Professional Documents
Culture Documents
ሀዋሳ
በራስ መተማመን ማለት እንደ ጴጥሮስ ሦስቴ ከመካድ መታቀብ ወይም መዳን ማለት
ነው፡፡ ማቴ ፳፮፡ ፸
በዚህ ትርጉም መሰረት በራስ የመተማመን ክህሎት የሚከተሉትን ደረጃዎች ተግባራዊ
ማድረግ ይጠይቃል፡-
የምንፈልገውን ነገር ምን እንደሆነ እና ለምን እንደፈለግነው መረዳት
የፈለግነው ጉዳይ በእርግጥ አስፈላጊ መሆኑን ማረጋገጥና ማመን፡፡
ያለንበትን ተጨባጭ ሁኔታ ያገናዘበ ተገቢ እና ህጋዊ የመፍትሄ እርምጃ
(የፈለግነውን ነገር የማግኛ መንገድ) መምረጥ
የመፍትሄ እርምጃውን ያለምንም ፍርሃት ተግባራዊ ማድረግ
ከፈጣሪ በታች ፈጣሪን በማመን …
በራስ መተማመን ሲባል ከሁለት ጠባያት ራስን ማራቅ ነው፡ - ይሉኝታ እና
አምባገነን ከሆኑ ጠባያት
ይሉኝታ (ፈሪነት)፡ - የምንፈልገው ምን እንደሆነ እና ለምን
እንደፈለግነው እያወቅን ይሣካልን ዘንድ ምንም ዓይነት እርምጃ
አለመውሰድ፡፡
አምባገነን (በራስ መመካት)፡ - የምንፈልገው ምን አንደሆነ እና ለምን
እንደፈለግነው እያወቅን የፈለግነው ነገር (ጉዳይ) ይሳካልን ዘንደ
ሁኔታውን (ቦታውን፣ ሰዎችን፣ ወዘተ) ያላገናዘበ ተገቢ ያልሆነ ወይም ህገ
ወጥ እርምጃ መውሰድ ነው፡፡ ምሣሌ በድብድብ፣ በማስፈራራት፣
በማታለል (በብልጠት)፣ ወዘተ የፈለጉትን ለማሳካት መጣር፡፡
ጥልቅ ስሜትን መቆጣጠር
የሰው ልጅ እንደ እንስሳነቱ እንስሣዊ ጠባያት ያለው ቢሆንም እንደ ሰውነቱ ሰዋዊ
ጠባያት ይጐላበታል፡፡
በዚህ ረገድ እንስሳዊ የሚያሰኘው ጠባዩ በስሜት መጓዙ ነው፡፡
በመሰረቱ ስሜታዊ መሆን ተፈጥሮአዊ ነው፡፡ ነገር ግን ምንም ይሁን ምን ስሜታዊነት
ከሚጠበቀው በላይ ሲገን ተገቢ ስሜት ነው ማለት ያስቸግራል፡፡ ለምሳሌ መፍራት ተገቢ
ሊሆን ይችላል ነገር ግን ከመጠን ያለፈ ፍርሃት ተገቢ ነው ማለት ይከብዳል፡፡ ይህን
ዓይነት ጠባይ እግዚአብሔርን መርሳት ወይም አለማመን ነው፡፡ በተመሳሳይ መውደድ፣
መናደድ፣ መቆጨት፣ ማዘን፣ መደሰት፣ ወዘተ በልክ እስከሆነ ድረስ ተገቢ ነው፡፡
ነገር ግን ልክ አጥቶ ራስን ሊጎዳ በሚችል ደረጃ በውስጣችን ከነገሰ የቱም ይሁን የቱ
ተገቢ ነው ማለት አይቻልም፡፡ እንዲህ ዓይነቱን ስሜት ነው ጥልቅ ስሜት የሚባለው፡፡
ጥልቅ ስሜትን መቆጣጠር
ጓደኛ በህይወት ውስጥ ቅመም ቢሆንም ጓደኝነት በጥንቃቄ ሊያዝ የሚገባው ግንኙነት መሆኑ
መጤን አለበት፡፡
በጓደኞቻችን አማካይነት የሚደረግብን ተጽዕኖ (ግፊት) ብዙውን ግዜ መልካም እና ተገቢ
