Professional Documents
Culture Documents
ኡሪም መተዳደሪያ ደንብ
ኡሪም መተዳደሪያ ደንብ
0|Page
ማውጫ
መግቢያ .........................................................................................................................................................................1
ደንብ አንድ፤ ስያሜ .......................................................................................................................................................2
ደንብ ሁለት፤ ትርጓሜ ....................................................................................................................................................2
ደንብ ሶስት ፤ የሕብረቱ ዓላማና ተግባር ........................................................................................................................2
ደንብ አራት ፤ የሕብረቱመዋቅር ....................................................................................................................................3
ደንብ አምስት ፤ የአባልነት መመዘኛ ..............................................................................................................................3
ደንብ ስድስት ፤ የአባላት መብትና ግዴታ ......................................................................................................................3
6.1 መብት ..................................................................................................................................................................3
6.2 ግዴታ ...................................................................................................................................................................4
ደንብ ሰባት ፤ የጠቅላላ ጉባዔ ሥልጣንና ተግባር ...........................................................................................................5
ደንብ ስምንት ፤ የሥራ አመራር ጉባዔ ሥልጣንና ተግባር ..............................................................................................5
ደንብ አሥር ፤ በሥራ አመራር ጉባዔ የሰብሳቢ የሥራ ድርሻ ..........................................................................................7
