Professional Documents
Culture Documents
63693834
63693834
1
Contents
1.መግቢያ ......................................................................................................................................................... 2
2. የልምድ ቅመራው ዓላማ .................................................................................................................................... 3
3. የልምድ ቅመራው አሠራር ስልት .......................................................................................................................... 3
4. የልምድ ቅመራው የተካሄደባቸው ርዕሶችና ቅመራው የተካሄደበት ወረዳ ዝርዝር ................................................................ 4
5. የተሻለ ውጤት ያስመዘገቡ አርሶአደሮች ቴክኖሎጅዎችን የፈጸሙበት ዝርዝር አሰራር ........................................................... 4
5.1. የኮትቻ አፈርን በዝቆሽ ዘዴ አጠንፍፎ ስንዴ ማልማት.......................................................................................... 4
5.1.1 የወረዳውና የቀበሌው አጠቃላይ ገፅታ........................................................................................................... 4
5.1.2.አሰራሩ ተግባራዊ ከመሆኑ በፊት የነበሩ ሁኔታዎች ............................................................................................ 6
5.1.3.አሰራሩን ተግባራዊ በማድረግ የተገኘ ውጤት .................................................................................................. 6
5.1.4. ውጤቱ የተገኘበት ዝርዝር ሂደት ................................................................................................................ 7
5.1.5. ተግባሩን በመፈጸም ሂደት ያጋጠሙ ችግሮች እና የተፈቱበት አግባብ ..................................................................... 9
5.1.6. ለውጡን ተግባራዊ በማድረግ ሂደት የእያንዳንዱ ባለድርሻ የነበረው .................................................................... 10
5.1.7. ከዚህ ምርጥ ልምድ የተገኘ ተሞክሮ........................................................................................................... 10