ቢሆንም አልፎ አልፎ ያልተገባ እና ጎጂ ሊሆን ይችላል፡፡
እናጥና፣ መጠጥ ጎጂ ነው መጠጣት የለብንም፣ ከሰው ጋር መጣላት ጉዳት እንጂ
ጥቅም የለውም፣ ሰው ክቡር ነው ሰው ማክበር ይገባናል፣ መስረቅና ማታለል ፀያፍ ነው፣
ወዘተ ዓይነት ግፊቶች እጅግ መልካም ተጽዕኖዎች ናቸው፡፡
በአንጻሩ የሌሎችን ንብረት መዝረፍ፣ ሳይሰሩ ለመበልፀግ የሚደረግ ጥረት፣ ሌሎችን
ጎድቶ ራስን ማስደሰት ወይም ማበልፀግ፣ ሌሎችን ለአደጋ መዳረግ፣ መስረቅ፣ ወዘተ
ዓይነት ግፊቶች ያልተገቡ ጎጂ የአቻ ግፊቶች ናቸው፡፡
የአቻን ግፊት መቋቋም …
በአጭሩ የአቻ ግፊት ማለት በመልካምም ይሆን በጎጂ ጎኑ የራሳችንን አቋም ትተን
የጓደኛችንን አቋም እንድንከተል የሚደረግ ግፊት ወይም ተጽዕኖ ነው፡፡
እንዲህ ዓይነት ተጽዕኖ የራሳችን የምንለውን አመለካከት፣ እምነት እና ጠባይ
እንድንለውጥ የሚያደርግ ተጽዕኖ ነው፡፡
የአቻ ግፊት በበጎ ጎን ሲሆን ጠቃሚ የሚሆነውን ያህል ባልተገባ መልኩ ሲሆን ደግሞ
ይብዛም ይነስም ጎጂ ነው፡፡
በዚህ መሰረት አንዳንድ ጊዜ ጓደኞቻችን የምናምነውን ትተን የማናምነውን፣ የሚገባውን
ትተን የማይገባውን እንድንሰራ ሊገፋፉን እንደሚችሉ በመገመት እና በማመን ያለንን
ግንኙነት በጥንቃቄ ልንመራ ይገባል፡፡ ለዚህ ሚዛን መሆን ያለበት ቃለ እግዚአብሔር ነው፡፡
ለዚህም ሲባል የጓደኛን ተጽዕኖ መቋቋም የሚያስችል ክህሎት ልናዳብር ይገባል፣ ይህም
እጅግ አስፈላጊ መሆኑን መረዳት ይገባል፡፡
የአቻን ግፊት መቋቋም …
የጓደኛን ተጽዕኖ መቋቋም ማለት ያመንባቸውንና መሆን ይገባቸዋል የምንላቸውን ጉዳዮች
በተመለከተ በማይስማማ መልኩ እንድንጥስ ሲገፋፉን አይሆንም ብሎ መከላከል ነው፡፡ ቲቶ
፫፡ ፲ - ፲፩
ለምንወዳቸው ጓደኞቻችን ‘አይሆንም’ ማለት እጅግ ከባድ መሆኑ እውን ነው፡፡
ምክንያቱም አይሆንም ስንላቸው ስለእኛ የሚፈጥሩት ግምት ምን ሊሆን እንደሚችል ማሰቡ
በራሱ ያስጨንቃልና ነው፡፡
ከጓደኛችን ጋር በማያጣላንና የጓደኛችንን ክብር በማያሳጣን መልኩ ‘አይሆንም’ ማለት
የሚያስችለን ጥሩ መንገድ (ደረጃዎች) እንዳሉ ሊታወቅ ይገባል፡፡ እነኝህም ደረጃዎች
የሚከተሉትን አማራጮች ይይዛሉ፡ -
የግፊቱን ወይም ህገ ወጥ ተግባሩን በግልጽ ለጓደኛችን መንገርና ስህተትነቱን (ህገ
ወጥነቱን) እንዲያስተውሉ ማስቻል
በግፊቱ ምክንያት የሚከሰተውን ስህተት ሊያስከትል የሚችላቸውን አደገኛ
ውጤቶች መግለጽ (ግልጽ እንዲሆንላቸው ማድረግ)
