You are on page 1of 7

ሐምሌ 15 ቀን 2014 ዓ.

የ2 ኛው ግማሽ ዓመት የስራ አፈጻጸም


ምዘና ትግበራ
ኢትዮ ቴሌኮም ከ2013 በጀት ዓመት ጀምሮ የሠራተኞች የሥራ አፈፃፀም ግምገማ በኦራክል ፐርፎርማንስ
ማኔጅመንት ሲስተምን /OPM/ በመተግበር እየሰራ እንደሆነ ይታወቃል፡፡ በመሆኑም በ2014 በጀት ዓመት
የሁለተኛው ግማሽ ዓመት የሥራ አፈፃፀም ግምገማን ከዚህ በፊት በሲስተሙ ላይ የታዩ ክፍተቶችን በመለየትና
ማሻሻያዎችን በማድረግ ለትግበራ ዝግጁ ተደርጓል፡፡ ስለሆነም ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መርሆዎች
በመከተል እንደ እ.ኤ.አ ከሐምሌ 25 እስከ ነሐሴ 12 ቀን 2022 ይከናወናል፡፡

1. ኦራክል ፐርፎርማንስ ማጅመንት ሲስተም /OPM/ በሚጠቀሙበት ጊዜ መወሰድ ያለባቸው ነጥቦች፡

1. ገምጋሚዎች በስራቸው ያሉትን ሠራተኞች ሲስተሙ ከመዝጋቱ ከ5 ቀን በፊት ገምግሞ/ማ


ለተገምጋሚ መላክ አለበት፡፡
2. አንድ ተገምጋሚ የግምገማው ውጤት ወደ እሱ/ሷ ከተላከ በ5 ቀን ውስጥ የግምገማ ሂደቱን መልሶ
ለገም ጋሚ መላክ አለበት፡፡ በ5 ቀን ውስጥ መመለስ ካልቻለ/ች ሲስተሙ ወደ ገምጋሚው
የግምገማ ሂደቱን የሚመልስ ይሆናል፡፡

3. አንድ ሰራተኛ ሶስት ወር እና ከዚያ በላይ ሌላ ክፍል ሰርቶ በግምገማ ወቅት ሌላ ክፍል ቢገኝ አሁን
ላይ ያለው የቅርብ አለቃው ምንም መሙላት ሳይጀምር Change Main Appraiser የሚለውን
በመጫን ግምገማውን ወደ ሚመለከተው ገምጋሚ ማስተላለፍ አለበት፡፡

1
ሐምሌ 15 ቀን 2014 ዓ.ም

4. Change Main Appraiser በምንጠቀምበት ጊዜ ግምገማ እንዲያረግ የተመረጠው ሰው


የማሳወቂያ መልክት በERP Worklist ላይ የሚመጣውን መልክት በመጫን መገምገም የሚችል
ይሆናል፡፡

5. ለመገምገም ሲሞከር የግምገማ ሂደቱ ሲስተም ላይ በተገምጋሚው ትይዩ፡-

— Planned የሚል ከሆነ ለመገምገም ዝግጁ ስለሆነ የእስራስ ምልክቱን በመጫን ግምገማውን
መጀመር ይቻላል፡፡
— Pending Approver ካለ የግምገማ ሂደቱ ወደ አጽዳቂው ተልኳል ማለት ነው፡፡
— Transferred to Appraisee የሚል ከሆነ የግምገማ ሂደቱ ተገምጋሚው ጋር ስለሆነ
የግዴታ ተገምጋሚው የግምገማ ሂደቱን መመለስ ይኖርበታል ማለት ነው፡፡
— Ongoing with Main Appraiser ከሆነ ግምገማ ሂደቱ በዋናው ገምጋሚ መጀመሩን
ያሳያል በመሆኑም update በማድረግ የሂደቱን ወደ ሚመለከተው መላክ ይኖርበታል፡፡

