You are on page 1of 4

Poimen Ministry Email: poimenministry516@gmail.

com

ትምህርት 4- የማግባት ጥቅሞች

የትምህርቱ ዓላማዎች
በትምህርቱ መጨረሻ ላይ ተማሪዎች፡
❖ ማግባት ለተጋቢዎች እንዲሁም ለኅብረተሰቡ የሚሰጠውን ጥቅሞች
ያብራራሉ፡፡
❖ እነዚህን የጋብቻ ጥቅሞችን እውን ለማድረግ ወይም በሕይወት ለመለማመድ
ምን ማድረግ እንደሚገባቸው ይገልጻሉ፡፡

በዚህ ክፍል ውስጥ ሰዎች በማግባት የሚያገኙአቸውን ጥቅሞችን አብረን እንመለከታለን፡፡


እነዚህ አጠቃላይ የጋብቻ ጥቅሞች መሆናቸውን እንጂ ያገባ ሰው ሁሉ እነዚህን ነገሮች በሙላት
ይለማመዳል ማለት ላይሆን ይችላል፡፡ እነዚህ እምቅ ጥቅሞች እውን ለማድረግ እያንዳንዱ ተጋቢ
ማድረግ የሚገባውን ማድረግ ይጠበቅበታል፡፡
ሰዎች ጋብቻ
ለአንዳንዶች ጋብቻ የዕድሜ ልክ እስር ቤት ነው፡፡ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ጋብቻን በአዎንታዊ መልክ
በመምሥረታቸው ምን
ከመመልከት ይልቅ አሉታዊ እይታዎች እየበዙ መጥተዋል፡፡ ከወጣቶች ጋር ባለኝ አገልግሎት
ምን ጥቅሞችን ሊያገኙ
ስለጋብቻ ብዙ አሉታዊ አሳቦችን ሰምቻለሁ፡፡
ይችላሉ
ማግባት ለብቻ ከመኖር በብዙ ነገር የተሻለ ነው፡፡ አንዳንድ ትዳርን የመሠረቱ ሰዎች ሰብዓዊ
ድርሻቸውን ተገቢ በሆነ መንገድ ባለመወጣታቸው የትዳር ሕይወታቸው ባይጥማቸውም ጋብቻ
መልካም ነው፡፡ የአንዳንድ ትዳሮች ስኬታማ አለመሆን ጋብቻ መልካምነቱ አይቀርም፡፡ የጋብቻ
ግንኙነት መልካምና የሚጣፍጥ እንዲሆን ባልና ሚስት የበኩላቸውን ሚና መጫወት
አለባቸው፡፡ ይህ ሳይሆን ሲቀር መልካም ሆኖ የተሰጠን ጋብቻ መልካምነቱ በግንኙነት ውስጥ
እውን ላይሆን ይችላል፡፡

ጋብቻ የሕይወት አጋር ያስገኛል

እግዚአብሔር ለአዳም ሔዋንን የፈጠረበት አንዱ ዓላማ ለአዳም ረዳት (የሕይወት ዘመን ጓደኛ)
እንድትሆነው ነው (ዘፍ.2፡18)፡፡ እውነተኛ ጓደኛ ማግኘት ለሕይወት እርካታ አስፈላጊ ነው፡፡ ‹‹ሰው
ብቻውን ይሆን ዘነድ መልካም አይደለም›› የሚለው ሐሳብ የወዳጅነትን አስፈላጊነት
ያመለክታል፡፡ ሰው ማሕበራዊ ፍጡር በመሆኑ ወዳጅን ይፈልጋል፡፡ ሚሉ የሆነ ወዳጅ ደግሞ
የሚገኘው በጋብቻ ውስጥ ነው፡፡ ከፍጥረት በኋላ እግዚአብሔር የፈጠራቸውን ነገሮች ሁሉ
ከትዳር ጓደኛ ጋር
ሲገመግም መልካም እንደሆነ ተናገረ፡፡ ወደ አዳም ሲመጣ ግን ብቻውን በመሆኑ መልካም
የሚኖረው ወዳጅነት እንዳልሆነ ተናገረ፡፡ ስለዚህ ሴትን መፍጠር አስፈለገ፡፡ ያገባ ሰው ከአባት፣ ከእናት፣ ከወንድም፣
ከሌሎች ሰዎች ጋር ካለን ከእህትና ከማንኛውም ሰው ይልቅ የምትቀርበውን የሕይወት ዘመን ወዳጅ ያገኛል፡፡ ሴትም
ወዳጅነት በምን ይለያል እንዲሁ፡፡ ወዳጅነታቸው ሁለንተናዊ ሕይወትን ሁሉ የሚነካ ነው፡፡