ደንብ አሥራ አንድ ፤ በሥራ አመራር ጉባዔ የምክትል ሰብሳቢ የሥራ ድርሻ ..................................................................8
ደንብ አሥራ ሁለት ፤ በሥራ አመራር ጉባዔ የጸሐፊው የሥራ ድርሻ ..............................................................................8
ደንብ አሥራ ሦስት ፤ በሥራ አመራር ጉባዔው የሒሳብ ክፍል እና ንብረት ተቆጣጣሪ ድርሻ..........................................9
ደንብ አሥራ አራት ፤ በሥራ አመራር ጉባዔ የልማት፣የንድረክ ዝግጅትና የመርሐ ግብር ክፍል የሥራ ድርሻ...............10
ደንብ አሥራ አምስት ፤ በሥራ አመራር ጉባዔ የስልጠና ክፍል የሥራ ድርሻ .................................................................10
ደንብ አሥራ ስድስት ፤ በሥራ አመራር ጉባዔ የመዝሙርና የሥነ-ጥበብ ክፍልየሥራ ድርሻ ........................................11
16.3 የመዝሙር ክፍል ................................................................................................................................................11
16.4 የሥነ-ጥበብ ክፍል ..............................................................................................................................................12
ደንብ አሥራ ሰባት ፤ በሥራ አመራር ጉባዔው የግንኙነት ክፍል የሥራ ድርሻ ..............................................................13
ደንብ አሥራ ዘጠኝ ፤ በኃላፊነት ሊመረጡ የሚችሉ አባላት መመዘኛ ነጥቦች .............................................................13
ደንብ ሃያ ፤ የቅጣት ደረጃዎች ......................................................................................................................................14
ደንብ ሃያ አንድ ፤ ልዩ ልዩ ድንጋጌዎት ...........................................................................................................................15
21.1 ሥርዓተ-ትምህርት .............................................................................................................................................15
21.2 መምህራን .........................................................................................................................................................15
21.3 መዝሙርና የመዝሙር መሣሪያዎች ....................................................................................................................15
