዓላማ መዋሉን ለማረጋገጥ ነዉ፡፡
የመመሪያዉ ይዘት
• መንግሥት በመካከለኛ ዘመን የሚዘጋጀዉን የማክሮ ኢኮኖሚ
ፊስካል ማዕቀፍ ዕቅድ ማዘጋጀትና መፅደቅ፣
• የአስተዳደር እርከንኖች የበጀት ድጋፍ ማሰታወቅ፣
• የበጀት አጠያየቅና አፈቃቀድ ሂደቶችንና የጊዜ ሰሌዳን እና
• የበጀት አስተዳደር ዋና ጉዳዮች ናቸዉ፡፡
በዚህ መመሪያ በዋናነት የሚታየዉ ከቅድመ በጀት ዝግጅት እስከ በጀት ማፅደቅ ድረስና
የበጀት አስተዳደርና አፈጻጸም ይሆናል፡፡ ስለዚህ
 በጀት ሲዘጋጅ ሊሰበሰብ የሚችል የገቢ መጠን በወረዳዉ ዉስጥ ያለዉን የወጪ መጠን
ሊሸፍን የሚችል መሆን አለበት፣
 ዓመታዊ በጀት ሲዘጋጅ ሁሉንም መረጃ ያየዘና ለሁሉም ዜጎች ተደራሽ መሆን አለበት፣
2. የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች የሂሳብ አያያዝ መመሪያ ፣
የመመሪያዉ ዓላማ
• በጥሬ ገንዘብ ላይ የተመሰረተዉ የተሻሻለ የሂሳብ አያያዝ
ሥርዓት በመጠቀም በጥንድ የሂሳብ መዝገብ አያያዝ ዘዴ
ሀብትንና ዕዳን መመዝገብና ሪፖርት ለማድረግ፣
1. ከበጀት ሥርዓት ጋር አብሮ የሚሄድ የጥንድ የሂሳብ
አያያዝ ሥርዓት መከተል፣
2. ለጥሬ ገንዘብ ገቢና ወጪ እዉቅና መስጠት፣
3. ጥሬ ገንዘብ ነክ ላልሆኑ ሂሳቦች እዉቅና መስጠት፣
በተዘረጋዉ የሂሳብ አያያዝና አወቃቀር ሥርዓት መሠረት ሒሳቦችን
በየዕለቱ በመመዝገብና በመወራረስ (የሂሳብን ኡደትን በመጠቀም)
 ትክክለኛ፣ ወቅታዊና የተሟላ የሂሳብ መረጃ በማዘጋጀት ፣
1. ለመንግሥትና ለልማት አጋሮች የሚቀርበዉን የመረጃ
ጥራት ለማሻሻል፣
2. በወቅታዊና በትክክለኛ መረጃ ላይ በመመስረት
የተሻለ የዉሰኔ አሰጣጥ እንዲኖር ለማስቻል፣
 IBEX በመጠቀም አለምአቀፍ ደረጃዉን የጠበቀ መረጃ በማዘጋጀት የመንግሥትና የልማት
አጋሮችን ፍላጎት ማሟለት፣
 ከክፍያ በፊት የተፈቀደ በጀት መኖሩን በማረጋገጥ የበጀት ቁጥጥርን ማሻሻል፣
 የማይሰበሰብ ተሰብሳቢ ሂሳቦች፣ የጠፋ ገንዘብ ወይም ንብረት ከመዝገብ መሰረዝ
የሚያስችል የአፈጻጸም ሥርዓት በሥራ ላይ ማዋል፣
 የፋይናንስ እንቅስቃሴ የተከናወናባቸዉንና የተመዘገበባቸወ የሂሳብ ሰነዶችና መዛግብት
ሥርዓት ባለዉ መንገድ ደህንነታቸዉ ተጠብቆ እንዲያዝና እንዲአስፈላጊነቱ እንዲወገድ
የሚየደርግ አሰራር እንዲኖር ማድረግ ፣
በዚህ መመሪያ የመን/መ/ቤቶች የፋይናንስ አሰራር ኃላፊነት

• ሀብትን ከብክነትና ከጥፋት መካላከል በሚያስችል መልኩ


ተገቢዉ የሥራ ክፍፍልና አደረጃጀት ኖሮት የመንግሥትን