የአቻን ግፊት መቋቋም …
ሊከናወን የታሰበው ተግባር ራስንም ሆነ ሌሎችን በማይጎዳ መልኩ ተግባራዊ
ሊደረግ የሚችልባቸው ሌሎች መንገዶች ካሉ መግለጽ (ማሣየት)
ይህን ሁሉ ገልጸን ጓደኛችን አይሆንም ብሎ(ላ) መጀመርያ ባሰበው(ችው) አደገኛ
መንገድ ካልሄድኩ የሚል(የምትል) ከሆነ መብቱ(ቷ) መሆኑን በመግለጽ መተው
ተገቢ ነው፡፡
ይሁንና በማንኛውም ሰዓት ወደ እኛ አስተሳሰብ መምጣት የሚፈልግ(የምትፈልግ)
ከሆነ ግን በደስታ የምንቀበላቸው መሆኑን መግለጽ ተገቢ ነው፡፡
ልብ በሉ ጓደኛችን (ጓደኞቻችን) መብታቸውን አክብረን ከእኛ ፍላጎት (ዕምነት)
ውጭ ወደ ሌላ መንገድ ሲሄዱ እንደተውናቸው (እንደፈቀድንላቸው) ሁሉ እነሱም
እኛ ወደ አመነው ተግባር እንድናመራ ይፈቅዳሉ ተብሎ ይታመናል፤ መብታችንንም
ማክበር ይጠበቅባቸዋልና፡፡ ይህ ካልሆነ ግን ምኑን ጓደኛ ሆኑ!
የአቻን ግፊት መቋቋም …
በአጭሩ እኛ መብታቸውን እናከብራለን እና እነርሱም የእኛን መብት ሊያከብሩ ይገባል
(ያከብራሉም)፡፡ ካላከበሩ ግን ጓደኞቻችን መሆን አይችሉምና በግልጽ ልንነግራቸው
ይገባል፡፡
ይህንንም አልረዳ ካሉንም ጓደኝነታችንን ልናቋርጥ ይገባል፡፡ ጓደኝነታችንን ችግር
ከተፈጠረ በኋላ በጥል ከምናጣ ችግር ከመፈጠሩ በፊት ሣንጣላ በስምምነት ብንለያይ
ይሻላል፡፡ ተግባር ፬
አንዳንድ ጊዜ በጓደኛ ተጽዕኖ አማካይነት ሊከሰት የሚችልን ችግር አስቀድሞ በመገመት ራስን
ማዘጋጀት ይቻላል፡፡ ለዚህም የሚከተሉትን ቀላል መንገዶች መከተል ተገቢ ነው፡ -
ሊከሰቱ የሚችሉ ችግሮችን ቀድሞ መገመት
ችግሮቹ ቢከሰቱ ምን ማድረግ እንደምንችል አስቀድሞ መወሰን
የምንለያቸው የመፍትሄ መንገዶች ችግሮቹን በቁጥጥራችን ስር ማዋል የሚያስችሉን
ወይም ከነአካቴው የሚያስወግዱልን መሆኑን ማረጋገጥ፡፡ ይህ ካልሆነ ግን ‘ያልጠረጠረ
ተመነጠረ' እንዳሉት እንደሚገጥመን አይጠርጥሩ፡
ያለ አደጋ አለመግባባትን መፍታት
ሰዎች በጋራ በምንኖርበት አኗኗራችን ውስጥ በመካከላችን አለመግባባት እና
ግጭት ሊከሰት ይችላል፡፡ ይህ ሊከሰት የሚችል በመሆኑ ምንም የሚያስገርም
አይደለም፡፡ ሌላ ቀርቶ በጣም ከምናፈቅረው ሰው ጋር ልንጋጭ እንችላለን፡፡
ትልቁ ቁም ነገር ከሰዎች ጋር የማያግባቡን ነገሮች ተጋንነው ከቁጥጥር ውጭ
እንዳይሄዱ መጠንቀቅ አስፈላጊ መሆኑን መረዳት ነው፡፡
በመሰረቱ ልዩነቶች እርስ በእርስ ለሞሞራረድ እና ከአንድ የስብዕና ደረጃ
ወደተሻለ የስብዕና ደረጃ ለመሸጋገር ጥሩ መሰረት ናቸው፡፡