2
ሐምሌ 15 ቀን 2014 ዓ.ም

6. ሲስተም ላይ በሚገመግሙበት ጊዜ በመጀመሪያው ገጽ የሚገኘው የካምፖኒ እሴቶች /Core


Value/ እና የንኪኪ ነጥብ /Touch Point/ ሲሆኑ ለእያንዳንዱ ከ1 እስከ 5 ነጥብ ብቻ ነው
መሙላት የሚቻለው፡፡ ከ5 በላይ እንዲሁም ክፍልፋይ ቁጥር መስጠት አይቻልም፡፡

7. በሁለተኛ ገጽ መጀመሪያ ላይ የሚገኘው የዋና ክፍል/የዞን እና ሪጅን ኦርሬሽናል ዳሬክተር ውጤት


ተኮር/ Division or Respective Operation Directors BSc/ ውጤት ሲሆን እሱም መሞላት
ያለበት በሰው ኃይል ዋና ክፍል ብቻ ነው፡፡ በመቀጠልም አራቱ የውጤት ተኮር እይታዎች /BSc
Perspective/ ሠራተኛው/ዋ እንዳገኘው/ችው የውጤት ተኮር /BSc/ ውጤት የሚሞላ ይሆናል፡፡

8. ተገምጋሚው employee self-service በመግባት የግምገማ ውጤቱን ወደ ገምጋሚው


መመለስ የሚችሉ ይሆናል፡፡

3
ሐምሌ 15 ቀን 2014 ዓ.ም

9. እንዲጸድቅ ወደ አጽዳቂ የተላከ የግምገማ ሂደት አጽዳቂዎች በራሳቸው ERP worklist ላይ


ማስታወቂያውን/Notifation/ ካላገኙት Full Listን በመጫን የሚያገኙት ይሆናል፡፡

10. አጽዳቂው በግምገማው ውጤት ያልተስማማ ከሆነ እና ውጤቱ እንዲስተካከል ወደ ገምጋሚው


ለመመለስ Reject በሚያረጉበት ጊዜ የግምገማ ሂደቱን ስለሚያስተጓጉል ወደ ገምጋሚው
ለመመለስ Return for correction የሚለውን በመጫን ለገምጋሚው መመለስ አለባቸው፡፡

11. ገምጋሚዎች የግምገማ ውጤቱን ወደ ተገምጋሚው ከመላኩ በፊት ሁሉንም ነጥቦች በትክክል
መሞላቱን ማረጋገጥ አለበት፡፡ እንዲሁም ተገምጋሚዎችም ውጤቱ በሚላክበት ወቅት
አጠቃላይ ውጤቱን ከማየት ባሻገር እያንዳንዱ ነጥቦች በትክክል መሞላታቸውን ማረጋገጥ
አለባቸው፡፡
12. እያንዳንዱ የስራ መሪ በግምገማ ወቅት በስሩ ያሉት የሰራተኞች የግል BSc ከዲቪዝን ወይም
ከዞን እና ሪጅን ኦፕሬሽን ዳይሪክተር BSc ውጤት የሚቃረን መሆን የለበትም፡፡

2. የግለሰብ ውጤት ተኮር (Individual BSc) እይታዎች

የግለሰብ ውጤት ተኮር /Individual BSc/ 4 እይታዎች አሉት፦

1. ፋይናንስ እይታ /Finance Perspective/ ትርፋማነት፣ የኢኮኖሚ እሴት መጨመር፣ የሽያጭ


ዕድገት፣ የገንዘብ ፍሰት፣ የካምፓኒውን ሀብት አጠቃቀም እና ሌሎች የፋናንስ ነክ መለኪያዎች፡፡
2. የደንበኛ ተኮር /Customer Perspective/ የደንበኛ እርካታ፣ አያያዝ፣ የገበያ ውስጥ ያለ ድርሻ

