Professional Documents
Culture Documents
2012 Education
2012 Education
Contents
ክፍል አንድ............................................................................................................................................................................................................................... 2
የ 2011 ዓ.ም የትምህርት ዋና ዋና እቅዶች አፈፃፀም የሁኔታ ግምገማ............................................................................................................................. 2
ክፍል ሁለት፡- የካፒታል ፕሮጀክት ሥራዎች አፈፃፀም.................................................................................................................................................... 3
ክፍል ሶስት፡- በእቅድ አፈፃፀም ወቅት ያጋጠሙ ችግሮችና የተወሰዱ መፍትሄዎች...........................................................................................……..5
ክፍል 2....................................................................................................................................................................................................................................... 6
2.1. የ 2012 ዓ.ም አጠቃላይ ዕቅድ መነሻዎች፣ታሳቢዎችና የትኩረት አቅጣጫዎች........................................................................................... 6
2.4. የመነሻ ዕቅዱ አስፈላጊነት/Importancy/..........................................................................................................................................6
2.5. የዕቅዱ አጠቃላይ ግብ/Goal/.........................................................................................................................................................6
2.6. የዕቅዱ ዋና ዋና አላማዎች/Aims/....................................................................................................................................................6
2.7. የዕቅዱ ዝርዝር አላማዎች...............................................................................................................................................................7
2.8. ዕቅዱን ለመፈፀም የምንከተላቸዉ መርሆች.......................................................................................................................................7
2.9. የእቅዱ ተፈፃሚነት ወሰን( Scope of the plan)................................................................................................................................7
2.10. የትምህርት ዘመኑ ዕቅድ ዋና ዋና ይዘቶች......................................................................................................................................7
2.11. ዕቅዱ መነሻ ያደረጋቸው ታሳቢዎች..............................................................................................................................................8