እንደ አዳም አንድ ሰው በጥሩ አካባቢ ወይም ቤት ውስጥ ቢኖር፣ ለምግብ፣ ለመጠጥ፣
ለመዝናኛ የሚሆኑ ነገሮች ሁሉ ቢኖረው፣ ደስ የሚሰኝነበት ሥራ ሁሉ ቢኖረው፣ እቤት ውስጥ
የሚያጫውቱት ውሾችና ድመቶች ቢኖረው፣ ከወላጆቹ ወይም ወንድም እህቶቹ ጋር ጥሩ

Page 1 of 4
Poimen Ministry Email: poimenministry516@gmail.com

ግንኙነት ቢኖረው የትዳር ጓደኛን አይተኩም፡፡ ሁሉ ነገር ቢኖር በትዳር ጓደኛ የሚሞላ የሕይወት
ክፍል ግን ባዶ ሆኖ ይኖራል፡፡

ባልና ሚስት መሆን ሁለት ሆነው በሕይወታቸውና በአካባቢያቸው የሚያጋጥሙአቸውን


ተግዳሮቶች ማሸነፍ ይችላሉ፡፡ አንድ ከመሆን ሁለት መሆን ይሻላል (መክ.4፡9-12)፡፡ ባልና ሚስት
ጥንካሬዎቻቸውን አንድ ላይ ይደምራሉ፡፡ አንድ ላይ ሲደመሩ በግል ይኖሩ ከነበሩበት ሕይወት
በላይ ይኖራሉ፡፡ እንዲሁም የአንዱ ድካም በሌላው ጥንካሬ ይሸፈናል፡፡ ስለዚህ ሕይወትን በተሻለ
ሁኔታ ለመኖር ዕድልን ይሰጣል፡፡

ወሲብን በሙላት ለመለማመድ ይረዳል

የባልና ሚስት አንድ ሥጋ መሆን ከትዳር ውጭ ከሚደረገው የተለየ ኅብረት ነው፡፡ በጋብቻ
ከጋብቻ ውጭ እና ውስጥ ወሲብ ወዳጅነትን ይገልጻል፡፡ በሁለቱ መካከል ያለው መልካም ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ
በጋብቻ ውስጥ የሚያሳድግ ነው፡፡ ከጋብቻ ውጭ የሚፈጸም ወሲብ በአብዛኛው የወሲብ ፍላጎትን ለማርካት
በሚደረግ የወሲብ ነው፡፡ በትዳር ውስጥ ወሲብ ሲፈጸም የፍቅር ሙላትን ይገልጻል፡፡ ፍቅር ለማግኘት ሳይሆን
ግንኙነት መካከል ያለው
ያለውን ፍቅር ለማጎልበት ያገለግላል፡፡ ከትዳር ውጭ የሚፈጸም ወሲብ ግን ሲደጋገም ያሰለቻል፣
ከዚያም ወደ መለያየት ያመራል፡፡ የወሲብ ግንኙነት ትክክለኛው ቦታ ጋብቻ ውስጥ ነው፡፡
ልዩነት ምንድነው

ጋብቻ ልጆችን ለመውለድና ለማሳደግ ምቹ ሥፍራ ነው

በመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት መሠረት ልጆች መወለድ ያለባቸው ከባልና ከሚስት ነው፡፡ ጋብቻ
አንዱ ዓላማው ዘር ለመተካት ነው፡፡ ልጆች ደግሞ መወለድ ብቻ ሳይሆን ማደግም አለባቸው፡፡
የልጆች ሁለንተናዊ ዕድገት መልካም እንዲሆን ደግሞ አባትና እናት አብረው ሆነው ማሳደግ
ይኖርባቸዋል፡፡ ሁለቱም አንድ ላይ ሲሆኑ የልጆችን ሁለንተናዊ ፍላጎት የማሟላት ዕድላቸው ከፍ
ይላል፡፡

