You are on page 1of 1

n 82

HR Ad hocinformation communication kit

ኢትዮ ቴሌኮም የሙያ መሰላል(Career Path )ስርዓት አካል የሆነውን የሙያ


ዕድገት (Career progression) አሰራር ተግባራዊ ሊያደርግ ነው
ኢትዮ ቴሌኮም የሰራተኞቹን ምርታማነት ለማሳደግ፣ የስራ ተነሳሽነታቸውን ለመጨመር፣ የአፈፃፀም ብቃታቸውን ለማሻሻልና
በየትኛውም ቦታና ሁኔታ ውስጥ ተወዳዳሪና ውጤታማ የሆነ ሰራተኛ ለመፍጠር የሰው ሀይል አመራሩን በየጊዜው እያሻሻለ ይገኛል፡፡
የዚህ የሰው ሀይል አመራር ማሻሻያ አካል የሆነው የሙያ መሰላል/አቅጣጫ (Career Path ) ትግበራ አንዱና ዋነኛው ነው፡፡

የሙያ መሰላል/አቅጣጫ (Career Path ) ማለት


አንድ ሰራተኛ በስራ ዘመኑ በተለያዩ የስራ መደቦችና
ቦታዎች ላይ ተዘዋውሮ የሚሰራበት ሁኔታ ሲሆን፣ ይህ
ዝውውር ወደጎን (Horizontal) ፣ ወደላይ (Ver-
tical/)እንዲሁም አግድም (Cross func-
tional) ሊሆን ይችላል፡፡ ኬርየር ፓዝ ስንል ሁሉንም
ዓይነት ምደባዎች ማለትም ዝውውርን፣ የስራ ማዕረግ
ለውጥንና ዕድገትን ኮምፒተንሲን መሰረት በማድረግ
የሚሰራ ማለት ነው፡፡ በኢትዮ ቴሌኮም የሚተገበረው
የኬርየር ፓዝ ከላይ በተገለፀው መልኩ ሰራተኞች ወደ
ተለያየ የስራ ክፍል ተዘዋውረው የመስራት ዕድልን
የሚሰጣቸው ሲሆን፣ እነዚህ የዝውውርና የዕድገት እድሎች የሚፈፀሙት ሰራተኞች ለስራው የሚያስፈልጋቸውን ኮምፒተንሲ ማለትም
ዕውቀት፣ ክህሎት፣ ችሎታና የግል ስብዕና መሰረት በማድረግ ይሆናል፡፡ በመሆኑም በኢትዮ ቴሌኮም የሚተገበረው የኬርየር ፓዝ
ኮምፒተንሲን መሰረት ያደረገ ይሆናል ማለት ነው፡፡

የሙያ መሰላል/አቅጣጫ (Career Path ) ከሚተገበርባቸው መንገዶች አንዱ የሙያ ዕድገት (Career progression) ስርዓት ሲሆን፣
የሙያ ዕድገት (Career progression)ማለት ከአንድ ዝቅተኛ ንዑስ የስራ መደብ(Sub band) ወደሚቀጥለው ከፍተኛ
ንዑስ የስራ መደብ ሰራተኛው በሚቀመጡ መስፈርቶችና የመምረጫ ስርዓቶች እንዲሸጋገር የሚደረግበት ስርዓት ነው፡፡ ይህ በተለመደ
መልኩ በማስታወቂያ ከሚተገበረው የዕድገት አሰራር የተለየ ሲሆን፣ በዚህ ስርዓት የሚደረገው ምደባ ያለማስታወቂያ በየስራ ክፍሉ
ውስጥ ያሉትን ሰራተኞች እርስ በርስ በማወዳደርና ለምርጫ የተቀመጡትን የመምረጫ መስፈርቶች በተሻለ ውጤት የሚያልፉትን
ወደሚቀጥለው ሰብባንድ እንዲሸጋገሩ የሚያደርግ ስርዓት ነው፡፡ ይህ ስርዓት ቀደም ሲል ያልነበረ ሲሆን፣ የኬርየር ፓዝ ስርዓትን
መጀመር ተከትሎ የሚተገበር አዲስ አሰራር ይሆናል ማለት ነው፡፡