ሥራ ሲያከናዉኑ ሥራ ላይ ፀንቶ ባሉ አዋጆች፣ ደንብ እና
መመሪያዎች እንዲመራ ማድረግ አለባቸዉ፡፡
• መ/መ/ቤቶች ለጥቃቅን የሥራ ማስኬጃ ወጪዎች
የሚዉለዉን ገንዘብ አስተዳደር በገንዘብ የአተካክ ዘዴ
ማከናወን አለባቸዉ፡፡
3 የጥሬ ገንዘብ አስተዳደር መመሪያ
የዚህ መመሪያ ዓላማ
ለበጀት ዓመቱ የተፈቀደዉን በጀት መነሻ በማድረግ፣
 ዓመታዊ የጥሬ ገንዘብ ገቢና ወጪ ዕቅድ በወር ከፋፍሎ ማዘጋጀት፣
 ተንከባላይ የ3 ወር የገቢና የወጪ የጥሬ ገንዘብ ፍላጎት ፍሰት ትንቢያ ማዘጋጀት፣
 በብድርና በእርዳታ የሚካሄድ ፕሮግራሞችና ፕሮጅክቶች ክፍያ ለፕሮግራሙ
ባለቤቶች ለማስተላለፍ እንዲቻል የጥሬ ገንዘብ ዕቅድ በአስፈጸሚ መ/ቤቶች
ተዘጋጅቶ እንዲቀርብ ማድረግ፣
 የጥሬ ገንዘብ ገቢና ወጪ አፈጻጸም በየጊዜ መገምገም፣
 የመንግሥት ጠቅላላ የፋይናንስ አቅም ለመገመት እና የሚፈጠረዉን ጊዜያዊ
የፋይናንስ ጉድለት ለመሸፈን የሚያስችል አሰራር ተግባራዊ ለማድረግ፣
 በተጠቃለለ ፈንድ ዉስጥ ያለሥራ የተቀመጠዉን ገንዘብ መጠንን በመቀነስ ለአጭር
ጊዜ ወጪ መሸፈኛ የሚከፈል ወለድን ለመቀነስ፣
 ተረፊ የመንግሥት ገንዘብ ሲኖር ቅድሚያ በሚሰጣቸዉ መስኮች ላይ እንቨሰት
የሚደረግበት ሁኔታ ለመወሰን፣
የጥሬ ገንዘብ መመሪያ የቀጠለ…
የመንግሥት ገንዘብ አሰባሰብና ገቢ አደራረግን የተቀላጠፈ ለማድረግ፤
 ማንኛዉም የመንግሥት ገንዘብ ለመቀበል/ለመሰብሰብ የሚቻለዉ
በመ/ቤቱ የበላይ ኃላፊ ገንዘብ ለመሰበሰብ ዉክልና የተሰጠዉ ቋሚ
የመንግስት ሠራተኛ ብቻ ይሆናል፣
 ገንዘብ ሊሰበሰብ የሚቻለዉ ተከታታይ ቁጥር ባለዉና ቢሮ
ባሰተመዉ የገቢ ደረሰኝ ወይም መ/መ/ቤቱ ቢሮን በማስፈቀድ
በዘጋጀዉ የገቢ ደረሰኝ ይሆናል፡፡
 በጥናት ላይ የተመሰረተ የገቢ ዕቅድ ለማቀድ፣
 የገቢ ዕቅድና አፈጻጸም በየጊዜ ለመገምገም … ወዘተ ናቸዉ፡፡
የባንክ ሂሳብ አስተዳደር
• ማንኛዉም የመን/መ/ቤት ከቢሮ በጽሑፍ ሳይፈቀድለት የባንክ ሂሳብ ሊከፈት
አይችልም፣
• የመንግሥት መ/ቤቶች የባንክ አካዉንት የሚከፈተዉ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ይሆናል፣
• ከመንግሥት ማዕከላዊ ግምጃ ቤት ለተመደበዉ በጀት ማንቀሳቀሽነት የባንክ ሂሳብ ባንክ
የሚከፈተዉ ራሱን ችሎ ሂሳብ አቅራቢ ለሆነ ወይም በሥራቸዉ ባህሪይ ምክንያት በሌለ
አካባቢ ላሉ የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች ብቻ ነዉ፡፡
• ቢሮዉ በመንግሥት መ/ቤቶች ስም የተከፈቱ የባንክ ሂሳቦችን በበቂና አሣማኝ ምክንያት