ሳያገቡ ልጆችን ወልደው በአብዛኛው በጋብቻ ውስጥ ተወልደው በአባትና እናት የሚያድጉ ልጆች ተገቢውን እንክብካቤ
በሚያሳድጉና ተጋብተው ስለሚያገኙ ጤናማ አካላዊ፣ አእምሮአዊ፣ መንፈሳዊና ሥነልቦናዊ ሕይወት ይኖራቸዋል፡፡
ልጆችን ወልደው አብረው የወላጆቻቸውን የቅርብ ድጋፍና ክትትል ስለሚያገኙ በትምህርታቸውና በተሠማሩባቸው የሥራ
በሚያሳድጉ መካከል ምን መስኮች ፍሬያማ የመሆን ዕድላቸው ይሰፋል፡፡ እነዚህ ልጆች ስለቤተሰብ ሕይወት ከወላጆቻቸው
ልዩነት ይኖራል መልካም ምሳሌነትን ስለሚያገኙ ወደፊት ሕይወታቸውን በዚያ መሥመር የመቃኘት ሁኔታን
ያሳያሉ፡፡

ጋብቻ ለመልካም ጤንነትም አስተዋጽኦ አለው

ጋብቻ ለጤንነት አስተዋጽኦ እንዳለው ተጋቢዎች ላያውቁ ይችላሉ፡፡ ይህ በብዙ መንገድ ሊከሰት
ይችላል፡፡ ባለትዳሮች በአብዛኛው የሚመገቡት ከቤታቸው ነው፡፡ ይህ ደግሞ የሚመገቡትን
በጥንቃቄ በመምረጥ እንዲመገቡ ይረዳቸዋል፡፡ የተመጣጠነ እንዲሁም እንደ ዕድሜያቸው
ሁኔታ መመገብ ይችላሉ፡፡ በምግብ ዝግጅት ጊዜም ንጽሕናው የተጠበቀ እንዲሆን ማድረግ
ማግባት እንዴት ለሰዎች
ወይም መከታተል ይችላሉ፡፡ ከምግብ ዐይነት እንዲሁም ከንጽሕና ጉድለት የሚመጣውን በሽታ
ጤንነት አስተዋጽኦ
መከላከል ይችላሉ፡፡
ሊያደርግ ይችላል

ጋብቻ የመሠረቱ ሰዎች ለበሽታ ሊያጋልጡአቸው ከሚችሉ ነገሮች ራሳቸውን ይከላከላሉ፡፡ ባልና
ሚስት በወሲብ ግንኙነት ለእርስ በርሳቸው ታማኞች ከሆኑ በወሲብ ግንኙነት ከሚመጡ ተላላፊ

Page 2 of 4
Poimen Ministry Email: poimenministry516@gmail.com

በሽታዎችን ራሳቸውን ይጠብቃሉ፡፡ ልቅ ወሲብ የሚፈጽሙ ያላገቡ ሰዎች ግን ለአባለዘር


በሽታዎች የመጋለጥ ዕድላቸው ከፍተኛ ነው፡፡

በጋብቻ ግንኙነት ውስጥ ያሉ ሰዎች በሕይወታቸው ጫናዎች ወይም ውጥረቶች


ሲያጋጥሙአቸው ጭንቀታቸውን ለትዳር ጓደኛቸው ያካፍላሉ፡፡ በዚህም እፎይታን ያገኛሉ፡፡
ውጥረታቸውን/ ጭንቀታቸውን የሚጋራቸው ሰው አላቸው፡፡ እውነተኛ ወዳጅ ችግርን
የሚካፈል ሰው ነው፡፡ ውጥረትና ጭንቀትን መቀነስ ደግሞ ለጤና አስተዋጽኦው የጎላ ነው፡፡

አንዳንድ ጥናቶች በተገቢው ጊዜ ትዳር የመሠረቱ ሰዎች ረጅም ዕድሜ እንደሚኖሩ ይናገራሉ፡፡
ባለትዳሮች በሽታን የመቋቋም አቅማቸው ከፍ ይላል፡፡ በቤተሰብ ውስጥ ያለው መተሳሰብና
መደጋገፍም ጉልበት ይሆናቸዋል፡፡