የሙያ ዕድገት (Career progression) ስርዓትን መተግበር ካስፈለገባቸው ምክንያቶች ውስጥ


• ተከታታይነት ያለውን ትምህርትና መሻሻል የሚያሸልምና ዋጋ የሚያሰጥ የስራ አካባቢንና ባህል መፍጠር፣
• የሰራተኞችን ንቁ ተሳታፊነትና የስራ አፈፃፀም ከኩባንያው ፍላጎት ጋር በተናበበ መልኩ ለማሳደግ፣
• በተቀናጀ ትምህርት ማለትም በሰራተኛው የግል ጥረት የሚወሰድ ትምህርትን፣ በኩባንያው አነሳሽነት የሚሰጥ ስልጠናና
ትምህርትን እንዲሁም በስራ አካባቢ ከቡድን የስራ ባልደረቦች የሚገኝ ትምህርትና ተሞክሮን በማጣመር እና ቀጣይነት ያለው
የሰው ሀብት ልማት ስራ በመስራት የስራ ጥራትን ለማረጋገጥ፣
• ልዩ የሆኑ ችሎታዎችን /ተሰጥኦዎችን/ ከውጭ ለመሳብና በውስጥ ያሉትንም ለማቆየት፣
• የኩባንያችን የሰው ሀይል ተወዳዳሪና ምርታማ እንዲሆን ለማድረግ እንዲሁም
• ሰራተኞች ወደፊት ያላቸውን የዕድገት አማራጮችና ዕድሎችን በማሳወቅ የስራ ተነሳሽነታቸውንና ተቆርቋሪነታቸውን ለማሳደግና
በተቀመጠላቸው የዕድገት አማራጭ ለመጠቀም ራሳቸውን የማብቃትና የማሻሻል ስራ በተከታታይ እንዲሰሩ ለማነሳሳት የሚሉት
ዋና ዋናዎቹ ናቸው፡፡
ይህንን የኬርየር ፕሮግሬሽን ስርዓት በተሳለጠ መልኩ ተግባራዊ ለማድረግ በስርዓቱ ዙሪያ እንደኩባንያ ያለውን ግንዛቤ፣ ስርዓቱን
በተጨባጭ ግምገማና ውጤት ለመተግበር ከሚያስፈልገን የስርዓትና የሲስተም ዝግጁነት እንዲሁም ይህ ስርዓት በሚፈለገው መልኩ
ተግባራዊ እንዲሆን ሁሉም ሰራተኛ፣ የቅርብ አለቃና ማኔጅመንቱ በየደረጃው የሚጠበቅባቸውን ሃላፊነት ከመገንዘብና ከመወጣት
አንፃር ያለውን የልምድ ማነስ መሰረት በማድረግ አጀማመሩ የስርዓቱን ዋና ዓላማ መሰረት በማድረግ አንድ ሰራተኛ በአንድ የስራ
መደብ በቅጥር ወይም በዕድገት ተመድቦ ውጤታማ ስራ የሚሰራበትን ቢያንስ የሁለት ዓመት የስራ ቆይታና ልምድ፣ በኩባንያው
ሰራተኞች ለዕድገት ለመወዳደር የሚያበቃቸውን የስራ አፈፃፀም ውጤትና የስነ ምግባር ግድፈት(Disciplinary Record )ታሳቢ
በማድረግ እንዲሁም ባለፈው ዓመት የተሰራውን የኮምፒተንሲስ አሰስመንት ውጤት ከግንዛቤ በማስገባት ትግበራው እንዲጀመር
ተወስኗል፡፡ በዚህም የኬርየር ፕሮግሬሽን የመጀመሪያው ዙር ትግበራ ለውድድር የተቀመጡትን የአገልግሎት፣ የስራ አፈፃፀም፣
የዲስፕሊን ረከርድና የብቃት መመዘኛ (Competency assessment ) ውጤት ከሚያሟሉት ሰራተኞች ውስጥ በ70 ፐርሰንት
ኮታ የሚጀመር ሲሆን ለውድድር የሚቀርቡት ሰራተኞች በቃለ መጠይቅ ፈተና ተለይተው በኮታው መሰረት የተሻለ ነጥብ ያገኙ
ሰራተኞች የሰብባንድ ለውጥ /ዕድገት/ በማግኘት የኬርየር ፕሮግሬሽን ተጠቃሚ ይሆናሉ፡፡

ይህ ስርዓት መጠነኛ የዕድገትና የደመወዝ ጭማሪ የሚያስገኝ ስለሆነ አንድ ሰራተኛ በኬርየር ፕሮግሬሽን የሰብ ባንድ ለውጥ ካገኘ የ5
ፐርሰንት የደመወዝ ጭማሪ ይደረግለታል፡፡ በዚህ መልክ የኬርየር ፕሮግሬሽን ዕድል ተጠቃሚ የሆነ ሰራተኛ ወደሚቀጥለው የኬርየር
ፕሮግሬሽን ለመወዳደርና ለማደግ ቢያንስ ሁለት ዓመት መስራት ያለበት ሲሆን በመደበኛው ምደባ በማስታወቂያ ለሚደረግ የዕድገት
ውድድር ለመሳተፍ ግን ቢያንስ አንድ ዓመት ማገልገል ይኖርበታል፡፡ ስለሆነም አንድ ሰራተኛ አዲስ በሚጀመረው የኬርየር ፕሮግሬሽን
ተጠቃሚ ከሆነ ቢያንስ እስከ አንድ ዓመት ለዕድገት መወዳደር አይችልም ማለት ነው፡፡