ነገር ግን ከላይ እንደተገለፀው ከቁጥጥር ውጭ የመውጣት ዕድል ካገኙ ወደ
ከፋ አደጋ ሊያመሩ ይችላሉ፡፡
ያለ አደጋ አለመግባባትን …
ትንሿን ግጭት ‘ሣይቃጠል በቅጠል' እንደሚባል በእንጭጩ መቅጨት ብልህነት ነው፡፡ ይህ
ታዲያ ስሜትን የመቆጣጠር ክህሎትን፣ ጭንቀትን የመቋቋም ክህሎትን የድርድርን
ክህሎትን በተገቢው ቦታና መንገድ ተግባራዊ እንድናደርግ ይሻል፡፡
ያለ አደጋ አለመግባባትን ለመፍታት የሚከተሉትን ነጥቦች ተግባራዊ ማድረግ ይመከራል፡-
ለሌላው ሰው ምን እንደሚያስጨንቅህ (ያለመግባባታችሁን ምክንያት) በጥሩና ፍቅር
በተመላበት መልኩ መግለጽ፡፡
ስሜትሽን ተቆጣጠሪው እንጂ እንዲቆጣጠርሽ ዕድል አትስጪው፡፡
ሌላውን ሰው በሚገባ አድምጠው በሚገባ ልትረዳውም ሞክር፡፡
በዚህ ረገድ ስም መጥራት፣ መስደብ፣ መቆጣት፣ መጮህ፣ ለመማታት መቃጣት
(መማታት) … ፈጽሞ አይገባም፡፡
ማቻቻል የሚያስችል መንገድን መፈለግ፡፡
ለሰዎች መራራት
መራራት (ማዘን) ማለት በሰዎች ችግር ውስጥ ራስን አስገብቶ ችግሩን እንደራስ ችግር አድርጎ
ለመቅረፍ ጥረት ማድረግን ያመለክታል፡፡
ይህ ማለት የሰዎችን ችግር በመረዳት ያሉበትንም ሁኔታ ከራስ ሁኔታ ጋር በማገናኘት (እኛም
እንደ እነርሱ ባለ ሁኔታ ውስጥ ልንገባ እንደምንችል በማሰብ) ችግራቸውን በመጋራት
ችግራቸው የሚቀልበት (ከተቻለም ሙሉ በሙሉ የሚቀረፍበትን) ሁኔታ ማመቻቸት ማለት
ነው፡፡
እንዲህ ዓይነት ህይወት ሲጀመር አደጋ የበዛበትና ውስብስብ ሊሆን የሚችል ቢሆንም ውጤቱ
ግን እጅግ አርኪ መሆኑን መረዳት ይገባል፡፡
ለሰዎች ማዘን የህይወት ክህሎት በአጭሩ ሲጠቃለል ሰዎችን በመርዳት ራሣቸውን ችለው
ኑሮአቸውን መኖር እንዲችሉ ማድረግ ነው፡፡
ይህ በሰዎቹ ውስጥ የጥገኝነት ስሜት መፍጠርን አይሻም፡፡ ይልቁንም በሁለት እግራቸው
ቆመው በራሣቸው ጉዳይ ራሣቸው መወሰን የሚችሉ ማድረግ ነው፡፡
የመደራደር ክህሎት
የመደራደር ክህሎት የጓደኛን ተጽዕኖ ለመቋቋምና እርስ በእርስ ለመግባባት እጅግ
አስፈላጊ የሆነ የህይወት ክህሎት ነው፡፡
ይህ የህይወት ክህሎት በውስጡ በራስ የመተማመን ክህሎት፣ ለሰዎች የማዘን ክህሎት፣
እና ነገሮችን (ጉዳዮችን) ከራስ መርህ ጋር የማቻቻል ወይም የማጣጣም ችሎታ የሚጠይቅ
(በውስጡ የሚያካትት) የህይወት ክህሎት ነው፡፡
ይህ ክህሎት የራስን ጥቅም አሣልፎ ባለመስጠት የሌሎችንም ጥቅም አሣልፎ
ባለመውሰድ ወይም የራስን ጥቅም ሊከሰት ካለ (ከተከሰተ) ችግር አንጻር አሣልፎ ወይም