2.12. የበጀት ምንጭ..........................................................................................................................................................................8
ክፍል 3....................................................................................................................................................................................................................................... 9
3. የ 2012 ዓ.ም የአጠቃላይ ትምህርት ዕቅድ................................................................................................................................................................ 9
3.1.1. የትምህርት አመራር አሰራርና አደረጃጀት ማሻሻያ መርሃ-ግብር.................................................................................................................... 9
3.1.2. የመምህራን ልማት መርሃ-ግብር......................................................................................................................................................................... 10
3.1.3. የትምህርት ቤት ማሻሻያ መርሃ-ግብር................................................................................................................................................................ 13
3.1.4. የስነ-ዜጋና ስነ-ምግባር ትምህርት መርሃ-ግብር..................................................................................................................................... 19
3.1.5. የስርዓተ-ትምሀርት ማሻሻያ መርሃ-ግብር........................................................................................................................................................... 21
3.1.6. የኢንፎርሜሽን ኮምዩኒኬሽን ቴክኖሎጅ አገልግሎትን የማስፋፋት መርሃ-ግብር................................................................23
3.2. አብይ ተግባር......................................................................................................................................................................................................... 24
3.2.1. የትምህርት ሽፋንን ማሳደግ 25%....................................................................................................................................................................... 24
3.2.2. ንዑስ ተግባር፡-የሲቪል ሰርቪስ ማሻሻያ ፕሮግራም (5%)........................................................................................................................... 26
ክፍል 4..................................................................................................................................................................................................................................... 28