ሊዘጋ ይችላል፣
• የባንክ ሂሳብ መደቦች (A, B, C, D, F, L, S & Z ) ናቸዉ፡፡
• የተከፈቱ የባንክ ሂሳቦች በአግባቡ ተመዝግበዉ መያዝ አለባቸዉ፣
• ለእያንዳንዱ የባንክ ሂሳብ በየወሩ በኢትዮጵያ አቆጣጠር የተዘጋጁ የባንክ መግለጫዎችን
ከባንክ በመምጠት ከመ/ቤቱ ባንክ ሌጀር ካርድ ጋር በማነጻጸር በየወሩ የባንክ
ማስታረቂያ እየተዘጋጀ ተደረጅቶ መቀመጥ አለበት፣
4. የገንዘብ ክፍያ መመሪያ፣
የዚህ መመሪያ ዓላማ
• የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች የገንዘብ አስተዳደር ጤናማ ለማድረግ፣
• በተገባ ዉል ወይም መ/ቤቶች ባለባቸዉ የክፍያ ግዴታ መሠረት ከተፈቀደላቸዉ በጀት ላይ ወጪ
ለማድረግ ነዉ፣
የመንግሥት መ/ቤቶች የፋይናንስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 128/2002 በአንቀፅ 32 በተደነገገዉ
መሠረት የወጪ በጀት ክፍያን ለመጠየቅ ዓመታዊ የገቢና የወጪ ዕቅዳቸዉንና የ3 ወራት የገቢ ዕቅድና
የወጪ ፍላጎት በጥሬ ገንዘብ አስተዳደር መመሪያ መሠረት ማቅረብ አለባቸዉ፡፡
የክፍያ አፈጻጸም
 ለሚከፈለዉ ክፍያ የተፈቀደ በጀት መኖር አለበት፣
 በጀት በሌለበት ክፍያ መፈፀም የለበትም፣
 ክፍያ የሚፈፀመዉ በጥሬ ገንዘብ፣ በቼክ እና በባንክ ዝዉዉር፣
 እስከ 2,000 ብር በካዝና እንዲቀመጥ ከተወሰነ ጥሬ ገንዘብ ጣሪያ መሆን አለበት፣
 ከ2,000 ብር በላይ በቼክ መፈፀም አለበት፣
 ክፍያዎች ከመፈፀማቸዉ በፊት የሚቀርቡ የክፍያ ጥያቄዎችን በአግባቡ መመርመር ያስፈልጋል፣
 ክፍያ የተከፈለባቸዉ የሂሳብ ሰነዶችን ለሚመለከተዉ አካል በወቅቱ ማስተላለፍ፣
በመንግሥት መ/ቤቶች በጀትን ለመቆጣጠር ሁለት ቁልፍ
ተግባራት አሉ፡፡
 ክፍያ መፈፀም የሚቻለዉ በአዋጅ የተፈቀደ በጀት ሲኖር ብቻ
መሆኑን ማረጋገጥ ነዉ፣
 በሥራ ላይ የዋለዉ ወጪ ከተስተካከለዉ በጀት አለማብለጡን
መቆጣጠር ናቸዉ፡፡
 በፋይናንስ አዋጅ ምዕራፍ 5 አንቀጽ 33 በመተላለፍ የተፈቀደ በጀት
መኖሩን ሳያረጋግጥ ከተፈቀደለት በጀት በላይ ወጪ ማድረግን የሚጠይቅ
ማናቸውንም ውል የተፈራረመ ወይም እንዲፈረም ያደረገ የመንግስት
መሥሪያ ቤት ኃላፊ/ተወካይ ከብር 5 ሺህ በማያንስና ከብር 20 ሺህ
በማይበልጥ የገንዘብ መቀጮና ከ5 ዓመት በማያንስና ከ10 ዓመት
በማይበልጥ ጽኑ እስራት ይቀጣል፡ (ምዕራፍ 13 አንቀጽ 64 - (4)
ከበጀት ቁጥጥር የቀጠለ ….
