You are on page 1of 13

በየካ ክፍለ ከተማ አስተዳደር

የወረዳ 07 ቤቶች አስተዳደር ጽ/ቤት

የ2016 በጀት አመት እቅድ

ነሃሴ፣ 2015 ዓ.ም


አዲስ አበባ
ኢትዮጵያ
ማውጫ
• ገፅ
• ክፍል አንድ፡-…………………………………………………………………………………… 1
• 1.2.1. የቢሮው ራዕይ፤ ተዕልኮ እሴትና የቢሮው ተግባርና ኃላፊነት -------------------------------------- 4
• 1.2.3. ቤት ልማትና የአሰራር ስርዓት ዘርፍ ------------------------------------------------------------------ 5
• 2. የተቋሙ ዋና ዋና ግቦች፣ አላማዎች እና ተግባራት-- --------------------------------------------------6
• ግብ 1፡- ተቋማዊ ማስፈጸም አቅም፣ ሃብት አጠቃቀም እና አገልግሎት አሰጣጥ አሰራር ማጎልበት /15%/ 6
• ግብ 2፡- የቤት ልማት አቅርቦት ማሳደግ /45%/-------------- Error! Bookmark not defined.
• ግብ 3፡- የመንግስት ቤቶች የማስተዳደር፣ ለተጠቃሚዎች የማስተላለፍ፣ የቤት ማህበራት እና የመረጃ አያያዝ አሠራር ስርዓትን
ማሻሻል /40%/፣ --------------------------------------------------------------------------------8
• ክፍል 3 --------------------------------------------------------------------------------------------------------------10
• 3. የድርጊት መርሃ ግብር---------------------------------------------------------------------------------- 10
• ክፍል 4 --------------------------------------------------------------------------------------------------------------19
• 4. የዓመቱን ዕቅድ ለማሰካት የሚተገበሩ ማስፈጸሚያዎች------------------------------------------- 19
• 4.1. የተቋማዊየለውጥ (Transformation)አጀንዲዎች---------------------------------------------------19
• 4.2. የፖሊሲሪፎርምአጀንዳዎች----------------------------------------------------------------------------- 19
• 4.2.1. አዲዲስፖሊሲዎች--------------------------------------------------------------------------------------- 19
• 4.2.2. ነባርፖሊ-------------------------------------------------------------------------------------------------
19
• 4.3. የኢኮቴናዲጅታላይዜሽንአጀንዳዎች፡------------------------------------------------------------------ 20
• 4.4. የአፈጻጸምክትትልናግምገማሥርዓት----------------------------------------------------------------- 20
• 4.5. የግምገማና ሪፖርት ስርዓት---------------------------------------------------------------------------- 21
ክፍል አንድ

– መግቢያ
• በ2016 በጀት ዓመት ይሰራሉ ተብሎ የተያዙ ዋና ዋና ግቦች ተቋማዊ ማስፈጸም አቅም፣ ሃብት አጠቃቀም እና አገልግሎት አሰጣጥ አሰራር

ማጎልበት፣ የቤት ልማት አስተዳደር ማሳደግ ፣ለተጠቃሚዎች የማስተላለፍ እና የቤቶች የመረጃ አያያዝ ስረዓትን ማሻሻል ሲሆኑ በመኖሪያ

ቤት ህብረት ስራ ማህበራት ቢሮው በ2005 ዓ.ም የ20/80 እና የ40/60 ከተማ አስተዳደሩ ባወረደው 30/70 ፕሮግራም መሰረት 26

አባዎራዎች የጋራ መኖርያ ቤት ህብረት ስራ እንዲደራጁ መረጃ አደራጅተን ለክ/ከተማ ልከናል፡፡ በዚህ በጀት ዓመትም ቢሮው

የሚያስቀምጠው አቅጣጫ መሰረት መረጃ የማደራጀት ስራ ይሰራል፡፡ የመንግስት ቤቶች መረጃ 1135 በማደራጀት እና ወደ በለፀገው ሶፍት