ከፍሎ በመስጠት (ዋጋ በመክፈል) ከችግር ራሣችንን የምናወጣበት (የምንታደግበት)
የህይወት ክህሎት ነው፡፡
ምድራዊ በሆነ በማንኛውም ነገር መደራደር ይቻላል፤ ነገር ግን የማንደራደረው አንድ
ወሳኝ ነገር አለ - ክርስትናችን፡፡
፫. ችግሮችን የማስተዋልና የመፍታት ክህሎቶች፡፡
ችግሮች በተለያዩ ምክንያቶች ይከሰታሉ፡፡ ከዚህ አንጻር ችግርን አታምጣብኝ ማለት
ይከብዳል፤ ምክንያቱም የችግር መግቢያ ቀዳዳዎቹ ብዙ ናቸውና፡፡ ይልቁንም ችግርን
የምቋቋምበት አቅምና የማሸንፍበትን ጥበብ አድለኝ ማለት የተሻለ ፀሎት ነው፡፡
ችግርን ለመቋቋም ብሎም በአሸናፊነት ለመዝለቅ የዚህ የህይወት ክህሎት ዘርፍ
ውስጥ የሚመደቡትን የህይወት ክሂሎች በራስ ውስጥ ማልማት እጅግ በጣም አስፈላጊ
እና ጠቃሚ ነው፡፡
በዚህ የህይወት ክህሎት ዘርፍ ውስጥ የሚመደቡትን የህይወት ክሂሎች በዝርዝር
እንመለከታለን፡፡ እነሱም
በጥልቀት የማሰብ (አርቆ የማስተዋል)
ፈጠራዊ አስተሣሰብ ክህሎት
ውሣኔ የመስጠት ክህሎት
ችግር የመፍታት ክህሎት
በጥልቀት የማሰብ (አርቆ የማስተዋል)
አርቆ የማስተዋል ክህሎት በአንድ ሃሳብ፣ ጉዳይ፣ ነገር፣ ሁኔታ፣ ወዘተ ላይ የሚደረግ
ምክንያታዊ ግምገማን ያመለክታል፡፡
እንዲህ ዓይነት ግምገማ ሲደረግ መስፈርት መጠቀም ተገቢ ብቻ ሣይሆን ግድም
ነው፡፡
ከዚህ አንጻር አርቆ የማስተዋል ክህሎት የአንድን ሃሳብ፣ ነገር፣ ሁኔታ፣ ወይም ጉዳይ
ብቃት በጥንቃቄ መመዘን የምንችልበት ብልህነትን መሰረት ያደረገ የግምገማ እና
የማስተዋል ስርዓት ወይም ጥበብ ሲሆን ሰዎች ምን ማመን እና እንዴት መስራት
እንዳለባቸው የሚወስኑበት መንገድ ነው፡፡
በጥልቀት ማሰብ ከምክንያታዊነት ጋር ወይም እኛ ካለን ምክንያታዊ አስተሳሰብ ጋር
ይያያዛል፡፡ ምክንያታዊነት ማለት አንድን ነገር ለማመን ወይም ላለማመን ወይም
ተግባራዊ ለማድረግ ወይም ላለማድረግ ወይም ችግርን ለመፍታት ምክንያትን
(ምክንያቶችን) መጠቀም ማለት ነው፡፡
በጥልቀት የማሰብ (አርቆ የማስተዋል)
ምክንያታዊነት ደግሞ የሚጀምረው ከራሳችን መሆኑ መታወቅ አለበት:: ይህም በውስጡ
የሚከተሉትን ያካትታል፡ -
ለምናምነው እና ለምንሰራው ምክንያት እንዲኖረን ማድረግና ምክንያቶቹንም መረዳት
የራሳችንን ዕምነት እና ሥራ በጥልቀት መመርመር
ለዕምነታችን እና ለተግባራችን ምክንያት የሆኑትን ጉዳዮች ለሌሎች ማስረዳት
መቻል፡፡
ተግባር ፭፡ - ለምን የማ/ቅ ኣባል ሆናችሁ?