5.1.8. የአ/አደሮቹ ወጭ እና ገቢ ....................................................................................................................... 11
5.1.9. የወጭ ዝርዝር ..................................................................................................................................... 11
5.1.20 የገቢ ስሌት........................................................................................................................................ 12
5.1.21.የኮትቻ አፈርን በቢቢኤም በማጠንፈፍ ስንዴን የማምረት ዘዴ ............................................................................. 13
5.12.1.የወረዳውና የቀበሌው አጠቃላይ ገጽታ ...................................................................................................... 13
5.12.2.ቀደም ሲል ቴክኖሎጅውን በመተግበር ረገድ የነበሩ ሁኔታዎች.......................................................................... 14
5.12.3.አሰራሩን ተግባራዊ በማድረግ የተገኘ ውጤት .............................................................................................. 15
5.12.5.ተግባሩን በመፈጸም ሂደት የነበሩ አደናቃፊ አመለካከቶችና የተፈቱበት አግባብ ...................................................... 17
5.12.6.ተግባሩ ተከናውኖ ውጤት ከተገኘ በኋላ የመጣ የአመለካከት ለውጥ .................................................................. 18
5.12.7.ተግባሩ በሚከናወንበት ወቅት እያጋጠሙ ያሉ ችግሮች .................................................................................. 18
5.12.8.ችግሮችን ለመፍታት የተወሰዱ ዕርምጃዎች ................................................................................................. 19
5.12.9.የተገኘውን ውጤት ለማምጣት የባለድርሻ አካላት ሚና .................................................................................. 19
5.13.7.ከዚህ ምርጥ ልምድ የተገኘ ተሞክሮ ......................................................................................................... 20
6. የወጭ ዝርዝር ............................................................................................................................................... 21