ዌር የማስገባ ስራ ተከናውኑዋል፡፡ ስለሆነም ወደ በለጸገው ሶፍት ዌር የገባውን መረጃ በ2016 የማረም እና የማስተካከል ስራ ይሰራል፡፡

• የመንግስት መኖሪያ ቤቶችን፣ንግድ ቤቶችን እንዲሁም የጋራ መኖሪያ ቤቶችን መረጃ በNUHDM SYSTE Mሙሉ በሙሉ የማስገባት ሥራ

እና ለ 1135 ቤቶች የውል እድሳት ሥራ ይከናወናል፡፡

• ከመንግስት መኖሪያ ቤቶች እና /ንግድ ቤቶች 4 ሚሊዮን ብር ገቢ ለመሰብሰብ ለመሰብሰብ ትኩረት ተሰጥቶ ይሰራል፡፡

• የመንግስት ቤቶች በህገወጥ እንዳይያዙ መቆጣጠር እና የተያዙትን ቤቶች በማስለቀቅ ህጋዊ በሆነ መንገድ ለሚገባቸው ዜጎች የማስተላለፍ

ሥራ ይሰራል፡፡ እንዲሁም ለልማት ተነሽና የተፈጥሮ አደጋ ተነሽዎች የጋራ መኖሪያ ምትክ ቤት በምርጫቸው መሰረት እንዲስተናገዱ

ከፍተኛ ትኩረት ይሰጣል፡፡


የልማት ዕቅዱ እንድምታዎች እና የሚጠበቁ ውጤቶች
• የ2016 ልማት ዕቅዱ የ10 አመቱን ስትራቴጂካዊ ዕቅድ ታሳቢ በማድረግ እና የሚጠበቁ ውጤቶችን የክፍለ ከተማችን የቤት ፍላጎት በመነሳት በዘርፍ ደረጃ ግቦችን በማስቀመጥ
የተዘጋጀ ሲሆን በጥቅሉ የላቀ የቤት ልማት፣ ፍትሃዊ ቤት ማስተለለፍ እና የላቀ የቤት አስተዳደር የሚጠበቁ ውጤቶች ናቸው፡፡
• 1.2.1. የጽ/ቤቱ ራዕይ፤ ተዕልኮ እሴትና የቢሮው ተግባርና ኃላፊነት

• 1.2.1.1. ራዕይ
• በ2017 ዓ.ም የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች አቅም ያገናዘበና ለኑሮ ምቹ የሆነ የመኖሪያ ቤት ተጠቃሚ ሆነው ማየት፡፡