ጋብቻ ደስታን ይጨምራል


በጋብቻ ግንኙነት ባልና ሚስት ተግባብተው የሚኖሩ ሲሆን ደስታቸው ይጨምራል፡፡ የሕይወት
ዘመን ጓደኛ መከራን የሚካፈል እና ደስታን የሚያባዛ ሰው ነው፡፡

ጋብቻ ሀብትን ለማፍራት ያግዛል

በዚህ ዓለም እጅግ ባለጠጋ የሆኑ ሰዎች ባለትዳሮች ናቸው፡፡ በአገራችንም ሁኔታ ስንመለከት
በእናንተ እይታ ማግባት
ከፍተኛ ሀብት ያላቸው ሰዎች ባለትዳሮች ናቸው፡፡ ባለትዳሮች ሀብት እንዲያፈሩ አስተዋጽኦ
የሚያደርጉ በርካታ ምክንያቶች ይኖራሉ፡፡ ከእነዚህም ጥቂቶቹን ለመጥቀስ ያህል፡
ሀብት ለማፍራት ያግዛል
• ዋስትና ያለውን ሥራ ለመያዝ ጥረት ያደርጋሉ፤ ሥራቸውን እንዲሁ በቀላሉ
ወይስ ሰው በኢኮኖሚ
አይለቁም፣ ሥራቸውን በትጋት ይሠራሉ፣
እንዳያድግ ያደርጋል፡
• ባለትዳሮች ከሚያገኙት ገቢ የተወሰነውን ገንዘብ ይቆጥባሉ፣ ይህ ደግሞ ቀስ በቀስ
ተወያዩበት፡፡
እያደገ በመሄድ ትልቅ ሀብት ይሆናል፤ ይህን ገንዘብ በሌላ ትርፋማ ሥራ ላይ ያውላሉ፣
• የሚያዋጣቸውን ትርፋማ የሥራ መስክ በጥንቃቄ ይመርጣሉ፣
• ሁለት ሆነው ይሠራሉ፣ ወጪዎቻቸውን ይቀንሳሉ

በጋራ ንብረት ለማፍራትና ያፈሩትንም በመቆጠብ ለመጠቀም ትዳር አስፈላጊ ነው፡፡ ብዙ


ንብረት የሚያፈሩና ለጡረታ ዘመናቸውም የሚያስፈልጋቸውን ሀብት የሚያከማቹ እንዲሁም
ለልጆቻቸው ብዙ ሀብት የሚያወርሱት በትዳር ውስጥ የቆዩ ባልና ሚስት ናቸው፡፡ ስለዚህ
በተገቢው ጊዜ ማግኘት ሀብት ለማፍራትም የበኩሉን ሚና ይጫወታል፡፡

በአጠቃላይ ለብቻ ከመኖር ቤተሰብ መሥርቶ መኖር በርካታ ጥቅሞች አሉት፡፡ በቤተሰብ ውስጥ
በቀጣይነት የሚኖር የስሜት ድጋፍ፣ መብትና ግዴታዎችን መፈጸም ይኖራል፡፡ አንድ ጊዜ
የሕይወት አጋራችንን ከመረጥን ወይም ልጆች ከወለድን ሁልጊዜ ፍለጋ አንሄድም፡፡ እነዚህ
የቤሰብ አባላት ደግሞ የራሳቸውን ሚና ያከናውናሉ፡፡ የትዳር ጓደኛ፣ ልጅ፣ ወላጅ ፣ ወይም
ወንድም ወይም እህታችን የቤተሰባችን አባላት በመሆናቸው ሚናቸውን በሕይወት ዘመናቸው
ሁሉ በቤተሰብ ተግባራት ውስጥ እንደሚሳተፉ እንጠብቃለን። መስጠትና መቀበል የሚለው
መርሕ ተግባራዊ ይደረጋል፡፡ የቤተሰብ አባላቶቻቸውን በሆነ ሁኔታ ውስጥ ብንገኝ
እንደሚደርሱልን ተስፋ እናደርጋለን፡፡

Page 3 of 4
Poimen Ministry Email: poimenministry516@gmail.com

ጥያቄዎች

❖ ……………………………………………..……….

❖ ………………………………………………………

Page 4 of 4

You might also like