4
ሐምሌ 15 ቀን 2014 ዓ.ም

እና ሌሎች ከደንበኛ ጋር የተያያዙ መለኪያዎች፡፡


3. የውስጥ ሂደት /Internal Process Perspective/ የስራ ላይ ግቦች ፣ የጥራት፣ ብዛት፣ በቆይታ
ጊዜ እና የውጤታማነት የሚለኩ መለኪያዎች።
4. መማር እና እድገት /Learning and Growth/ ዕውቀትን ለሌላ ማካፈል፣ ስልጠና፣ ችሎታ እና
የግል አቅም ማጎልበቻ እቅድ (Personal Development Plan-PDP) ተነሳሽነት ናቸው፡፡

3. የሥራ አፈፃፀም ውጤት

1. ለማኔጅመንት የሥራ መደብ የግለሰብ ውጤት ተኮር (Individual BSc) እይታዎች ለእያንዳንዱ
እይታ እንደየዲፖርትመንቱ የተለያየ ክብደት ሲኖረው አጠቃላይ ውጤቱ ከ55% ይሆናል፡፡
በተጨማሪም የካምፖኒ እሴቶች እና የንኪኪ ነጥቦች /touch points/ 30% ውጤቱን ሲይዙ
ቀሪው 15% የዲቪዥን ወይም የዞን እና የሪጅን ውጤትን የሚወስዱ ይሆናል፡፡
2. ለሠራተኛ የሥራ መደብ የግለሰብ ውጤት ተኮር (Individual BSc) እይታዎች በተመሳሳይ እንደ
ማኔጅመንት የሥራ መደብ እንደየዲፖርትመንቱ የተለያየ ክብደት ሲኖራቸው አጠቃላይ ድምር
ውጤቱ ከ70% ሲሆን የካምፖኒ እሴቶች እና የንኪኪ ነጥቦች /touch points/ 15% ውጤቱን
ሲይዙ ቀሪው 15% የዲቪዥን ወይም የዞን እና የሪጅን ውጤትን የሚወስዱ ይሆናል፡፡
3. በግምገማ ወቅት የሚታዩ የውጤት አሰጥጥ ስህተቶች፤
በግምገማ ሂደት ጊዜ የሚታዩት የተለመዱ የምዘና ውጤት አሰጣጥ ስህተቶች ከዚህ በታች
ተዘርዝረዋል፤
3.1 መካከለኛ የስራ አፈፃፀም የመስጠት ስህተት፣
• ሠራተኞች አፈፃፀማቸው ከፍተኛ ወይም ዝቅተኛ ቢሆንም ጽንፎችን ለማስወገድ በመሞከር እና
ተጠያቂነትን ለመሸሽ ሁሉንም ሠራተኞች በመካከለኛ የአፈፃፀም መደብ ውስጥ መሰብሰብ
ሲሆን ይህ አሰራር ጥረት የሚያደርጉ ሠራተኞችን የስራ ተነሳሽነት ሊቀንስ ይችላል፤
3.2 በመለሳለስ የሚፈጠር ስህተት፣
• ሠራተኞች በሰሩት ሥራ ከመገምገም ይልቅ ላለመጋጨት ወይም በሠራተኞች ለመወደድ
ሲባል ለሁሉም ከፍተኛ የሥራ አፈፃፀም መስጠት፤
3.3 በጥሩ ስራ ብቻ የመመዘን ተጽዕኖ፣
• በግምገማ ስርዓቱ ውስጥ ከተለመዱ ስህተቶች አንዱ ሲሆን ሠራተኛን አንድ ጊዜ በተሰራ ጥሩ
ስራ ወይም በአንድ ነገር ላይ የተደረገ ጥሩ ነገርን መነሻ ብቻ በማድረግ ሁሉንም ሥራዎች
መመዘን፤
3.4 በመጥፎ ስራ ብቻ የመመዘን ተጽዕኖ፣