• 1.2.1.2. ተልዕኮ
• በአዲስ አበባ ከተማ ያለዉን ከፍተኛ የሆነ የመኖሪያ ቤት ፍላጎት ለማሟላት ጥራት ያለውና ወጪ ቆጣቢ ቤት በማስገንባት፣በፍትሐዊነት እንዲተላለፍ በማድረግ፤ ቀልጣፋና
ውጤታማ የቤት አስተዳደር ስርዓት በመዘርጋትና በመተግበር የከተማዋ ነዋሪዎች ተጠቃሚነትን ማሳደግ፡፡
• 1.2.1.3. የጽ/ቤቱ ተግባርና ኃላፊነት
• 1. የጽ/ቤቱን እቅድ ያቅዳል ፣ ይተገብራል ፣ ይገመግማል ፣ በበላይነት ይመራል
• 2. ከቢሮ የሚወርዱ ፖሊሲዎች፣ ዝርዝር የህግ ማዕቀፎች እንዲሁም ስታንዳርድ በወረዳ ተፈጻሚ መሆናቸውን ያረጋግጣል፤ የማሻሻያ ግብዓቶች ያሰባስባል፤
ለሚመለከተው አካል ያስተላልፋል፤ ተግባራዊነቱንም ይቆጣጠራል፤
• 3. የሚያስተዳድራቸውን ቤቶች መረጃ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ይይዛል፤ የመኖሪያ ቤት ዓይነቶችን መደብና ደረጃ ያወጣል፤ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ይሰጣል፤
• 4. የጋራ መኖሪያ ቤት ማህበራት የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በትብብር ችግሮቹ እንዲወገዱ ያደርጋል፤
• 5. በወጪ እና ጊዜ ቆጣቢ ለሚገነቡ ግንባታዎች የሚያስፈልገውን ሰፋፊ የመንግስት ቤቶች ይዞታ ይለያል ቁጥጥር ያደርጋል፡፡
• 6. በአነስተኛና መካከለኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ያሉ ነዋሪዎች በተለይም ሴቶች፣ አካል ጉዳተኞች በቤት ልማት ፍትሐዊ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ይሰራል፡፡
• 7. የመንግስት ቤቶች አላግባብ ወደ ግል እንዳይዞሩ ከፍተኛ ጥበቃ ያደርጋል፣
• የሚያስተዳድራቸውን ቤቶች ያከራያል፤ እንዲጠገን ያደርጋል፣
• በጋራ መኖሪያ ቤቶች ህብረተሰቡን የሚያውኩ እና ህገ-ወጥ ተግባራትን የሚፈፅሙ አካላትን ከሚመለከተው አካል ጋር በመሆን ቁጥጥር
ያደርጋል፤ እርምጃ እንዲወሰድ ያደርጋል፤
• የከተማ አስተዳሩ ንብረት የሆኑ የመኖሪያ፣ ንግድ ቤቶች፣ ለኪራይ አገልግሎት ተገነቡ ቤቶች እንዲሁም የጋራ መኖሪያ ቤቶች በህገ-ወጥ
መንገድ ከያዙት አካላት ያስለቅቃል፡፡
– የተቋሙ እሴቶች

ጥራት ያለው የቤት አቅርቦት፣
• ወጭ ቆጣቢነት፣
• ለአካባቢ ጥበቃና ለሥራ ላይ ደህንነት ትኩረት መስጠት፣
• ተገልጋይ ተኮርና አክብሮት፣
• ፍትሀዊነት፣
• ግልፅነት፣
• ተጠያቂነት

– የቤቶች ልማት ዘርፍ የትኩረት መስክ


• የላቀ የቤት ልማት፣
• ፍትሃዊ ቤት ማስተለለፍ፣
• የላቀ የቤት አስተዳደር ናቸው፡፡

• ቤት ልማትና የአሰራር ስርዓት ዘርፍ
• በዚህ ዘርፍ የመንግስት መኖሪያ እና ንግድ ቤቶች፣ የቀበሌ ቤቶች እና የጋራ መኖሪ ቤቶችን በዘመናዊ እና ከብክነት በፀዳ ሥርዓት መረጃ
ማስተዳደር፣ ውጤታማ የገቢ መሰብሰቢያ ስርዓት መዘርጋት እና ተግባራዊ ማድረግ፣ ፍትሐዊ የቤት ማስተላፍ ሥርዓት መዘርጋት እና
ተግባራዊ ማድረግ እንዲሁም የቤት ችግር የሚፈታበትን አስራር መዘርጋት፡፡


• ክፍል 2
• የተቋሙ ዋና ዋና ግቦች፣ አላማዎች እና ተግባራት
• ግብ 1፡- ተቋማዊ ማስፈጸም አቅም፣ ሃብት አጠቃቀም እና አገልግሎት አሰጣጥ አሰራር ማጎልበት /15%/
• ዓላማ 1፡- የዕቅድ ዝግጅት፣ የክትትልና ግምገማ እና የስታቲስቲክስ መረጃ አስተዳደር አሰራር ማሻሻል፣
• የሚከናወኑ ተግባራት፡-
• ወቅቱንና ጥራቱን የጠበቀ ዕቅድና ሪፖርት ማዘጋጅት፣ ዕቅድ 19
• የክትትልና ግምገማ ስርዓት ትግበራ፣ ዕቅድ 4