አርቆ የማስተዋል ክህሎት በሚገባ የታለመና በግለሰብ ደረጃ የተቀነባበረ የአስተሣሰብ
ሂደት ሲሆን መረጃዎችን፣ ዘዴዎችን፣ መስፈርቶችን፣ ሁኔታዎችን፣ ወዘተ
የምናብራራበት፣ የምንተነትንበት፣ የምንገመግምበት ብሎም ያንን ተከትሎ ሊመጣ
የሚችለውን ሁኔታ የምንገምትበት ሂደት ነው፡፡
በጥልቀት የማሰብ (አርቆ የማስተዋል)
አርቆ የሚያስብ ሰው ዘወትር መጠየቅ፤ መመርመር ለሚነሱ (ለሚያነሳቸው) ጥያቄዎች መልስ
ለመስጠት የሚተጋ፣ ሚዛናዊ የሆነ አዕምሮ ያለው፣ ነገሮችንም በዚህ መሰረት የሚመዝን፣ ተገቢና
አስፈላጊ መረጃዎችን በመፈለግ ረገድ ትጉህ (ታታሪ) የሆነ፣ አጥጋቢ የሆኑ መስፈርቶችን ሚዛናዊ
በሆነ መልኩ የሚለይ፣ ነገሮችን ወይም ሁኔታዎችን ለመመርመር (ለመመልከት) ፈቃደኛ የሆነ፣
ለውጤት እስከመጨረሻው የሚፀና፣ ….. ጠባይ አለው፡፡
በዚህ መሰረት በጥልቀት የሚያስብ ሰው ጥያቄ ይጠይቃል፣ መልስ ይፈልጋል፣ አማራጭ
መፍትሄዎችን ያነጻጽራል፤ ይህንንም ተከትሎ የማይፀፅተውን ውሣኔ ይወስናል፡፡
በጥልቀት የማሰብ ክህሎት በውስጡ ተያያዥ የሆኑ በርካታ ግቦችን የያዘ እንጂ እሱ ብቻውን ለራሱ
ያለቀለት ግብ ነው ማለት አይቻልም፡፡
በዚህ መሰረት ሰዎች በጥልቀት የማሰብ ክህሎትን ሲያዳብሩ ከሱ ጋር በተያያዘም ሣይንሳዊ
የምርምር ባህርይን፣ የፈጠራዊ አስተሳሰብ ክህሎት፣ ውሣኔ የመስጠት ክህሎት ብሎም ችግር
የመፍታት ክህሎትም አብረው ይዳብራሉ፡፡
ፈጠራዊ አስተሣሰብ ክህሎት
ፈጠራዊ አስተሣሰብ ክህሎት በጥልቀት የማሰብ የህይወት ክህሎትን ተያይዞ (ተከትሎ)
የሚያድግ የህይወት ክህሎት ሲሆን ወደ አዲስ አመለካከት፣ አዲስ አማራጭ መንገድን
የመለየት፣ ነገሮችን በአዲስና ለየት ባለ መንገድ መረዳትን የሚያመጣና የሚያካትት
ነው፡፡
በሌላ አገላለጽ ፈጠራዊ አስተሳሰብ ክህሎት ነገሮችን በሚደነቅ መልኩ የምናይበት
ወይም የምንሰራበት መንገድ ሲሆን በአራት ይዘቶች ወይም ጠባያት ይገለጻል፤ እነሱም፡
-
አንደበተ ርቱዕነት (አዳዲስ ሃሳቦችን ማፍለቅ)፣
ተለማጭነት (አስተሳሰብን በቀላሉ መቀየር)፣
የመጀመርያነት (አዲስ ነገር መፀነስ) እና
ማብራራት (በሌሎች ሃሳብ ላይ መገንባት ወይም ማዳበር) ናቸው፡፡