• የበጀት ቁጥጥር የሚያስፈልገዉ የመንግሥት ሀብት ለተገቢና
አግባብ ባለዉ የመንግሥት አካል ለፀደቀ ዓላማ ብቻ
ስለማዋሉ መቆጣጠር ሲሆን አጠቃቀሙም ቁጠባን፣
ብቃትንና ዉጤታማነትን በከፍተኛ ደረጀ ሊያስገኝ በሚችል
መንገድ መፈፀሙን ማረጋገጥ ያስፈልጋል፡፡
የገንዘብ ክፍያ መመሪያ የቀጠለ…
የመንግሥት ሠራተኞች የደመወዝ አከፋፈል፣
የመንግሥት ሠራተኞች ደመወዝ ሊከፈል የሚገባዉ፣
 በመንግሥት ሠራተኞች አስተዳደር መመሪያ መሠረት ለተቀጠሩ፣
 ከመንግሥት መ/ቤቶች ሠራተኞቹ በሥራ ላይ ስለመሆናቸዉ ወር
በገባ እስከ 20ኛ ቀን ድረስ ለፋ/ኢ/ል/መምሪያ/ጽ/ቤት
መረጃዉን ተደራሽ መደረጉን በማረጋገጥ፣
 የሠራተኞችን ዝርዝር መረጃ በአግባቡ በማጣራት የክፍያ ፔይሮል
በማዘጋጀት፣
 የደመወዝ ክፍያ መፈፀም… ወዘተ
5. የጋራ አገልግሎት አሰጣጥና አደረጃጀት መመሪያ
በአሁን ጊዜ ተግባራዊ እየተደረገ ያለዉ ዘመናዊ የፋይናንስ አስተዳደር መረጃ
አያያዝ በዞንና በወረዳ በፋ/ኢ/ል/ሴክተር ብቻ የሚዘረጋ በመሆኑ፣
 በወረዳ በዞን የሚገኙ ባለበጀት መ/ቤቶች መኖር የለባቸዉም፣
 የአገልግሎት አሰጣጡ ወቅታዊ፣ ጥራት ያለዉና ቀልጣፋ ለማድረግ
በአደረጃጀት፣ በሰዉ ኃይልና በሥራ መሣሪያዎች የማጠናከር፣ የአቅም ግንባታ
ሥራዎች የሚሰሩ ይሆናል፣
ከዚህ በላይ የተገለጸዉ ቢኖርም የሥራ ባህሪያቸዉ ለዚህ ሥራ አመቺ ለማይሆኑ
መ/ቤቶች ብቻ ከጋራ አገልግሎት ዉጭ እንዲስተናገዱ ማድረግ የሚቻለዉ
ባለበጀት መ/ቤት በጋራ አገልግሎት ማዕቀፍ ዉስጥ መካተት የማይችልበት
ተጨባጭና አስገዳጅ ምክንያት መኖሩ በቢሮ ተረጋግጦ ሲፈቀድ ነዉ፡፡
የዚህ መመሪያ ዋና ዓላማ
• የመንግሥት በጀት፣ገንዘብና ንብረት በአግባቡ፣ በቁጠባና ዉጤታማ በሆነ መልኩ መጠቀም
ማስቻል፣
• የሰዉ ኃይል ዉጤታማ በሆነ መልኩ በመጠቀም ጥራት ያለዉ የፋይናንስ አስተዳደርና አሰራር
እንዲሁም የተቀናጀ የግዥና የንብረት አስተዳደር ሥርዓት እንዲኖር ማድረግ፣
• በየመስሪያ ቤቱ በፋይናንስ አስተዳደር ሥራ ላይ የተሰማራዉን የሰዉ ኃይል በአንድ ማዕከል
በማደረጀት ጥራት ያለወ አፈጻጸም እንዲኖር ለማስቻል፣
• አስፈጻሚ መ/ቤቶች ከድጋፍ ሰጪ አገልግሎት መስጠት ተግባራት ወጥተዉ በዋነኛነት
የተቋቋሙበትን ዓላማ እንዲፈጽሙ ማስቻል፣