• ዓላማ 2፡- የሰው ሀብት ልማት እና አስተዳደር አሰራርና ውጤታማነት ማሻሻል፣
• የሚከናወኑ ተግባራት፡-
• አሠራርን የጠበቀ የሰው ኃይል ስምሪት፣ ዕቅድ 100%
• የአመራሩንና የሠራተኛውን አቅም መገንባት፣ ዕቅድ 100%
• የውስጥ የማበረታቻ ስርዓት መዘርጋት፣ ዕቅድ 2
• የሰራተኛ እርካታን ማሳደግ፣ዕቅድ 92%

• ዓላማ 3፡- የኢንፎርሜሽን፣ ኮሙኒኬሽን እና ቴክኖሎጂ አሰራርንና ውጤታማነትን ማሻሻል፣
• የሚከናወኑ ተግባራት፡-
• ወረቀት አልባ (ኦቶሜሽን) አሰራርን መተግበር፣ ዕቅድ 50%
• በቴክኖሎጂ በታገዘ የመረጃ ቋት የተደራጀ መረጃ፣ዕቅድ 60%
• የተሻሻለና ደህንነቱ የተረጋገጠ የኢኮቴ አጠቃቀም፣ዕቅድ 60%





• ዓላማ 4፡- የሚደረገውን ድጋፍና ክትትል ማሻሻል፣
• የሚከናወኑ ተግባራት፡-
• የወረዳውን ዕቅድ ከክ/ከተማ ከጽ/ቤት ዕቅድ ጋር ማጣጣም፣ ዕቅድ 2
• በየሩብ ዓመቱ ከባለድርሻ አካላት ጋር ሪፖርት መገምገም፣ ዕቅድ 4
• በየሩብ ዓመት አፈጻጸም ከወረዳ ባለሙያዎች ጋር በጋራ መገምገም፣ዕቅድ 4
• ለልዩልዩ አደረጃጀቶች እና ዘርፎች ፣ የአቅም ግንባታ ድጋፍ መስጠት፣ዕቅድ 4
• ዓላማ 5፡- የስነ ምግባርና ፀረ-ሙስና የክትትል ሥራዎችን ማሻሻል፣
• የሚከናወኑ ተግባራት ፡-
• በብልሹ አሰራር ዙርያ ጥቆማ ከተደረገባቸው ውስጥ ማስተካከያ የተደረገባቸው፣ ዕቅድ 100%
• ለብልሹ አሰራር የተጋለጡ አሰራሮች በጥናት በመለየት የማሻሻያ ሀሳብ ማቅረብ፣ዕቅድ 1
• የሀብት ምዝገባ ያካሄዱ አመራሮች እና ባለሞያዎች፣ ዕቅድ 100%
• ዓላማ 6፡- የሴቶችና ማሕበራዊ ተሳታፊነትንና ተጠቃሚነትን ማሻሻል፣
• የሚከናወኑ ተግባራት፡-
• ወደ አመራር የመጡ ሴት ሰራተኞች ብዛት ማሳደግ፣ ዕቅድ 2%
• ሥልጠና ያገኙ ሴት ሰራተኞች ድርሻ ማሳደግ፣ ዕቅድ 100%
• ለአካል ጉዳተኛ ሰራተኞችና ተገልጋዮች ምቹ የስራ ሁኔታና ቦታ መፍጠር፣ ዕቅድ 100%

• ዓላማ 7፡- የበጎ አድራጎት እና የማህበረሰብ አገልግሎት ሥራዎችን ማሻሻል፣
• የሚከናወኑ ተግባራት፡-
• ለተለያዩ ማህበራዊ ቀውሶች የተደረገ ድጋፍ፣ዕቅድ 4,000ብር
• የአቅመ ደካማ ቤተሰብ ቤት ማደስ ፣ ዕቅድ 26 ቤት