6.1. የአ/አደሮቹ የገቢ ስሌት............................................................................................................................. 21
6.1.2.ማጠቃለያ........................................................................................................................................... 22
1
1.መግቢያ
ዞናችን በክልላችን በሠብል አምራችነታቸው ከሚታወቁ ዞኖች ውስጥ አንዱ
ነዉ ። በ 2011/2012 ምርት ዘመን በሀገሪቱ ከተመረተው አጠቃላይ ምርት
ውስጥ 10 % የሚሆነው በዚህ ዞን ዉስጥ የተመረተ ነው። በዞኑ የዕድገትና
ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ላይ እንደተመለከተው በ 2011/2012 ምርት ዘመን 12.2
ሚሊዮን ኩ/ል ምርት ለማምረት የታቀደ ሲሆን ይህም በ 2011/2012 ምርት
ዘመን 10.7 ሚሊየን ኩ/ል ምርት ተገኝቷል ። የዋናዋና ሠብሎች ምርታማነት
በ2011/2012 ምርት ዘመን ከተገኘው 24 ኩ/ል በሄ/ር ወደ 28 ኩ/ል ማደግ
ይኖርበታል። ይህንን ውጤት ለማምጣት ደግሞ በተለያዩ አካባቢዎች ለእያንዳንዱ
ሠብል በፓኬጅ አጠቃቀም መመሪያ ላይ የተቀመጠውን ምክረ-ሃሳብና
የራሣቸውን ዕውቀት በመጨመር ተግባራዊ አድርገው የተሻለ ምርታማነት
ያስመዘገቡ አርሶአደሮችን ተሞክሮ በመቀመር ወደ ሌሎች አካባቢዎች የማስፋት
ስራ (Scalling up) መስራቱ ወሳኝ ተግባር ነው።
በዚህም መሠረት የማስፋት ስትራቴጂውን ተግባራዊ ለማድረግ እንዲቻል
በተወሰኑ አርሶ አደሮች ተተግብረዉ ዉጤት ያስገኙ አሰራሮች ወደ ሌሎች አርሶ
አደሮች በአጭር ጊዜ ውስጥ በስፋት እንዲደርሱ ለማድረግ እንዲቻል ምርጥ
ልምዶቹ ከመገኘታቸው አስቀድሞ የነበረውን ነባራዊ ሁኔታ፣ አሁን የተገኘውን
ውጤት፣ ውጤቱ የተገኘበትን ዝርዝር ሂደት፣ ውጤቱን በማስገኘት ሂደት
ያጋጠሙ ችግሮችና የተፈቱበት አግባብ እና ከዚህ ምርጥ ልምድ የተገኙት
ተሞክሮዎች ተዘርዝረው ተቀምረዉ ለሚመለከተዉ ደርሰዋል ፡፡
2
2. የልምድ ቅመራው ዓላማ
በክልሉ የሠብል ል/ጥበቃና የአፈር ለምነት ቴክኖሎጅ አጠቃቀምን
በተዘጋጀው የፓኬጅ ምክረ-ሃሳብና የራሳቸውንም ዕውቀት በመጨመር
ተግባራዊ አድርገው ውጤት ያስመዘገቡ አርሶአደሮችን መልካም ተሞክሮ
በጽሁፍና በፎቶግራፍ ዶክመንት በማድረግና ወደሌሎች አካባቢዎች
በማስተላለፍ የ5 ዓመቱን የሰብል ምርት ዕቅድ ማሣካት ነው።
3
በተዘጋጀው መጠይቅ መሠረት የተሰበሰበውን መረጃ ልምዱን
ለመቅሰም በሚያስችል መልኩ መጻፍ ዋናዋናዎቹ ነበሩ።
4
ወረዳው በሰሜን ለገሂዳ ወረዳ፣ በደቡብ የሰሜንሸዋ ወረዳ፣ በምዕራብ ከለላ
ወረዳዎች እንዲሁም በምስራቅ ወረኢሉ ወረዳዎች ያዋስኑታል።
ወረዳው 21 የገጠር ቀበሌዎች 1 የንዑስ ከተማ ቀበሌዎች በድምሩ 22 ቀበሌዎች
ያሉት ሲሆን የአ/አደር ብዛቱም ወንድ 17763 ሴት 2582 በድምሩ 20345
ይደርሳል። የወረዳው ዋና ዋና የግብርና ምርቶ
ጤፍ፣ስንዴ፣በቆሎ፣ማሽላ፣አተር፣ባቄላናቸው። እነዚህ ሰብሎች የሚመረቱት
በመኸር ነዉ ።
5
በመኸር ወቅት ስንዴ 1096 ሄክታር የተዘራ ሲሆን 65 ኩንታል ምርጥ ዘር
ጥቅም ላይ ውሏል።
8
5.1.5. ተግባሩን በመፈጸም ሂደት ያጋጠሙ ችግሮች እና የተፈቱበት አግባብ
ስንዴን በጥቁር አፈር በዝቆሽ ከመዝራት አንፃር በአካባቢው የሚታዩ ብዙ