በመሆኑም ሰራተኞች በመደበኛ የማስታወቂያ ውድድር


የሚኖራቸውን አማራጭና በኬርየር ፕሮግሬሽን
የሚኖራቸውን አማራጭ በማገናዘብ የሚሻላቸውን
የሚመርጡበት ሁኔታ ይኖራል ማለት ነው፡፡ የዚህ
ስርዓት መተግበር ሰራተኞች ያላቸውን አማራጭ
ከራሳቸው አቅምና ፍላጎት በመነሳት በኩባንያው ውስጥ
ያሉትን አማራጮች በአግባቡ በመፈተሸ የመምረጥ
ዕድል የሚሰጣቸው ስለሆነ ለኩባንያችን ሰራተኞች
የተሻለ መነቃቃትንና ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጥና
ለብዙ ጊዜ በሰራተኞች ሲጠየቅ የነበረውን ጥያቄ

ሰራተኛውንም ኩባንያውን በሚጠቅም መልኩ ምላሽ የሚሰጥ ይሆናል፡፡ ይህ አዲስ ስርዓት በኩባንያው የቆየውን የረዥም ጥያቄ
ከመመለስና በፍጥነት ከመተግበር አንፃር የተጠራቀመውን ጥያቄ ለመፍታት ሲባል በየዓመቱ አንድ ጊዜ ብቻ የሚደረገው የኬርየር
ፕሮግሬሽን ስርዓት ትግበራ ለሚቀጥሉት ሁለት ዓመታት ብቻ በየስድስት ወራት የሚደረግ ይሆናል፡፡ ይህ ማለት በመጀመሪያው
ዙር ያላገኙ ሰራተኞች በሁለተኛው ወይም በሶስተኛ ዙር ተጠቃሚ የሚሆኑበት ዕድል ይኖራል፡፡ ለዚህ ሰራተኞች ከአንደኛ ወይም
ከሚቀጥለው ዙር የሚማሩትን ትምህርት በመውሰድና ማሻሻል የሚገባቸውን ነገር የሚቀጥለው የውድድር ጊዜ ከመምጣቱ በፊት
በማሻሻል ለቀጣዩ ውድድር መቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡ በዚህ መሰረት የመጀመሪያው ዙር የኬርየር ፕሮግሬሽን ምደባ በየካቲትና
በመጋቢት 2019 ወራት በኮርፖሬት፣ በዞንና ሪጅን በሚደረጉ የቃለ መጠይቅ ፈተናዎች የሚጀመር ሲሆን ሁለተኛው ዙር ከስድስት
ወራት በኋላ የሚቀጥል ይሆናል፡፡

በኩባንያው የቆየውን የኬርየር ፓዝ ጥያቄ በፍጥነት ከመመለስ አንፃር የተቀየሰው አሰራር ከሁለት ዓመት በኋላ ግን በየዓመቱ
አንድ ጊዜ ብቻ የሚሆን ሲሆን የመምረጫ መንገዱም ከቃለ መጠይቅ ፈተና በተጨማሪ የፅሁፍ ፈተና እና የ360 ዲግሪ ምዘና
ስርዓትን በማካተት የሚተገበር ይሆናል፡፡ በተጨማሪም ከሁለት ዓመት በኋላ የሚተገበረው የኬርየር ፕሮግሬሽን ስርዓት በደፈናው
በኮታ የሚተገበር ሳይሆን እያንዳንዱ የስራ ክፍል ባስመዘገበው የቀደመው በጀት ዓመት የስራ አፈፃፀም እና ኩባንያው ለዚህ ስርዓት
መተግበር በሚመድበው በጀት ላይ ብቻ ተመስርቶ የሚፈፀም ይሆናል፡፡

በመሆኑም ሰራተኞች በአንድ በኩል ለኬርየር ፕሮግሬሽን የሚያስፈልጉትን ቅድመ ሁኔታዎች እና የኬርየር ፕሮግሬሽን ተጠቃሚ
መሆን ያለውን ጥቅምና ውጤት እንዲሁም በማስታወቂያ ከሚደረግ መደበኛ የእድገት ውድድር ጋር ያለውን መስተጋብር በአግባቡ
በመረዳት ለተግባራዊነቱና ለውጤታማነቱ የራሳቸውን አስተዋፅዖ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል፡፡

የኬርየር ፕሮግሬሽን ስርዓትን ዝርዝር አተገባበር አስመልክቶ በተከታታይ ለሰራተኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ መልዕክቶች የሚተላለፉ
ሲሆን ሁሉም የኩባንያችን ማህበረሰብ ይህ አዲስ ስርዓት የታሰበለትን ዓላማ በማሳካት ሰራተኛውን ደስተኛ ኩባንያውም ውጤታማ
እንዲሆን በሚያስችል መልኩ እንዲተገበር የበኩሉን ሚና እንዲወጣ ከአደራ ጭምር እናሳስባለን፡፡

የሰው ኃይል ዲቪዥን


ጥር 2011 ዓ.ም

Published by: Internal Communications Section

You might also like