• ዓላማ 8፡-የህግ ጉዳዮችን በተሻለ ሁኔታ መምራት፤
• የሚከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት፡-
• 1. የፍርድ ቤቶች ክርክር መከታተል100%
• 2. የሚዘጋጁ መመሪያዎች ተፈፃሚ ማድረግ፣ ዕቅድ 100%
• 3. በህግ ጉዳዮች ላይ ለአመራሩ እና ለፈጻሚው የግንዛቤ ማስጨበት ስልጠና መስጠት፣ ዕቅድ 1
• 4. ወንጀል ሲፈፀም ከሚመለከተው የፍትህ አካል ዘንድ ቀርቦ አቤቱታ እና ማስረጃ ማቅረብ፤ ዕቅድ 100%
• 5. በሙስና ወንጀሎች ዙሪያ የመጡ ጥቆማዎችን በማደራጀት ለፌደራል የሥነ-ምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሽን ማሳወቅ፣ ዕቅድ
100%
• 6. የተቋሙ ኦዲት ግኝቶች ላይ እየተወሰደ ስላለው እርምጃ ክትትል ማድረግ፣ ዕቅድ 100%
• 7. በድርድር ቢያልቁ የተቋሙ ጥቅም በላቀ ሁኔታ ሊከበርባቸው የሚችሉ ጉዳዮችን በመለየት በሚመለከተው አካል ሲፈቀድ
ጉዳዮችን በድርድር መጨረስ፣ ዕቅድ 100%
• 8. በተከፈቱ መዝገቦች ላይ ተገቢውን ክትትል ማድረግ፣ ዕቅድ 100%
• 9. የተወሰነ ውሳኔን ተከታትሎ በወቅቱ ማስፈጸም፣ ዕቅድ 100%
• 10. በሌብነት ተግባር ውስጥ ገብተው የተገኙ አመራሮችንና ፈጻሚዎችን ተጠያቂ ማድረግ፣ ዕቅድ 100%
• ግብ 2፡- የመንግስት ቤቶች የማስተዳደር፣ ለተጠቃሚዎች የማስተላለፍ፣ የቤት ማህበራት እና የመረጃ አያያዝ አሠራር ስርዓትን ማሻሻልና
ማስፈፀም /40%/፣
• ዓላማ 1፡- 6 የመንግስት ቤቶችን ለተጠቃሚዎች ፍትሐዊ በሆነ መንገድ ማስተላለፍ፣ 1135 የመንግስት ቤቶችን ውል ማደስ እና 4 ሚሊየን ብር
ገቢ ማሰባሰብ፤
• የሚከናወኑ ተግባራት፡-
• 1) ለተጠቃሚዎች የሚተላለፉ የኪራይ ቤቶች፣ ዕቅድ 6
• 2) ውል የሚታደስላቸው በመንግስት የሚተዳደሩ ቤቶች፣ ዕቅድ 1135
• 3) ከመንግስት ቤቶች የሚሰበሰብ ገቢ፣ ዕቅድ 4 ሚሊዮን ብር
• 4) ለቤት ችግረኞች ቤቶችን በፍትሐዊ መንገድ ማስተላለፍ፣ ዕቅድ 6
• ዓላማ 2፡- 1135 የመንግስት ቤቶች እና 1990 የጋራ መኖሪያ ቤቶች አስተዳደርና የመረጃ አያያዝ ስርዓትን ማሻሻል፤
• የሚከናወኑ ተግባራት፡-
• የተገነቡ የመንግስት ቤቶችን መረጃ በUHDM system software መመዝገብ /በዘመናዊ መንገድ ማደራጀት/፣ ዕቅድ በቁጥር 1135
• የተገነቡ የጋራ መኖሪያ ቤቶችን መረጃ በUHDM system software መመዝገብ /በዘመናዊ መንገድ ማደራጀት/፣ ዕቅድ 1990፣
• የመንግስት ቤቶች በህገወጥ መንገድ እንዳይያዙ መቆጣጠር፣ የተያዙትንም በማስለቀቅ ወደ ህጋዊ ስርዓት መመለስ፣ ዕቅድ 100%፣
• በልማት፣በተፈጥሮና በሰው ሰራሽ አደጋ ለሚነሱ ሰዎች ምትክ ቤት መስጠት፣ ዕቅድ 100%፣
• ከሚተላለፉ ቤቶች ሴቶች 30%፣ አካል ጉዳተኞች 5% ተግባረዊ ማድረግ ማድረግ፣ዕቅድ 100%፣
• ለመንግስት ቤቶች ካርታ እንዲሰራላቸው መረጃ አደራጅቶ መስጠት፣ ዕቅድ 100%
• የወጡ የቤት ልማት ስትራቴጅዎችን መተግበር ዕቅድ 100%፣
• በቤቶች ዙሪያ የሚታዩ ችግሮችን ሊፈታ የሚችል ጥናት ማጥናት፣ ዕቅድ 1፣
• የቤቶች ልማት ፕሮግራም ተዋናዮች በሶስት ርዕሶች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መሳተፍ፣
• የተዘረጉ የአሰራር ስርዓቶችና የህግ ማዕቀፎች መተግበራቸውን በክትትል መለየት፣ ዕቅድ 100%፣
• ክፍተት ያለባቸውን የአሰራር ስርዓቶችና የህግ ማዕቀፎች የመፍትሄ ሀሳብ ለሚመለከተው ክፍል ማቅረብ፣ዕቅድ 100%፣
• ዓላማ 3፡- የጋራ መኖሪያ ቤቶች የቤት ባለቤት ማህበራትን አሠራርና መረጃ አያያዝን 100% ማሻሻል፤