ጎታች የአመለካከት ችግሮች ነበሩ። በበጋ ደጋግሞ አለማረስ፣ ስንዴ ሞላ ብሎ
ካልተዘራ ምርት አይሰጥም፣ የተሻሻሉ ዝርያዎችን በስፋት አለመጠቀምና
ዋጋውን አጋኖ ማየት፣ማሳው ሰፊ ስለሆነ ሁሉንም በዝቆሽ ለመሸፈን ጉልበት
ያንሳል ብሎ ማሳብ፣ አምና የተከሰተውን ቢጫ ዋግ ዘንድሮም ይከሰታል ብሎ
በመፍራት ስንዴ ለመዝራት አለመፈለግ ጎልተው የሚታዩ ችግሮች ነበሩ።
ከዚህ በተጨማሪ በክልል፣ በዞንና በወረዳ ደረጃ በሚሰጡ ስልጠናዎችም
የተሻሻለ የስንዴ ዝርያና የማዳበሪያን አጠቃቀምን ከማሳደግ አንፃር ብቻ
የተቃኙ ነበሩ።
ይህንን የአመለካከትና የክህሎት ችግር ለመፍታት በዞን እና በወረዳ ደረጃ
የሰብል ልማት ፓኬጅ ስልጠና በየደረጃው ላሉ ሙያተኞች፣ አመራር አካላት
እና አ/አደሮች ስልጠና በየደረጃው የወረዳና የቀበሌ ሙያተኞች በዘር ስራው
እገዛ አድርገውላቸዋል።የእነዚህ የአርሶአደሮች ስንዴን በጥቁር አፈር ላይ
በዝቆሽ መዝራት በብተና ከተዘራው የበለጠ የሰብል አቋም ያለው በመሆኑ
በቀበሌ ደረጃ ሶስት ዙር የአርሶአደር ባዕል በማዘጋጀት አርሶአደሮችን
ተሞክሮ እንዲወስዱና በቀጣይ ጊዚያት በተመሳሳይ መልኩ እንዲሰሩ
ለመቀስቀስ ተችሏል።
9
ስዕል 3. የአ/አደር ባዕል ሲካሄድ ጀማ ወረዳ በተሰራዉ ስራ
5.1.6. ለውጡን ተግባራዊ በማድረግ ሂደት የእያንዳንዱ ባለድርሻ የነበረው ሚና
የእነዚህ አ/አደሮች ስንዴን በዝቄሽ በመዝራት ውጤት ሊያመጡ የቻሉት
የተለያዩ የአመራርና ባለሙያዎች ድጋፍ ከፍተኛ ስለነበረ ነው። የቀበሌ
ሙያተኞች በአርሶአደር መረጣ በዘር ወቅት በሙያና በጉልበት በማገዝና
በየጊዜው የመስክ ድጋፍና ክትትል በማድረግ ተሳትፈዋል። የወረዳ
ሙያተኞች ስልጠና በመስጠት በዘር ወቅት የሙያና የጉልበት ድጋፍ
በማድረግና ከተዘራም በኃላ የመስክ ድጋፍ በማድረግ አስታዋፅኦ ነበራቸው።
የቀበሌ አስተዳደር አካላት በዘር ወቅት የጉልበት እገዛ አድርገዋል ።
የአገልግሎት የህብረት ስራ ማህበራትም በወቅቱ የስንዴ ምርጥ ዘርና
ማዳበሪያ በማቅረብ እገዛ አድርገዋል።
10
ለመስራት ምቹ እንደሆነም አሳይተዋል። በዝቆሽ የተዘራው ስንዴ በአካባቢው
በብተና እና ያለዝቆሽ ከተዘራው ይልቅ በፍሬ አያያዙ የግንዱ ውፍረትና
ዝናብ በተከሰተበት ወቅትም መሬቱ ዉሃ ያላዘለ መሆኑን ከዚህ ተሞክሮ
ለማወቅ ተችሏል። በአዲሱ አሰራር (ስንዴን በዝቆሽ) በመዝራታቸው 39
ኩንታል/ሄክታር ያገኙ ሲሆን በነባሩ አሰራር (በብተና) ግን ከ 20 ኩንታል
በላይ አግኝተው እንደማያውቁ ገልፀዋል ።
5.1.8. የአ/አደሮቹ ወጭ እና ገቢ
ወጭ ገ ወጭ ገቢ ወጭ ገ ወጭ ገቢ ወጭ ገ ወጭ ገቢ
ቢ ቢ ቢ
1 ማዳበሪያ 1245 1460 1420 1556 1556 1420
1.1 ም/ዘር 780 500 450 1400 750 450
1.2 አረም 300 500 450 650 550
1.4 አጨዳ 400 250 800 1000 1000 700
1.5 ለግዞሽ 160 100 100 200 100
1.6 ለዉቂያ 200 150 120 150 1000 100
1.7 መሬት
ኮንትራት
1.8 ለቀን ሰራተኛ
11
5.1.20 የገቢ ስሌት
ተ. ተግባራት በላይ ገዙ ዱባለ አየለ ሀሚድ አህመድ ካሳዉ አሰፋ ዳምጠዉ
የሱፍ መሃመድ ለገሰ
ቁ
ወ ገቢ ወጭ ገቢ ወ ገቢ ወ ገቢ ወ ገቢ ወ ገቢ
ጭ ጭ ጭ ጭ ጭ
2 የገቢ ዝርዝር
12
5.1.21.የኮትቻ አፈርን በቢቢኤም በማጠንፈፍ ስንዴን የማምረት ዘዴ
የወረዳው ስም- ለገሂዳ የቀበሌው ስም- ሴደሬ (09 ቀበሌ)