• የመንግሥት ፋይናንስ አስተዳደር መረጃዎች በዘመናዊ መልኩ በጥራት እንዲደራጁ እና የመረጃ
ፍሰቱን ልዉዉጥ ቀልጣፋ እንዲሆን ማድረግ፣
• በጥቅል ግዥ አሰራር የመንግሥትን ወጪን ለመቀነስና ለመቆጠብ እንዲሁም ጥራት ያላቸዉን
ዕቃዎችና አገልግሎቶች በተሻለና በተመጣጣኝ ዋጋ ግዥ እንዲፈፀም ማድረግ፣
• ለባለበጀት መ/ቤቶች በገንዘብ ማስተላለፍ ሂደት ይጠፋ የነበረዉን ጊዜ በመቀነስ ቀልጣፋ
የአገልግሎት አስጣጥ ማስፈን፣
• የተጠቃለለ የመንግሥት ገቢ በወቅቱ ተሰብስቦ ለታለመለት ዓላማ እንዲዉል ማድረግ፣
• የመንግሥት ንብረት በአግባቡ መጠቀም፣ ማስተዳደር፣ መጠበቅና የአገልግሎት ጊዜዉን ሲጨርስ
በወቅቱ እንዲወገድ ማስቻል፣
6. የዉስጥ ኦዲት የሙያ ሥነምግባር መመሪያ
የዉስጥ ኦዲተሮች ቀጥሎ የተመለከቱትን የሥነ-ምግባር መርሆዎችን መጠበቅ ይኖርባቸዋል፣
 ተአማኒነት፣ ሥራዎችን ሲያካናወኑ በታማኝነት፣ በትጋት፣ በኃላፊነት፣ የሕግ ማዕቀፎችን በማክበር፣
መሆን አለበት፣
 ገለልተኝነት፣ በራስ ጥቅም/በሌሎች ጠልቃ ገብነት ትክክለኛና ሚዛናዊ ያልሆነ አስተያየት ከመስጠት
መቆጠብ፣ የኦዲት ዋጋን በሚያሰጠዉ ጉዳይ ዉስጥ ያለመግበት፣ የኦዲተርን ሙያ ሊያዳክም የሚችል
ሥጦታ አለመቀበል፣ በኦዲት ወቅት የተገኙ ፍሬ ነገሮችን ሳይዛቡ/ሳይጓድሉ ሪፖረት ማቅረብ፣
 ምስጥርን መጠበቅ፣ ኦዲተሮች በሕግ አግባብ/በኃላፊ ካልተፈቀደ በስተቀር በሥራ አጋጣሚ
የሚገኘዉን መረጃ በምስጥር የመጠበቅ ኃላፊነት አለባቸዉ፣ በሥራቸዉ አጋጣሚ የሚያገኙትን
የመ/ቤቱን መረጃ ለግል ጥቅም ማስገኛ ወይም ህግን ለሚቃረን /ከመ/ቤቱ ሥነምግባር ዓላማዎች ጋር
ለሚቃረን ተግባር ያለማዋል፣
 ብቃት፣ ሙያዉ የሚፈቅደዉን ዕዉቀት፣ ክዕሎትና ልምድ በሥራ ላይ ማዋል፣ አስፈላጊዉን
ዕዉቀት፣ ክዕሎት እና ልምድ በሚያመሉበት የሥራ መስክ ብቻ መሳታፍ እና ብቃታቸዉን ሁልጊዜ
ማሻሻል ያስፈልጋል፣

7. የመንግሥት መስሪያ ቤቶች የደረሰኞችና የሌሎች የህትመት አያያዝና
አስተዳደር መመሪያ ቁጥር 27/2010
• የህትመት አያያዝና አስተዳደር ሥርዓት ተግባራዊ በማድረግ ለመንግሥት መስሪያ ቤቶች
የግልጸኝነት ሥርዓት በመፍጠር ለህትመቶች አግባብነት ያለዉን ጥበቃ ማድረግ እንዲችሉ፣