• የሚከናወኑ ተግባራት፡-
• በምዘና መስፈርት ከተለዩ የጋራ መኖሪያ ቤት ባለቤቶች ማህበራት ውስጥ ምርጥ አሠራር ያላቸው እና ሞዴል የሚሆኑ 3(ሶስት) ማህበራትን ለይቶ
በማውጣት ምርጥ ተሞክሮ መቀመር እና ማስፋፋት፣ ዕቅድ 1 ጊዜ
• ዓላማ 4፡- የ699 የቤት ፈላጊዎችን ን መረጃ አስተዳደር ሥርዓትን ማሳደግ፤የሚከናወኑ ተግባራት፡-
• የ699 የቤት ፈላጊዎችን መረጃ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ማደራጀት እና ማስተዳደር፣
• የ1990 የጋራ መኖሪያ ቤት ተጠቃሚዎች መረጃ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ማደራጀት እና ማስተዳደር፣
• ክፍል 3

• የድርጊት መርሃ ግብር

• ከዚህ በታች የቀረበው የድርጊት መርሐ-ግብር ካላይ በሀተታ የቀረቡትን ግቦች፣ አላማዎች እና ዝርዝር ተግባራት በ2016 ዓ.ም በምን

ያክል መጠን፣ ክብደት እና ጊዜ እንደሚከናወኑ በሚያሳይ ደረጃ የ2016 በጀት አመት እቅድን ማዘጋጀት ተችሏል፡፡

• በድርጊት መርሃ ግብሩ 2 ግቦች፣12 ዓላማዎችና 49 ተግባራት በዝርዝር የተካተቱበት ሲሆን ይህንንም በየወራቱ እና በየሩብ አመት