21.4 የንብረት አያያዝ .................................................................................................................................................16
21.5 የሒሳብ ክፍል ....................................................................................................................................................16
21.6 የስብሰባ ጊዜ ......................................................................................................................................................16
ደንብ ሃያ ሁለት ፤ ደንቡ የሚጸናበት ............................................................................................................................16
ደንብ ሃያ ሦስት ፤ ስለደንቡ መሻሻል ............................................................................................................................16
ደንብ ሃያ አራት ፤ የደንቡ የበላይነት ............................................................................................................................16
መግቢያ
መንፈሳዊ አገልግሎት ‹‹መንፈሳዊ (Spiritual)›› እና ‹‹አገልግሎት (Service)›› የሚሉትን ቃላቶች የያዘ
ሲሆን ‹‹መንፈሳዊ›› የሚለው ገላጭ የአገልግሎቱን ዓላማና መሪ የሚያሳይ ነው፡፡ መንፈሳዊ አገልግሎት
ዓላማው የሰው ልጆች ድኅነት ነው፡፡ መሪውም መንፈስ ቅዱስ ነው፡፡ በአጠቃላይ የሰው ልጆች ለመንግስተ
ሰማያት እንዲበቁ የሚደረግ ማንኛውም እንቅስቃሴ ‹‹መንፈሳዊ አገልግሎት›› ሊባል ይችላል፡፡ ይህም
የሕይወትን ቃል ያላወቁ ወገኖች እንዲያውቁና እንዲያምኑ ማድረግ፣ ያመኑት ደግሞ እንዲጸኑና መንፈሳዊ
ትሩፋትን እንዲሠሩ ማድረግን ያካትታል፡፡
በመንፈሳዊ አገልግሎት ተልእኮ ላኪው እግዚአብሔር ነው፡፡ ተልዕኮውን ለመፈጸም ፍላጎት፣ እውቀትና
ክህሎት ቢያስፈልግም ሰው ለመንፈሳዊ አገልግሎት የሚላከው በእግዚአብሔር ፈቃድ እንጂ በእውቀቱ
ብዛት አይደለም፡፡ አገልጋይ በሰዎች ጋባዥነት ወደ አገልግሎት ቢቀርብም ሰዎች የተልዕኮው ምክንያት እንጂ
ላኪዎች አይደሉም፡፡ በመንፈሳዊ አገልግሎት ውስጥ የተልዕኮውን ባለቤት (ላኪውን) ማስተዋል እጅግ
መሰረታዊና የመጀመሪያው ነጥብ ነው፡፡ መልእክተኛ የላኪውን ፈቃድ እንደሚፈጽም ሁሉ መንፈሳዊ
አገልጋይም የጠራውንና የላከውን የእግዚአብሔርን ፈቃድ ሊፈጽም እንጂ የራሱን ፈቃድ ወይም የሌሎች
ሰዎችን ፈቃድ ሊፈጽም አይገባም፡፡
1|Page
ደንብ አንድ፤ ስያሜ
ይህ የውስጥ መተዳደሪያ ደንብ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን _________________
ሕብረት የውስጥ መተዳደሪያ ደንብ ተብሎ ይጠራል።
2.3 አባል ማለት በሕብረቱ የአባላት ግንኙነት ክፍል ተመዝግቦ አስፈላጊውን መሥፈርት በማሟላት