5
ሐምሌ 15 ቀን 2014 ዓ.ም

• ሰራተኛን በተሠራ አንድ መጥፎ ስራ ወይም መጥፎ ፀባይ ብቻ ሁሉንም ሥራዎች የመመዘን
ችግር፤
3.5 ባለፈ ሥራ የመገምገም ስህተት፣
• ሠራተኞችን አሁን እየሰሩ ባሉት ስራ ሳይሆን በፊት በሰሩት መጥፎም ይሁን ጥሩ ስራን
መሠረት በማድረግ መገምገም፤
3.6 በአድሎዓዊነት የሚደረግ የግምገማ ስህተት፣
• ሠራተኞችን በሰሩት ስራ ከመገምገም ይልቅ በዘር፣ በብሔር፣ በጾታ፣በሃይማኖት፣ በዕድሜ፣
ወዘተ ባሉ አመለካከቶች የሚደረግ ግምገማ፤
3.7 ቅርብ ጊዜ በተሠራ ሥራ ብቻ የመገምገም ስህተት፤
• ዓመቱን ሙሉ የተሰሩ ሥራዎችን በመተው ሠራተኛን በቅርብ ጊዜ በተሰራ ጥሩም ይሁን
መጥፎ ሥራ ብቻ መገምገም ነው፡፡ ይህ የሚሆነው ገምጋሚው በመጨረሻዎቹ ጥቂት የስራ
ሳምንታት ላይ ያላቸውን አፈፃፀም ላይ ሲመሰርት ነው፡፡

4. በስራ አፈፃፀም ምዘና ወቅት የሚከሰቱ ስህተቶችን እንዴት ማስወገድ ይቻላል፡፡

በግምገማ ወቅት በውጤት አሰጣጥ ላይ የሚከሰቱ ስህተቶች የምዘና ውጤቱን የተሳሳተ ቁመና
እንዲኖረው እና ትክክለኛውን ውጤት እንዳይታይ ካምፓኒው ክፍተቶችን አይቶ ማስተካከያ
እንዳያደርግ የሚያደረጉ ምክንያቶች ናቸው። ስለሆነም "ገምጋሚዎች ከአዎንታዊ ሆነ አሉታዊ
ሁኔታዎች እና እውነታውን ከሚያዛባ ከማንኛውም ነገር መጠንቀቅ አለባቸው። ከላይ የተዘረዘሩትን
የሰራተኛ የሥራ አፈጻጸም ግምገማ መርሆዎች እና የምዘና ስህተቶችን ከግንዛቤ በማስገባት
በተቀመጠው ቀነ ገደብ የሥራ አፈጻጸም ግምገማውን እንድታጠናቅቁ እናሳስባለን፡፡

25- 27/07/2022 28/07-01/08/2022 02-07/08/2022 05-09/08/2022 10-12/08/2022


NAAZ CAAZ EAAZ SAAZ SWAAZ

ISecD ER CExQMD CEO Office Finance


NID WAAZ CER SD LD

CNR SSWR NEER CWR EER

CSD WR SER NNWR NWR

MD FND SWR NER SR


IAD MMD HRD SWWR WWR

SPPMD PSD NOSC FFD ISD


TExA SCD WLD CD

6
ሐምሌ 15 ቀን 2014 ዓ.ም

ማሳሰቢያ
ማንኛውን ተገምጋሚም ሆነ ገምጋሚም እንዲሁም አጽዳቂ የሲስተም መጨናነቅ እንዳይከሰት ከላይ
በተቀመጠው መረኃ ግብር መሠረት ብቻ የግምገማ ሂደቱን ማከናወን አለበት፡፡ ከተሰጠው ጊዜ ሰሌዳ ውጭ
የሚከናወን የሥራ አፈጻጸም ግምገማ ሲስተሙ የማይቀበል ሲሆን እንደ ከዚህ በፊቱም በማኑዋል የማንቀበል
በመሆኑ፡፡ ከዚህ ጋር ተያይዞ ለሚፈጠረው ማንኛውም ክፍተት ገምጋሚውና ተገምጋሚው ኃላፊነት የሚወስዱ
ይሆናል፡፡

የሰው ኃይል ዲቪዥን

You might also like