በማመላከት ድርጊት መርሃ ግብር እንደሚከተለው አስቀምጠናል፡፡















• ክፍል 4
• የዓመቱን ዕቅድ ለማሰካት የሚተገበሩ ማስፈጸሚያዎች
• በ2016 በጀት አመት ለመፈፀም የታቀዱ የየዘርፉ የልማት ግቦችን ውጤታማ በሆነ ደረጃ ለማሳካት እና የተቀመጡ አላማዎች
ጋር ለመድረስ ይቻል ዘንድ ከዚህ በታች የተዘረዘሩት አብይ ጉዳዮችን የማስፈጸሚያሥልችናሂደቶችንመከወን አስፈላጊ ነው።
– የተቋማዊየለውጥ (Transformation)አጀንዲዎች
• የተዘጋጀውን እቅድ ወደ ተግባር ለመቀየር የተለያዩ የለውጥ ሥራዎችን ማከናወን የሚያስፈልግ ሲሆን እነዚህን የለውጥ
ሥራዎች በአግባቡ በመተግበር ከእቅዱ የሚፈለጉ ውጤቶችን እና ለውጦችን እውን ለማድረግ ይረዳል፡፡ ተቋማዊ ለውጥ
ለማምጣት የሚተገበሩ የተለያዩ አጀንዳዎችና ለውጦች ያሉ ሲሆን ከተቋማችን አሰራርና ተግባር አንጻር ዋና ዋናዎቹ፡-
• የመልካም አስተዳደርን የሚያሰፍኑ እንዲሁም የአገልግሎት አሰጣጡን የሚያዘምኑ ስርዓቶችን መዘርጋት፣
• ጊዜን፣ ሀብትን እና የሰው ኃይል ጉልበትን የሚቆጥቡ አዳዲስ የግንባታ ቴክኖሎጂዎችን መተግበር፣
– የፖሊሲ ሪፎርም አጀንዳዎች
• አዲዲስፖሊሲዎች
• ተቋማችን ባለው የረጅም ጊዜ ልምድ በመነሳት የቤት ልማትን አስመልክቶ የሚዘጋጁ ፖሊሲዎች እንዲዳብሩ የሚያስችሉ
ግብዓቶችን በማቅረብ እና በመሳተፍ ድጋፍ ያደርጋል፡፡
• ነባርፖሊሲ
• ከቤት ልማቱ ጋር ተያያዥነት ያላቸው ፖሊሲዎችን በመለየት ከከተማችን ነባራዊ ሁኔታ ጋር በማጣጣም እንዲተገበሩ
እንዲሁም የምንመራባቸው ደንቦች፣ መመሪያዎች እና አሰራሮች ፖሊሲዎቹን የተመሠረቱ እንዲሆን ይደረጋል፡፡



– የኢኮቴና ዲጅታላ ይዜሽን አጀንዳዎች
• የተቋማችን የቤት መረጃዎች በዘመናዊ የመረጃ ቋት (DATA BASE) ለማስተዳደር የሚያስችል
ማዕከላዊ መረጃ ማደራጃ (DATA CENTER) ፡፡
• የውስጥ ሥራዎችን የተመለከቱ የመረጃ ልውውጥ በቴክኖሎጂ /በኔትወርክ/ በማገናኘት ከእጅ ንክኪ ነፃ
የሆነ የአሠራር ሥርዓት መዘርጋት የሚያስችል መሠረተ ልማት ይገነባል፡፡
• የዘመናዊ ቴክኖሎጂ ግብአቶችን እና ሀብቶችን በአግባቡ ማስተዳደር እና የመጠገን ስራዎችን በመስራት
የአገልግሎት አሰጣጥ እንዳይቆራረጥ የማድረግ ሥራ ተደራሽ እንዲሆን ይደረጋል፡፡