መደበኛ/ቋሚ/ የሆነ ነው፡፡
2.4 ጠቅላላ ጉባዔ ማለት የሕብረጡ መደበኛ አባላት በሙሉ የሚሳተፉበትና ስለሕብረቱ አጠቃላይ ሁኔታ
የሚወስን አካል ነው፡፡
2.5 የሥራ አመራር ጉባዔ ማለት በጠቅላላ ጉዔው የሚሰየምና የሕብረቱን ሥራ ከበላይ በመሆን የሚመራ
አካል ነው፡፡
2.6 ክፍል ማለት የሕብረቱን መንፈሳዊ አገልግሎት ለማከናወን ይረዳ ዘንድ በሥራ አመራር ጉባዔ
የሚሰየም ክፍል ነው፡፡
2.7 ምድብ ማለት መርሃ ግብር በአመቺ ሁኔታ ለማካሄድ ይቻል ዘንድ ቋሚ የሆኑ አባላት ለአገልግሎት
የሚመደቡበት የአባላት ስብሰብ ነው፡፡
3.1 የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሃይማኖትና ሥርዓት እንዳለ ጠብቆ እንግዳ በሆነ
ትምህርት ሳይለወጥ እና ሳይበረዝ በቀጥታ ለትውልድ ማስተላለፍ።
3.2 ወጥ የሆነ ሁሉን አቀፍ መንፈሳዊ አገልግሎት መስጠት (በዝማሬ፣ በኪነጥበብ፣በትምህርተ ወንጌል)
3.5 የሕብረቱ አባላት ባላቸው የሙያ ዕውቀት፣ ገንዘብ እና ጉልበት ለቤተክርስቲያኒቱ አገልግሎት
እንዲያበረክቱ ማድረግ እና ማበራታት።
5.3 ሕብረቱን ባላቸው ጊዜ፣ ጉልበት፣ ገንዘብና ዕውቀት ለማገልገል ፈቃደኛ የሆኑ።
6.1 መብት
6.1.1 ማንኛውም የሕብረቱ አባል ከሕብረቱ መንፈሳዊ አገልግሎቶችን ለማግኘት ሲጠይቅ ለምሳሌ
በቅድስት ቤተክርስቲያን በሥርዓተ ጋብቻውን ሲፈጽም በመንፈስዊ አገልግሎት እንዲታጅብለት ሲጠይቅ፣
አስቀድሞ በጽሑፍ ማመልከቻ ከጠየቀ ይፈቀድለታል፡፡
6.1.4 ማንኛውም የሕብረቱ አባል የሕብረቱን መደበኛ ጉባዔያት በማይጋጭ መልኩ ሌሎች
የቤተክርስቲያናችን የሆኑ መንፈሳዊ መርሃ ግብሮችን መካፈል ይችላል፡፡
6.1.5 ማንኛውም የሕብረቱ አባል ስለሕብረቱ የሚሰማውን ማለትም ሕብረቱየሚጠናከርበትንም ሆነ
ደካማ ጐን ለሚመለከተው ክፍል በግንባር ወይም በጽሑፍ በማንኛውም ጊዜ መግለጥ ይችላል፡፡
6.2 ግዴታ
6.2.1 ማንኛውም የሕብረቱ አባል የሕብረቱን የውስጥ መተዳደሪያ ደንብ የመፈጸም ግዴታ አለበት፡፡
6.2.2 አንድ የሕብረቱ አባል በመደበኛው መርሃ ግብር መቅረት አይፈቀድለትም፡፡ ነገር ግን መገኘት
የማይችልበት ሁኔታ ከአጋጠመው ለሚመለከተው ክፍል በማሳወቅ ይፈቀድለታል፡፡
6.2.3 ማንኛውም የሕብረቱ አባል ችግር ያለበት መሆኑን በማሳወቅ አስቀድሞ ካላስፈቀደ በስተቀር ጉባዔ
አቋርጦ መውጣት አይፈቀድለትም፡፡
6.2.4 አንድ የሕብረቱአባል በመደበኛ የጉባዔ ቀን ጉባዔውን የተካፈለ ለመሆኑ ማረጋገጫ በስም
መቆጣጠሪያው ላይ ምልክት ማስደረግ አለበት፡፡
6.2.5 ለረጅም ጊዜ በተለያየ ምክንያት ራቅ ብሎ የሚሄድ አባል ወይም የሕብረቱ አባል መደበኛ ጉባዔ
ወቅት በትምህርት፣ በሥራ ወይም በቤተሰብ ችግር ምክንያት ለረዥም ጊዜ መካፈል የማይችል ከሆነ
እስኪመጣ ድረስ ወይም ችግሩ እስኪቃለልለት ድረስ በአባልነት ለመቆየት እንዲፈቀድለት የሚመለከተውን
ክፍል መጠየቅና ፈቃድ ማግኘት አለበት፡፡
6.2.7 አንድ አባል ከሚመለከተው የሕብረቱክፍል ፈቃድ ከአላገኘ በስተቀር ሕብረቱን ወክሎ በማንኛውም
ቦታና ጊዜ ስብከት ማሰማት፣ መንፈሳዊ ዝግጅቶችን ማቅረብ፣ መዝሙር መዘመር አይችልም፡፡
6.2.9 ማንኛውም የሕብረቱ አባል በጠቅላላ ጉባዔ የሚወሰነውን ወርኃዊ መዋጮ ወቅቱን ጠብቆ መክፈል
አለበት፡፡
6.2.10 ማንኛውም የሕብረቱ አባል ንዑሳን ክፍሎችና ምድቦች በሚያቀርቡለት ጥሪ መሠረት መገኘትና
በሚሰጠው መንፈሳዊ አገልግሎት መሳተፍ አለበት፡፡
6.2.11 ማንኛውም የሕብረቱ አባል የሕብረቱን መርሃ ግብር ለማሰናከል ከውጭ መጥተው የማይገባ