ፈጠራዊ አስተሣሰብ ክህሎት
በመሰረቱ አለማችን በአንድ ቦታ የቆመች የረጋች አይደለችም፡፡ ይልቁንም ዘወትር
በለውጥ ላይ የምትገኝ እንጂ፡፡
በዚህ መሰረት የሰዎች ህይወትም ዘወትር በዚህ ተለዋዋጭ ዓለም ውስጥ አዳዲስ
ከሆኑ ሁኔታዎች ጋር መጋፈጥ ግድ ይላታል፡፡
ህይወት በየጊዜው የሚገጥሟትን ያልተገመቱ እና ያልተለመዱ ሁኔታዎችን
ተቋቁማና አሸንፋ መዝለቅ እንድትችል ይህ ፈጠራዊ አስተሣሰብ የህይወት ክህሎት
ጥቅሙ ጉልህ እና በህይወት ውስጥም ወሳኝ ነው፡፡
ይህ የህይወት ክህሎት በውስጣችን ካልዳበረ በሚገጥሙን ያልተጠበቁና ያልተለመዱ
ችግሮች ተጠላልፈን መውደቃችን በአብዛኛው አይቀሬ ነው -
ፈጠራዊ አስተሣሰብ ክህሎት
ፈጠራዊ አስተሣሰብ ከላይ እንደተገለፀው ራሱን ችሎ ብቻውን
የሚከሰት ሳይሆን እንደ ቀስተ ደመና በውስጡ በጥልቀት ማሰብ፣ ውሣኔ
የመስጠት ክህሎት እና ችግር የመፍታት ክህሎት አቆራኝቶ ይዟል፡፡
በሌላ አባባል እነኝህ የህይወት ክህሀሎቶች እርስ በእርሳሰቸው
የተቆራኙ ናቸው ማለት ነው፡፡
የተጠቀሱት የህይወት ክህሎቶች ያላቸውን ተያያዥነት መረዳት
ያቻለን ዘንድ የተቀሩትን የህይወት ክህሀሎቶች እንመለከታለን፡ -
ውሣኔ የመስጠት ክህሎት
ውሣኔ የመስጠት ክህሎት ይህ ይሻላል፣ ይህ አይሻልም፣ ይህ ይበጃል፣ ይህ ተገቢ አይደለም፣
ወዘተ ማለትን የሚጠይቅ የህይወት ክህሎት ነው፡፡
በሌላ አባባል ውሳኔ የመስጠት ክህሎት ሊሆኑ ከሚችሉ የተለያዩ አማራጮች ወይም
ምርጫዎች መካከል የተሻለውን የመምረጥ ክህሎት ነው፡፡
በመሰረቱ ውሣኔ የሚሹ (ምርጫ እንድንመርጥ የሚያስገድዱን) በርካታ ጉዳዮች በየዕለቱ፣
በየሰዓቱ፣ በየደቂቃው፣ በየሰከንዱ ይገጥሙናል፡፡ ይሁንና አንዳንዶቹ በባህርያቸው በጣም ተራ
በመሆናቸው ሌላ ቀርቶ ስሜትም ላይሰጡን ይችላሉ፡፡ አንዳንዶቹ ግና እጅግ ትኩረት የሚሹና
ህይወታችንን የሚያናጉ በመሆናቸው ከፍተኛ ጥንቃቄን ይፈልጋሉ፡፡
ምንም ይሁን ምን የምንወስነው ውሳኔ ውጤታማ በሆነ ደረጃ (ፀፀት በማያስከትል መልኩ)
መወሰን አለበት፡፡
ለዚህም ውሳኔ ከመወሰናች በፊት የውሣኔዎቻችንን ቀጣይ ውጤት በጥንቃቄ መተንበይ ወይም
መመዘን አስፈላጊ ነው፡፡
ውሣኔ የመስጠት ክህሎት