– የአፈጻጸምክትትልናግምገማሥርዓት
• የክትትል፣ ድጋፍና ግምገማ ስርዓት፡-
• የጽ/ቤቱ አጠቃላይ ሥራዎች በተያዘው ዕቅድ መሠረት እንዲተገበሩ የበላይ አመራሩ በጀነራል ካውንስል
በየ15 ቀን እየገመገመ የማስተካከያ እና የማበረታቻ ድጋፍ ያደርጋል፤ ውሳኔ ይወስናል፡፡
• የጽ/ቤቱ ሰራተኞች የቤት አስተዳደር ስርዓቱን ክትትልና ድጋፍ ያደርጋሉ፣
• የለውጥና መልካም አስተዳደር ሰራዎች የአቻ ፎረም ውጤታማነት፣ የለውጥ ሥራ አተገባበር እና
አገልግሎት አሰጣጥ አፈጻጸምን እየገመገመ የማስተካከያ እርምጃዎች እንዲወሰዱ ድጋፍ እና ክትትል
ያደርጋል፣
• የዕቅድ ዝግጅት፣ ክትትልና ግምገማ ቡድኑ የዕቅድ አፈጻጸምን እየገመገመ የማስተካከያ እርምጃዎች
እንዲወሰዱ ድጋፍ ክትትል ያደርጋል፣
– የግምገማና ሪፖርት ስርዓት
• በጽ/ቤቱ ስር ያሉ ቡድኖች ተጠሪ የወረዳ ቤቶች አስተዳደር ጽ/ቤቶች ወርሃዊ፣ የሩብ አመት፣ የግማሽ አመት
እና አመታዊ የተገመገመ የጽሁፍ ሪፖርት በማዘጋጀት ጽ/ቤቱ ኃላፊዎች በወቅቱ ያቀርባሉ፡፡
• በሚቀርቡ ሪፖርቶች እና የተግባር ክንውንን መሠረት በማድረግ በተቋሙ የበላይ አመራር፣ በሚመለከታቸው
ቡድን እና በክፍለ ከተማ አስተዳደሩ ስልጣን በሰጣቸው ተቋማትየዕቅድ አፈጻፀም በየሩብ
አመቱእንዲገመገም ይደረጋል፡፡
ማጠቃለያ
• የመጠለያ ችግር ያለባቸውን የህብረተሰብ ክፍሎች የቤት ባለቤት የማድረግ ጉዳይ ትልቁ ፈተናችን እንደሆነ
እንገነዘባለን፡፡ ስለሆነም ጊዜና ወጪ ቆጣቢ ቤቶች ከተማው ጋር በመተባባር እና በመስራት ፍትሀዊ የቤት
ማስተላለፍ ስራ መስራት ያስፈልጋል፡፡
• በወረዳ አቅም የሚሰሩ ስራዎችን በትኩረት መስራት ይገባናል፡፡ በህገ ወጥ የተያዙ ቤቶችን በማስለቀቅ በከፋ
ችግር ውስጥ ላሉ ወገኖች 8 የተገመገሙ መረጃቸውችን እንዲተላለፉ ተደርጉዋል፡
• ይህን ተግባራዊ ለማድረግ የብልሹ አሰራር አመለካከትና ተግባር በመድፈቅ፣ የሰራዊት ግንባታና የለዉጥ
ስራዎችን ትኩረት በመስጠት፣ መልካም አስተዳደር በማስፈን፣ የአግልግሎት አሰጣጥ ሂደትን በማሻሻል፣
ክፍተት የሚታይባቸውን ፈፃሚዎች፣ ቡድን መሪዎችና ወረዳዎች በመደገፍ፣ በአፈፃፀማቸዉ የተሻሉትን
በማበረታት፣ የተሻለ አሰራርና ተሞክሮዎችን በማስፋት፣ ለህዝብ ክንፍ በቂ ክትትልና ድጋፍ በማድረግ ዕቅዱ
ዉጤታማ ማድረግ ይጠበቅብናል ስለሆነም ሁሉንም አካላት ርብርብ እንዲያደርግ ጥብቅ ክትትል
ይደረጋል፡፡

You might also like