• በህትመት አያያዝና አስተዳደር ሥርዓት ላይ ለሚፈጠር ጥፋትና የማጭበርበር
ተግባርየተጠያቂነት ሥርዓት በሥራ ላይ ለማዋል፣
• የመንግሥት መስሪያ ቤቶች በህትመት አያያዝ፣ ስርጭት፣ አመላለስ፣ እንዲሁም የህትመት
አደረጃጀት በሚመለከት ወቅታዊና ትክክለኛ መረጃ ላይ በመመስረት ጠንከራ
የቁጥጥር፣የክትትልና የግምገማ ስርዓት እንዲያደርጉ ለማስቻል፣
• የፋይናንሰ እና የንብረት እንቅስቃሴ የተከናወነባቸዉና የተሰራባቸዉ ህትመቶች ሥርዓት ባለዉ
መንገድ ደህንነታቸዉ ተጠብቆ እንዲያዙ ወይም እንደ አስፈላጊነቱ እንዲወገድ ለማድረግ
እንዲቻል፣
8. የመስተንግዶ በጀት አመዳደብና አጠቃቀም መመሪያ
የመመሪያዉ ዓላማ፤
 የመስተንግዶ በጀት አመዳደብና አጠቃቀም ሁኔታ ሥርዓት ባለዉ
መልክና ወጥነት ባለዉ አሰራር ተግባራዊ እንዲደረግ ለማስቻል፣
 የበጀት ብክነትን በመቆጣጠር የክልሉ የሀብት አጠቃቀም ይበልጥ
በዉጤታማነት እንዲተገበር ለማድረግ፣
 በየደረጃ ለሚገኙ የአስተዳደር እርከኖች ሊኖር የሚገባዉን የሥራ
ኃላፊነትና ተጠያቂነት እንዲኖር ለማድረግ፣
 የመስተንግዶ በጀት አመዳደብና አጠቃቀም የቁጥጥር ሥርዓትን
በማጠናከር የሚስተዋሉ የአፈጻጸም ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት ነዉ፡፡
 በየአስተዳደር እርከኑ የሚገኙ የመ/መ/ቤቶች በየዘርፉ የተጠሉ ግቦችን
ለማሳካት የፀደቀላቸዉን ዓመታዊ በጀት መሠረት በማድረግ ለዋና ዋና
የወጪ መደቦች በጅታቸዉን በዝርዝር ሊመድቡ ይገባል፡፡
የመስተንግዶ በጀት የሚከተሉትን ያካትታል
• ከዉጭና ከዉስጥ ለሚመጡ እንግዶች የሚደረግ የሻይ፣ ቡና፣ዉሃ
መስተንግዶ፣
• በተለያዩ ሥልጠናዎች ላይ የሚደረግ የሻይ፣ ቡና፣ ዉሃ፣
• ለምክር ቤትችና ለሴክተር ጉባኤዎች የሚደረግ መስተንግዶ፣
• ለልዩ ልዩ ማቀጣጠያ ሠነድ የግንዛቤ ማዳበሪያ በዉይይት
መድረኮች የሚደረግ፣
• ለሲምፖዚያሞች፣ ለባህላዊ የዘመን መለወጫ በዓለት ዝግጅት
የሚደረግ፣
• በልዩ ልዩ ዘርፎች ብሔራዊና ክልላዊ ዓመታዊ የበዓለት ቀን
አከባበር ላይ የሚደረግ፣
• ለስፖርታዎ ዉድድር ሻምፕዮኖች ለተወዳደረሪዎች የሚደረግ፣
በዞን፣ በወረዳ፣ በኮሌጆች እና በተቋማት የተፈቀደዉ የመስተንግዶ ወጪዎች

ተ.ቁ በዞን ና ወረዳ ማዕከል የገንዘብ