ሥርዓት ከሚያሳዩ ግለሰቦች ጋር ምንም ዓይነት ጓደኝነት ወይም ዝምድና ቢኖር እንኳ በመጥፎ
ተግባራቸው መተባበር በሕብረቱ በኩል የተከለከለ ነው፡፡
6.2.12 የሕብረቱ የስራ አመራር አባላት በግልም ሆነ በጋራ በፖለቲካ መድረክ ላይ ሕብረቱን ወክለው
መሳተፍ አይችሉም።
6.2.14 የሕብረቱ አባላት ለደብሩ ሰንበት ት/ቤትየአገልግሎት ጥያቄ የመተባበር ግዴታ አለባቸው፡፡
6.2.15 እያንዳንዱ የ ሕብረቱ ዓባል በአባላት መካከል የመግባባት እና የመተባበር ስሜት እንዲዳብር
ማድረግ።
7.1 ቢያንስ በዓመት አንድ ጊዜ ወይም እንደአስፈላጊነቱ በየ6 ወሩ የደብሩ ሰንበት ት/ቤትተወካይ
በተገኙበት አጠቃላይ ስብሰባ ያደርጋል፡፡
7.2 የሕብረቱን የሥራ ሂደት ከሥራ አመራር በሚቀርበው ሪፖርት መሠረት ይገመግማል፡፡
7.5 የሥራ አመራር ጉባዔ አባላትን በሕብረቱ የምርጫ ሥነ ሥርዓት ደንብ መሠረት ይመርጣል፡፡
7.6 በደብሩ ሰንበት ት/ቤትበኩል ሲጠየቅ የሕብረቱ ተወካይ የሥራ አመራር ጉባዔ በሚያቀርብለት ዕጩ
መሠረት ይመርጣል፡፡ አሳማኝ ሆኖ ሲያገኝ ሥራ አመራሩ ለጠቅላላ ጉባኤው አቅርቦ እንዲሻሻል ያደርጋል።
7.7 ሕብረቱ የውስጥ መተዳደሪያ ደንብ አስፈላጊ ሆኖ ሲያገኘው እንዲሻሻል ጥያቄ ያቀርባል።
7.8 ከጠቅላላው ጉባኤ 2/3 አባላት የተገኙበት ጠቅላላ ስብሰባ ምልዓተ ጉባኤ ይሆናል ውሳኔዎችንም
ማሳለፍ ይችላል።
8.3 በሥሩ ያሉትን ክፍሎችና ምድቦች ተግባራቸውን በበቂ ሁኔታ ማከናወናቸውን ይገመግማል፣ አስፈላጊ
ሆኖ ሲገኝ ከሚመለከታቸው ክፍሎች ጋር በመተባበር የክፍል የምድብ አባላትን ይመርጣል፣ ይመድባል፡፡
8.4 በሥራ ወይም በአገልግሎት ሂደት ለሚከሰቱ ችግሮች እንደአስፈላጊነቱ ሰንበት ት/ቤትና ከሚመለከትው
ክፍል ጋር በመነጋገር መፍትሔ ይፈልጋል፡፡
8.5 አስፈላጊ ሆኖ ባገኘው ጊዜ የጠቅላላ ጉባዔውን ስብስባ ይጠራል፣ የመወያያ አጀንዳ ያዘጋጃል፡፡
8.7 ስለ ሕብረቱ አጠቃላይ የሥራ እንቅስቃሴ በዓመት ውስጥ ሁለት ጊዜ በስብሰባ ለጠቅላላ ጉባዔው ገለጻ
ያደርጋል፡፡
9.1.1 ሰብሳቢ
9.1.3 ጸሐፊ
እነዚህን አባላት የሚመርጠው ጠቅላላ ጉባዔው ሲሆን ከላይ የተዘረዘረውን የሥራ ክፍፍል የሚያደርጉት
ውስጥ እርስ በእርሳቸው ናቸው፡፡
9.2 የሥራ አመራር ጉባዔ ምርጫ የሚከናወነው በሕብረቱ የውስጥ መተዳደሪያ ደንብ መሠረት ነው።
9.4 የሥራ አመራር ጉባዔ የአገልግሎት ዘመን ሁለት /2/ ዓመት ብቻ ነወ፡፡ አንድ አባል በጠቅላላ ጉባዔው
ከታመነበት ሌላ የምርጫ ዘመን በድጋሚ ሊመረጥ ይችላል፡፡
9.5 ሁለት የምርጫ ዘመን በተከታታይ ያገለገለ የሕብረቱ አባል አንድ የምርጫ ዘመን አርፎ እንደገና
መመረጥ ይችላል።
9.6 በልዩ ልዩ ምክንያት ማገልገለ ባልቻሉ የሥራ አመራር ጉባዔ አባላት ከተጠባባቂዎች ይተካል፡፡
የአገልግሎት ዘመኑ ሳያልቅ ተጠባባቂዎች በሙሉ ከገቡ የጐደሉትን የሥራ አመራር አባላት ጠቅላላ ጉባዔው
ያስመርጣል።
10.3 አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ በአስቸኳይ ጉዳዮች ላይ ለመነጋገር ከመደበኛ ስብሰባ ውጭ የሥራ አመራር ጉባዔ
አባላትን በመጥራት ስብሰባ እንዲካሄድ ያደርጋል፡፡
10.4 የሥራ አመራር ጉባዔው አባላት የተሰጣቸውን የሥራ ድርሻና ኃላፊነት በአግባቡ መወጣት
አለመወጣታቸውንና ጠቅላላ የሕብረቱን አስተዳደራዊ ሥራ ይቆጣጠራል፡፡
10.7 በማንኛውም ስብሰባ ወቅት በውሳኔ አሰጣጥ በኩል እኩል ድምጽ በሚሆንበት ጊዜ ሊቀመንበሩ
የደገፈው ሐሳብ ይወስናል፡፡