5.12.1.የወረዳውና የቀበሌው አጠቃላይ ገጽታ
13
ወርጭ 5.16 ወይናደጋና 70.44% ደጋ ሲሆን ከባህር ወለል በላይ ከፍታው
ከ1644_3409 ሜ ይደርሳል።ዓመታዊ የዝናብ መጠኑ ከ 900-1200 ሚ.ሜ
ሲሆን አመታዊ የሙቀት መጠኑ ደግሞ ከ10-22.5 ዲ.ሴ ነው። በወረዳው ውስጥ
ከአለው አፈር 24.3 % ኮትቻ ፣44.8 % ቡናማና 10.8 % ቀይ እንደሆነ ነጭ
አሸዋማ 6.9% ይገመታል አለታማ 10.31% ።
በወረዳው ከሚመረቱ ሰብሎች ውስጥ ስንዴ፣ ጤፍ፣ ምስርና ባቄላ የሚጠቀሱ
ናቸው። በ 2010/2011 ምርት ዘመን በወረዳው 22169 ሄ/ር መሬት ታርሶ
በተለያዩ ሠብሎች ተሸፍኗል።
የኮትቻ አፈርን በማጠንፈፍ ስንዴን በመጀመሪያው ዙር በማልማት ልምድ
የተቀመረበት የሰደሬ ቀበሌ ከወረዳዉ ከተማ ያለው ርቀት 17 ኪ. ሜ ነው። የቆዳ
ስፋቱም 3,402 ሄ/ር ሲሆን ከዚህ ውስጥ 2,224 ሄ/ር መሬት ለእርሻ አገልግሎት
፣370 ሄ/ር ለግጦሽ፣307 ሄ/ር በደንና ቁጥቋጦ ፣ 35 ሄ.ር በውሃ የተሸፈነና 397
ሄ/ር ለመንደር ግንባታ ስራ የዋለ ነው። ቀበሌው በሰሜን ከደንቀዝ፣በደቡብ
ከይማዳ፣ በምዕራብ ከጀይራና ደጎላ ቀበሌና በምስራቅ ከአምባጨራ ቀበሌ ጋር
ይዋሰናል። የአየር ንብረቱ 100% ወይና ደጋ ሲሆን ዓመታዊ የዝናብ መጠኑ
ሰብልን ለማምረት በቂ ነው። ከባህር ወለል በላይ ከፍታው ደግሞ ከ1800-2000
ሜ ነው። አፈሩም 71% ቡናማ፣26% ቀይ እና 4% ኮትቻ አፈር ነው።
በቀበሌው 1026 ወንድና 571 ሴት በድምሩ 1597 አባወራና እማወራዎች
የሚኖሩ ሲሆን አጠቃላይ የህዝብ ብዛቱ 3,183 ወንድና 3,257 ሴት በድምሩ
6440 ነው። ጤፍ፣ ስንዴ፣ ባቄላና ምስር በቀበሌው የሚበቅሉ ዋናዋና ሰብሎች
ናቸው ።
5.12.2.ቀደም ሲል ቴክኖሎጅውን በመተግበር ረገድ የነበሩ ሁኔታዎች
ወረዳው ሠፊ የኮትቻ አፈር ሽፋን ያለው ቢሆንም በክላስትር የማምረት ተግባር
14
ለማምረት የሚያስችል ሁኔታ ቢኖርም በአካባቢው በኮትቻ አፈር ላይ ስንዴ
አይመረትም፣ውሃውን ማጠንፈፍ አይቻልም፣ቢቢኤምን በሬው መጎተት
አይችልም በሚል ጎታች አስተሳሰብ ምክንያት በኮትቻ አፈር ላይ ሰብልን ሁለት
ጊዜ በማምረት መገኘት የሚገባውን ያህል ምርት ሳይገኝ ቆይቶ ከ2002 ምርት
ዘመን ጀምሮ በ 145 ሄ/ር መሬት ላይ በ 420 አርሶአደሮች ተሳትፎ የአፈሩን
ትርፍ ውሃ በቢቢኤም በማጠንፈፍ የመጀመሪያውን ዙር ሰብል ምርታማነት
ከማሣደግ በተጨማሪ የመጀመሪያው ሰብል እንደተሰበሰበ በሚኖረው ዕርጥበት
ሁለተኛ ሰብልም ለማምረት ተችሏል።
15
ስዕል 5 . በቀበሌው ኮትቻ አፈርን በክላስተር በማጠንፈፍ የተዘራ የስንዴ ሰብል
የኮትቻ አፈርን ትርፍ ውሃ አጠንፍፈው ከዘሩ አርሶአደሮች ውስጥ አንዳንድ
አርሶአደሮች በመጀመሪያው ዙር ልማት ብቻ በሄ/ር ስሌት እስከ 70 ኩ/ል የስንዴ
ምርት አምርተዋል።በዚህ ምርት ዘመን በ 09 ቀበሌ አቶ አራጋዉ ዘይኑ ከ
0.25 ሄ/ር መሬት ላይ 17.5 ኩ/ል ወይም በሄ.ር ስሌት 70 ኩ/ል፣ አቶ ይመር
ከበዴ ከ 0.25 መሬት ላይ 14.5 ኩ/ል በሄ/ር 58ኩ/ል ፣አቶ አረብ መሃመድ ከ
0.75 ሄ.ር መሬት ላይ 16 ኩ/ል በሄ/ር 21 ኩ/ል እና አቶ ሁሴን መሃመድ ከ
0.25 ሄ/ር መሬታቸዉ ላይ 12-ኩ/ል በሄ/ር 48 የስንዴ ምርት አግኝተዋል።
5.12.4.ውጤቱ የተገኘበት ዝርዝር ሂደትና አሠራር
በወረዳው በምርት ዘመኑ የኮትቻ አፈርን በማጠንፈፍ በክላስተር የስንዴ ሰብል