ጣሪያ
ዋና አስተዳደሪዎችና ሀዋሳ ከተማ ካንቲባ/ምክትሎችና ዋና አፈ ጉባኤ፣ከፍተኛ 3200/1000
ፍ/ቤ/ፕሬዝዳነት
መምሪያ ኃላፊዎች/ሀዋሳ ከተማ ማዘጋጃ ቤት ሥራ አስኪያጅ 600
የዞን ም/መምሪያ ኃለፊ፣ የዋና አስ/አማካሪ፣ የአስ/ጽ/ቤት ኃላፊና ምክ/አፈ ጉባኤ፣ 400
የዞን ዋና ሥራ ሂደቶች፣ የወረዳ ሴ/ጽ/ቤት ሃላፊ፣ በወረዳ የማዘ/ቤት ሥ/አስ 300
የወረዳ ዋና አስተዳደሪ/ምክ/አስ እና ዋና አፈ ጉባኤ፣ የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ፕሬ 1000/400
ለ1ኛ ደረጃ ከተማ ከንቲባ/ ምክትል ከንቲባ፣ ተቋማትና የመጀ/ደረጃ ሆስፒታሎች 1500/600
ኮሌጆችና ጄነራል ሆስፒታሎች 800
ለ1ኛ ደረጃ ከተማ ሴ/ጽ/ቤት ኃላፊና የማዘጋጃ ቤት ሥ/አስኪያጅ 500
የቅርንጫፍ ጽ/ቤት 300
8. የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች የበጀት አመዳደብና የወጪ ቅነሳ
አጠቃቀም መመሪያ
• የትርፍ ሰዓት ክፍያን በተመለከተ፣
• የቢሮ አላቂ ዕቃዎች ግዥን በተመለከተ፣
• የህትማት ወጪን በተመለከተ፣
• የነዳጅና ቅባት ወጪን በተመለከተ፣
• የተሸከርካሪ ጥገና ወጪን በተመለከተ፣
• የፅዳትና አላቂ እቃዎች ግዥን በተመለከተ፣
• የመስተንግዶ ወጪን በተመለከተ፣
• የማስታወቂያ ወጪ በተመለከተ፣
• የግንባታ፣ የማሽነርና የተሸከርካሪ ኪራይ ወጪ በተመለከተ፣
• የስልክ ወጪን በተመለከተ፣
የበጀት አመዳደብና የወጪ ቅነሳ አጠቃቀም የቀጠለ…

• የሥልጠናና የስብሰባ ወጪን በተመለከተ፣


• የቢሮ ኪራይ ወጪን በተመለከተ፣
• የቋሚ እቃዎች ግዥ ወጪን በተመለከተ፣
• የድጋፍና የሥጦታ ወጪን በተመለከተ፣
• የዉሃና የኤልክትሪክ አገልግሎት ክፍያ ወጪን በተመለከተ፣
• የካፒታል በጀት ወጪን በተመለከተ፣
• የንብረት አስተዳደርን በተመለከተ፣
• የፋ/ኢ/ል/ሴክቴር ተግባርና ኃላፊነትን በተመለከተ፣
• የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች ተግባርና ኃላፊነትን በተመለከተ፣
• የአስተዳደር እርከን ዋና አስተዳደሪዎችና ካንቲባዎች ተግባርና ኃላፊነትን
በተመለከተ፣
›መሰግናለሁ

32

You might also like