4. ዕቅዱን ለመፈፀም ያሉ መልካም አጋጣሚዎች፣ስጋቶች፣መፍትሄዎችና የምንከተላቸው አቅጣጫዎች፣...................................................28
4.1. ዕቅዱን ለመፈፀም የሚኖሩ መልካም አጋጣሚዎች............................................................................................................................28
4.2 ሊያጋጥሙ የሚችሉ ችግሮች/ስጋቶች..................................................................................................................................................28
4.3 የመፍትሄ አቅጣጫዎች.......................................................................................................................................................................28
4.4 ዕቅዱን ለመፈፀም የምንከተላቸው አቅጣጫዎች......................................................................................................................................29
ክፍል 5...................................................................................................................................................................................................................................... 31
5. የዕቅዱ አተገባበር፣የግንኙነትና የሪፖርት አደራረግ ስርዓት..................................................................................................................................... 31
5.1 በትምህርት ቤት ደረጃ ፡-.....................................................................................................................................................................31
5.2 በጉድኝት ደረጃ ፡-..............................................................................................................................................................................31
ለዕቅድ ተግባራዊነትና ስኬት በጋራ እንረባረብ!!Page 1
የመተማ ወረዳ ትም/ጽ/ቤት የ 2012 ዓ.ም ዓመታዊ የጽ/ቤቱ የስራ ዕቅድ
ክፍል አንድ
የ 2011 ዓ.ም የትምህርት ዋና ዋና እቅዶች አፈፃፀም የሁኔታ ግምገማ
የተማሪዎች የትምህርት ቅበላ አፈፃፀም
የቅድመ መደበኛ ት/ት ፕሮግራም አፈፃፀምን በተመለከተ በ 4 የአፀደ ህፃናት ተቋማት ወ-375 ሴ-370 ድ-745 ህፃናትን ለማስተማር ታቅዶ ወ-458
ሴ-418 ድ-876 ለማስማር የተቻለ ሲሆን በ 82 ት/ቤቶች ደግሞ 8209 ኦ ክፍል (O ክፍል) ህፃናትን ለማከናወን ታቅዶ 964 ያህሉን ህፃናት ብቻ
ማስማር ተችሏል፡፡
በአንደኛ ደረጃ የትም/ት ፕሮግራም (1-8 ኛ) ወ-16,672 ሴ-16,498 ድ-33,170 ተማሪወችን ለማስተማር ታቅዶ እስከአመቱ መጨረሻ ወ-13,103 ሴ-
7,499 ድ-20,602 ተማሪወችን ማዝለቅ የተቻለ ሲሆን ወ-4,501 ሴ-2,097 ድ-6,598 ተማሪወች ግን አቋርጠዋል፡፡ ከባለፈዉ ዓመት (96%) አፈፃፀም
አንፃር ሲታይ የዚህ አመት አፈፃፀም በጣም የቀነሰ ሲሆን ለዚህ ዋነኛ ምክንያቱ በአመቱ ተፈጥሮ በነበረዉ ወቅታዊ ችግር ከነበሩን 87 1 ኛ ደረጃ
ት/ቤቶች ዉስጥ ከ 15 ያላነሱ ት/ቤቶች በመዘጋታቸዉ እና በተከፈቱም ቢሆን የተማሪወች አገር መልቀቅ ዋነኞቹ ናቸዉ፡፡
በሁለተኛ ደረጃ የት/ት ፕሮግራም (9-12 ኛ) ወ-1228 ሴ-1397 ድ-2625 ለማስተማር ታቅዶ እስከአመቱ መጨረሻ ወ-503 ሴ-509 ድ-1012
ተማሪወችን ብቻ ማዝለቅ የተቻለ ሲሆን ወ-288 ሴ-224 ድ-512 ተማሪወች ደግሞ አቋርጠዋል፡፡ በወረዳችን 2 ሁለተኛና 1 መሰናዶ ት/ቤቶች
ይገኛሉ፡፡