ደንብ አሥራ አንድ ፤ በሥራ አመራር ጉባዔ የምክትል ሰብሳቢ የሥራ
ድርሻ
11.1 ተጠሪነቱ ለሰብሳቢው ነው።
12.3 በጠቅላላ ጉባዔውም በሆነ በሥራ አመራር ጉባዔ ላይ ቃለ ጉባዔ ይይዛል፣ በውሳኔውም ላይ
የጉባዔውን አባላት ያስፈርማል፡፡
12.4 ከሥራ አመራር ጉባዔና ከጠቅላላ ጉባዔ አባላት የሚቀርቡ ጠቃሚ ሐሳቦችን በአጀንዳዎች ያዘጋጃል፡፡
12.5 የሥራ አመራር ጉባዔውን ውሳኔ ለሚመለከተው ክፍል በሰብሳቢው ፊርማ በጽሑፍም ሆነ በቃል
ያሳውቃል።
12.7 ለሕብረቱ የሚመጡትን ደብዳቤዎች ተቀብሎ እንደ አስፈላጊነቱ በሥራ አመራር ጉባዔ ላይ ያቀርባል፡፡
12.8 በመደበኛ የጠቅላላ ጉባዔ ስብሰባ ወቅትና በሕብረቱ ዓመታዊ በዓል እንዲሁም አስፈላጊ በሆነ ልዩ ልዩ
በዓላት ሁሉ የሕብረቱን የሥራ ሂደት በሪፖርት መልክ አርቅቆ በሥራ አመራር አጽድቆ ያቀርባል፡፡
12.9 የሥራ አመራር ጉባዔውን የስብሰባ ወቅት ላለመሻማት ሲባል ቀላል በሆኑ የተለመዶ ሥራዎች ላይ
ውሳኔ ይሰጣል፡፡
12.10 የሥራ አመራር ጉባዔውን የረጅምና የአጭር ጊዜ ዕቅድ በየወቅቱ በማስታወስ ተፈጻሚ እንዲሆን
ያደርጋል።
ደንብ አሥራ ሦስት ፤ በሥራ አመራር ጉባዔው የሒሳብ ክፍል እና ንብረት
ተቆጣጣሪ ድርሻ
13.1 ተጠሪነቱ ለጽ/ቤት ነው።
13.3.2 የሕብረቱ ሒሳብ ነክ እንቅስቃሴ /ገቢና ወጪ/ ይቆጣጠራል፣ የሕብረቱቤቱን ተንቀሳቃሽ፣ ቋሚና
አላቂ ንብረት በንብረት መዝገብ መዝግቦ በኃላፊነት ይቆጣጣራል ፡፡ ይህ ክፍል በሥሩ ሁለት ንዑሳን
ክፍሎች በሥራ አመራሩ በኩል ይመደብለታል።
13.3.4 ከልዩ ልዩ ዝግጅቶችና ከተለያዩ ንዑሳን ክፍል የሚገኘውን ለሕብረቱ ሒሳብ ክፍል በወቅቱ በደረሰኝ
ገቢ መሆናቸውን ይቆጣጠራል።
13.3.5 የሥራ አመራር ጉባዔው የፈቀደውን ወጪ በወጪ ማዘዣ ላይ ይሞላል። በገንዘብ ያዥ በኩል
እንዲከፍል ያዛል፡፡
13.3.6 ሕብረቱ በግዥም ሆነ በእርዳታ በሚያገኛቸው ንብረቶች በንዑሳን ክፍሎችና በኩል በአግባቡ
መቀመጣቸውን ይቆጣጠራል፡፡
13.3.9 የሕብረቱን ሒሳብ አያያዝና የገንዘብ መጠን የሚገልጽ ሪፖርት በማዘጋጀት በየሦስት ወሩ ለሥራ
አመራር ጉባዔው ያሳውቃል፡፡
13.4.1 በዓመት አንድ ጊዜ የንብረት ቆጠራ አድርጐ የሕብረቱን ንብረት ዓይነት ብዛት የሚገልጽ ሪፖርት
በማዘጋጀት ለሥራ አመራር ጉባዔው ሪፖርት ያደርጋል፡፡
13.4.2 እንደአስፈላጊነቱ በሕብረቱ የሥራ አመራር ጉባዔ ለሚወክል ኦዲተር /መርማሪ/ ስለሂሳብ አሠራሩ
ገለጻ ያደርጋል፣ ሒሳቡን ያስመረምራል፡፡
13.4.3 በሥራ አመራር ጉባዔው ሲታዘዝ ከተለያዩ የሕብረቱቤቶችና ሌሎች አካላት ለሚቀርቡ ሒሳቡ ነክ
ጥያቄዎች አስፈላጊውን መልስና ሙያዊ መብራሪያ ይሰጣል፡፡
13.4.4 ንዑሳን ክፍሎችም በእጃቸው ካለው ገንዘብ ምንም ዓይነት ወጪ እንዳያደርጉ ይቆጣጠራል፡
13.4.5 አገልግሎት በመስጠት የተበላሹ ከጥቅም ውጭ የሆኑ ንብረቶች ሲኖሩ ለሥራ አመራር ጉባዔው በቂ
መረጃ በመስጠት እንዲጠገኑ ወይም በምትካቸው ሌላ እንዲገዛ ያደርጋል፡፡ ያለአግባብ የባከኑ፣ የጠፉ
ወይም የተሰበሩ ንብረቶች ካሉም ለሥራ አመራር ጉባዔው ሪፖርት በማድረግ ውሳኔ እንዲሰጣቸው
ያደርጋል፡፡
14.4 በሕብረቱ ወይም በሕብረቱአማካይነት በሚደረጉ የበጎ አድራጎት ሥራዎች ላይ ይሳተፋል፡፡ ከዚህም
ጋር በማያያዝ በሕብረቱ ኃላፊነት መንፈሳዊ ጉዞ መርሃ ግብሮችን ይነድፋል፣ያስተባብራል፣ ይቆጣጠራል
ያስፈጽማል፡፡
14.7 ሕብረቱ ለሽያጭ የሚያዘጋጀውን ንዋያተ ቅዱሳትም ሆነ ሌሎች መንፈሳዊ ቁሳቁሶች ተረክቦ ይሸጣል።