የዘሩ 10603 አርሶአደሮች የነበሩ ቢሆንም ከወረዳው ውስጥ በ09ቀበሌ ነዋሪ
የሆኑት የአቶ አራጋዉ ዘይኑ፣አቶ ሁሴን መሃመድ ፣ አቶ አረብ መሃመድ ና
አቶ ይመር ከበዴ አሰራር እንደሚከተለው ቀርቧል።
እነ አቶ አራጋዉ ዘይኑ ከተወሰኑ ዓመታት በፊት ማሣቸውን ጤፍ፣ሽብራ ፣
ምሰር እና ጓያ ወይንም መሬቱን ጦም በማክረም የክረምቱ ዝናብ ከወጣ በኋላ
ሽምብራ ብቻ ያመርቱበት የነበረ ሲሆን ከተወሰኑ ዓመታት ወዲህ ግን ማሣውን
በዓመት ሁለት ጊዜ በማልማት ተጠቃሚ ለመሆን ችለዋል። አርሶአደሮቹ
16
በአለፈው ዓመት ሽብራ ዘርተውት የነበረውን 0.25 ሄ/ር መሬት የመጀመሪያውን
እርሻ መጋቢት መጀመሪያ፣ ሁለተኛውን እርሻ መጋቢት መጨረሻ፣ ሶስተኛውን
እርሻ ሃምሌ 5 አርሰዉ ቢቢኤም ተጠቅመው ሃምሌ 18 ቀን ትክክለኛ የንሽ
ወቅት ስለነበር የዘር ስራውን አከናውነዋል።
አርሶአደሮቹ የተጠቀሙት የስንዴ ዝርያ ዳንፊን ሲሆን የዘር መጠኑ 37.5 ኪ.ግ
ነበር ። ስንዴው የተዘራው በብተና ነው። እያንዳንዳቸዉ የተጠቀሙት የማዳበሪያ
መጠን 0.5 ኩ/ል ዳፕና 0.25 ኩ/ል ዩሪያ ሲሆን አጨማመሩም በዘር ወቅት
ዳፑን ሙሉ በሙሉና አንድ ሶስተኛውን ዩሪያ በመቀላቀል በማሣው ላይ
በትነዋል። የመጀመሪያውን አረም ስንዴው በተዘራ በ 24ኛው ቀን ከአከናወኑ
በኋላ ቀሪውን ዩሪያ የአፈሩን ዕርጥበት ግምት ውስጥ በማስገባት በብተና
ጨምረዋል። ሁለተኛው አረም ደግሞ ሀምሌ መጨረሻ ላይ ተከናውኗል።
አርሶአደሮቹ በክረምት ወቅት የቦይ ከፈታ ስራ የሠሩ ሲሆን ሠብሉ ለመታጨድ
ሲደርስ ታህሳስ 20 /2012 ዓ.ም ተሰብስቦ እንዲከመር ተደርጓል። ከዚያም መሬቱ
መጀመሪያ ተጠርቦ፣ ውሃ ተርከፍክፎ፣ገለባ ተነስንሶና በሰው እግር በሚገባ
ተጠቅጥቆ እንዲደርቅ ከተደረገ በኋላ የዉቂያ ስራዉ የካቲት 20 ቀን የውቂያ
ስራው ተከናውኗል። አርሶአደር አቶአራጋዉ ዘይኑ ከ0.25 ሄ/ር መሬት ላይ
17.5 ኩ/ል የስንዴ ምርት ወይም በሄ/ር ስሌት 70 ኩ/ል አግኝቷል።
19
ተግባሩን ለሚያከናውኑ አርሶአደሮች የተግባር ስልጠና በመስጠት
በኩል የወረዳና የቀበሌ ግብርና ባለሙያዎች ድርሻቸውን
ተወጥተዋል።
20
የአ/አደሮቹ ወጭ እና ገቢ
6. የወጭ ዝርዝር
ተ.ቀ የስራእና አራጋዉ ይመር አረብ ሁሴን መሃመድ
የግባዕት
ዘይኑ ከበዴ አህመድ
ዝርዝር
ወጭ ገቢ ወጭ ገቢ ወጭ ገቢ ወጭ ገቢ
1.6 መሬት 0 0
ኮንትራት
1.7 ለቀን 320 240
ሰራተኛ
1.9 ጠ/ወጭ 6139 4119 4419 5340
21
6.1.2.ማጠቃለያ
የግብርናው ዘርፍ የሃገሪቱ ዋናው የኢኮኖሚ ምሰሶ በመሆኑ ግንባር ቀደም/
ምርጥ አ/አደሮች የፈጸሙትን ተግባርና ያገኙትን ውጤት ሌሎችም አ/አደሮች
እንድተገብሩትና ተጠቃሚ እንድሆኑ በስፋት በሰራት ይኖርበታል፤
o በምርጥ /በግንባርቀደሞችም ሆነ በሌሎች አ/አደሮች የሚመረቱ ምርቶችን
በገበያ ተፈላጊና የተሸለ ዋጋ ሊያወጡ የሚችሉ ማድረግ ይጠበቃል፤
o ምርትና ምርታማነትን ለመጨመር፤ በገበያ ተፈላጊና የተሸለ ዋጋ ያላቸውን
ምርቶች ለማምረት ግብዓትና ቴክኖሎጅን አጠቃቀም ተደራሽነትን በሁሉም
አ/አደሮች በእኩል መጠን፤ ጥራትና ጊዜ ለማስረጽ ሰፊ ርብርብ ማድረግ
ያስፈልጋል፤
o ይህ የምርጥ ልምድ የተለያየ አካባቢዎች የተወሰደ ስለሆነ የተገኘውን
ምርጥ ልምድ ከአንዱ አካባቢ ወደ ተመሳሳይ አካባቢ በማሸጋገር
እንዲተገበር ማድረግ የእያንዳንዱ ወረዳ የግብርና ልማት ጽ/ቤት ኃላፊነት
ሊሆን ይገባል፡፡
22