ደንብ አሥራ አምስት ፤ በሥራ አመራር ጉባዔ የስልጠና ክፍል የሥራ ድርሻ
15.1 ተጠሪነቱ ለጽ/ቤት ነው።
15.8 የአባላቱ የመጽሐፍ ቅዱስ ዕውቀትና የቤተ ክርስቲያን ሥርዓተ ትምህርት ይበልጥ ለማጠናከር
መንፈሳዊ ስልጥናዎችን እንዲሰጡ ያደርጋል።
16.3.2 ከስልጠና ክፍል ጋር በመተባበር መዝሙር እና ምሥጢራዊ ሥርዓቱን ለአባላቱ እንዲሰጥ ማድረግ።
16.3.4 በሕብረቱ ልዩ መርሀ ግብር፣ በአዳራሽ ወይም በቤተክርስቲያኑ ዓውደ ምህረት ላይ የሚቀርቡ
መዝሙራት ከመቅረባቸው በፊት በሙያው በቂ እውቀት ያላቸውን ሊቃውንት በማሳየት እንዲቀርቡ
ማድረግ።
18.4 ከአባላት ጋር የቅርብ ግንኙነት እያደረገ ችግራቸውን ለመፍታት ጥረት ያደርጋል፣የመፍትሄ ሀሳብም
ይሰበስባል።
18.7 ሕብረቱ ከተለያዩ ሰ/ት/ቤቶችና ማኅበራት ጋር የጠበቀ ግንኙነት እንዲኖረው ሁነታዎችን ያመቻቻል።
18.9 የሕብረቱ አባል አደጋ ወይም ኃዘን ቢደርስበት አባላቱን በማስተባበር እንዲገኙ ያደርጋል።
18.10 በበዓላት እና ሕብረቱ ጋብዟቸው ከሌላ ቦታ የሚመጡትን እንግዶች ይቀበላል፣ የምግብ መስተንግዶ
ያደርጋል።
18.11 በሕብረቱ ለሚዘጋጅ ልዩ ዝግጅት ከጽ/ቤት ሲታዘዝ የጸበል ጸዲቅ ዝግጅት ያደርጋል።
19.3.5 አዲስ አማኝ ከሆነ/ች/ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሐይማኖትን ከተቀበለ/ች/ አምስት ዓመትና
ከዚያም በላይ የሆነው /የሆናት/ ፤
19.5.5 ከዚህ ቀደም በአስመራጭ ኮሚቴ ወይም በሌላ ተመሳሳይ የኮሚቴ አገልግሎት ላይ ተሳትፎ/ተሳትፋ
የነበረ ፤
20.2 ለሁለተኛ ጊዜ ጥፋት ከፈጸመ በሥራ አመራር ጉባዔው በኩል ምክርና ግሳጻ ይሰጠዋል፡፡
20.3 አሁንም በተሰጠው ምክርና ተግሳጽ የማይታረም ሆኖ ከተገኘና ለሦስተኛ ጊዜ ጥፋት ከፈጸመ በምክረ
አበው ክፈል የመጨረሻ ምክርና ተግሳጽ እንዲሁም ማስጠንቀቂያ ይሰጠዋል፡፡
20.4 ከላይ ደረጃ በደረጃ የተሰጡት ምክርና ማስጠንቀቂያዎች በጽሑፍ በዝርዝር ተይዘው በአባሉ የግል
ማኅደር እንዲቀመጡ ይደረጋል፡፡
20.5 በእነኝህ የቅጣት ደረጃዎች በጥፋቱ የማይመለስ ከሆነ እና አራተኛ ጊዜ ሲያጠፋ ከተገኘ ከሕብረቱ
ይሰናበታል፡፡ ውሳኔውንም የሕብረቱ አጠቃላይ ጉባዔ፣ የደብሩ ሰንበት ት/ቤት ጽ/ቤት እንዲያውቁት
ይደረጋል፡፡
21.1 ሥርዓተ-ትምህርት
ሕብረቱ አባላቱን በዕድሜና በዕውቀታቸው መጠን ከፋፍሎ በልዩ ልዩ መርሃ ግብሮች የሚያስተምር ሲሆን
ለሕፃናት ፣ ለእንግዶችና ለወጣቶች የሚመጥን ሥልጠና በሕብረቱ ትምህርት ክፍል ይቀረጻል፡፡ ከዚህ
በተጨማሪ እንደአስፈላጊነቱ ልዩ ልዩ ወቅታዊ ሴሚኖሮች በስልጠና ክፍሉ ተዘጋጀተው በሥራ መራር
ጉባዔው ተግባራዊ ይሆናሉ፡፡
21.2 መምህራን
በሕብረቱ የሚያስተምሩ መምህራን ፤
21.2.1 በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዋ ተልዕኮ መምሪያ
ወይም በሀገረ ስብከቱ የስብከተ ወንጌል መምሪያ በኩል እንዲያስተምሩ የተፈቀደላቸውን ሰባኪያን ፤
21.2.3 በሀገረ ስብከቱ የሰንበት ት/ቤት ማደረጃ መምሪያ ለሕብረቱ የተመደበው መምህር ፤
21.2.6 ከቤተክርስቲያኒቱ ኮሌጆችና ከፍተኛ ትምህርት ቤቶች የተመረቁና በትምህርት ክፍሉ የታመነባቸው
ናቸው፡፡
21.6 የስብሰባ ጊዜ
የሕብረቱን የዕለት ተዕለት ሥራ ለማከናወን በኃላፊነት የሚያገለግሉት አባላት ስብሰባ ማድረግ አስፈላጊ
በመሆኑ የሥራ አመራር ጉባዔው በ 2 ሳምንት አንድ ጊዜ ስብሰባ ሲያደርግ እያንዳንዱ ንዑስ ክፍል
በሳምንት ቢያንስ አንድ ጊዜ መሰብሰብ ይኖርበታል፡፡