በተቀናጀ ተግባር ተኮር የጎልማሶች የት/ት ፕሮግራም በ 135 ጣቢያወች 5899 ጎልማሶችን ለማሳተፍ ታቅዶ በ 111 ጣቢያወች 675 ጎልማሶችን
ማስተማር ተችሏል፡፡ በዚህ ዘርፍ ያለዉ ዉጤት በጣም ዝቅ ያለ ሆኖ ተገኝቷል፡፡ ስልጠናዉን ሲያመቻቹ የነበሩ አመቻቾች ብዛት ወ-20 ሴ-85 ድ-
105 ናቸዉ፡፡
በ 4 ልዩ ፍላጎት ዩኒቶች 48 ተማሪዎችን ለማስተማር ታቅዶ ክንዉኑ 29 ነዉ፡፡ በአካቶ ደግሞ 98 ተማሪወችን ማስተማር ተችለዋል፡፡
ስለሆነም በዚህ ዓመት ባለዉ ወቅታዊ ችግር ምክንያት አፈፃፀማችን የቀነሰ ሲሆን አራቱን ፕሮግራሞችን አስተሳስሮ ከመስራት አንፃርም
ክፍተቶች አሉ፡፡
በዓመቱ በተለያዩ ምክንያት የለቀቁ መምህራን ብዛት ወ-15 ሴ-16 ድ-31 ናቸዉ፡፡
የመምህራንና የትምህርት ተቋማት አመራሮች የሙያ ፈቃድ አሰጣጥና እድሣት ተግባራት አፈፃፀም
ለመመዘን ማመልከቻ ያስገቡ መምህራን ክላስተር ወ፡ 47 ሴ፡ 18 ድ፡ 45 ሲሆኑ ከነዚህ ውስጥ የተመዘኑት ወ- 1 ሴ-0 ድ- 1 ነው፡፡
በሊኔየር ተመርቀው ለመመዘን ፍቃደኛ ሁነው ማመልከቻ ያስገቡ መምህራን ብዛት ወ- 19 ሴ- 17 ድ- 36 የተመዘኑት ደግሞ ወ 1
ሴ 0 ድ 1
ር/መምህር ለመመዘን የተመዘገቡ ወ 2 ሴ 4 ድ 6 የተመዘኑ የሉም
ሱፐር ቫይዘር ለመመዘን የተመዘገቡ 2 ኛ ደርጃ ወ -- 1 ሴ - ድ --1 አንደኛ ደረጃ ወ- 1 ሴ- 0 ድ-1 ሲሆኑ የተመዘነ ወ 1 ሴ- 0
ድ- 1 2 ኛ ደረጃ የተመዘነ የለም በጥቅሉ መመዘን የሚገባው ሊኔርና ክላስተር 62 ሲሆኑ ከነዚህ ውስጥ ዞኑ የሰጠን ኮታ ሊኔር 8
ክላስተር 7 አጠቃላይ 15 ኮታ ቢሰጠንም የተመዘኑት 2 ብቻ ናቸው፡፡ ከተመዘኑት 3 ተመዛኞች መምህራን ውስጥ 2 ቱ የማለፊያ ውጤት
አስመዝግበዋል፡፡
ር/መምህራንና ሱፕርቨይዘር መመዘን ከሚገባቸው 6 አመራሮች 1 ሱፕርቫይዘር ብቻ መመዘን ችሏል፡፡ በተጨማሪም የሁለተኛ ደረጃ
መምህራን ለምዘና ብቁ ናቸው ያልናችው 62 መምህራን ለዞን በስም ዝርዘር የላክን ሲሆን ከነዚህ ውስጥ ለምዘና የቀረበ የለም፡፡
በተጨማሪም በ 2010 ዓ.ም 43 መ/ራን የሙያ ብቃት ምዘና በኮሌጂ ደረጃ ወስደዉ 70% እና ከዚያ በላይ ያስመዘገቡ 6 ብቁ የሆኑትን መ/ራን መረጃ
ተለይቶ ለዞን ተልኳል፡፡
በ 2011 ዓ.ም በጂኩፕ II ጠቅላላ የተመደበልን ብር 1,606,909 ከተመደበው 1,437,464 ብር ለት/ቤቶች ተደራሽ ተደርጓል፡፡ ቀሪው 169,445 ብር
በወቅታዊ ምክንያት ያልወሰዱ ት/ቤቶችን በጀት ወንበር እንዲሰራ ተድርጓል፡፡
ለ 2 ኛዉ ሩብ ዓመት ስራ ማስፈፀሚያ የሚሆን 220,508.47 ብር መድቧል፡፡ በዚህ በጀት 162178.87 ብር ስልጠና የወሰዱ የቅድመ መደበኛ
አመቻቾች ወ- 6 ሴ- 17 ድ- 23 ፣ ፆታዊ ጥቃትን በተመለከተ በላድርሻ አካለት ወ- 28 ሴ- 1 ድ- 29 ፣ የፆታዊ ትንኮሳ ፎካል ወ- 5 ሴ- 3 ድ- 8 ፣ የጎልማሳ
አመቻቾች ወ- 1 ሴ- 6 ድ- 7 ጠ/ድምር ወ- 40 ሴ- 27 ድ- 67 ሰልጣኝ ሰልጥኗል፡፡ በተጨማሪም በ 58,329.60 ሁለት ሞንቶሰሪ ግዥ በመፈጸም ለሁለት
ት/ቤት ተሰራጭቷል እንዲሁም 10,000 ብር ለክትትልና ድጋፍ ማዋል ተችሏል፡፡ በአጠቃላይ በየሩብ ዓመቱ የተመደቡልን በጀት ለታለመለት ዓላማ
በማዋል የበጀት አጠቃቀም ሪፖርት 100% ለክልል ፋይናስ መላክ ችለናል፡፡
የ 3 ኛው ሩብ ዓመት ስራ ማስፈፀሚያ የሚሆን 135,491.66 ብር መድቧል፡፡ በዚህ በጀት ስልጠና የወሰዱ የቅድመ መደበኛ አመቻቾች ወ - 1 ሴ- 8 ድ-
9 ፣ ፆታዊ ጥቃትን በተመለከተ በላድርሻ አካለት ር/መ/ር ወ- 19 ሴ- ድ- 19 ፣ የፆታዊ ትንኮሳ ፎካል ወ- ሴ- 8 ድ- 8 ፣ መ/ር ወ- 21 ሴ- 8 ድ- 29
ጠ/ድምር ወ- 41 ሴ- 24 ድ- 65 ሰልጣኝ ሰልጥኗል፡፡
የ 4 ኛው ሩብ ዓመት ስራ ማስፈፀሚያ የሚሆን 99,642.64 ብር መድቧል፡፡ ከዚህ በጀት 88790 ስልጠና የወሰዱ የቅድመ መደበኛ አመቻቾች ወ- 3 ሴ-
14 ድ- 17 እና የፆታዊ ጥቃትና ትንኮሳ ፎካል ወ- 6 ሴ- 3 ድ- 9 ፣ሲሆኑ ቀሪ ተግባራት በመከናወን ላይ ናቸዉ፡፡
ከአልማ በተገኘ 1‚192‚556.84 ብር በጀት በአንድ (በአጋም ዉሃ ) አንደኛ ደረጃ ት/ቤት 1 ብሎክ 4 መማሪያ ክፍል ለመገንባት በጥቃቅንና አነስተኛ
ለተደራጁ ኢንተርፕራይዞች ዉል ተሰጥቶ ግንባታው የተጀመረና መሰረቱን የጨረሱ ቢሆኑም በአሁኑ ወቅት ስራው በወቅታዊ ጉዳይ ሙሉ በሙሉ
ቆሟል፡፡ የግንባታ አፈፃፀሙ አሁን ላይ 30% ነው፡፡
በአቸራ 1 ኛ ደረጃ ደረጃ ት/ቤት በ 677‚000 ብር በ 2009 ዓ.ም የተጀመረዉ 1 ብሎክ 4 መማሪያ ክፍል ግንባታ አፈፃፀሙ አሁን ላይ 40% እንደደረሰ
ከዚህ ቀደም ሪፐርት ማድረጋችን ይተወቃል፡፡ ሆኖም ግን አሁንም የአፈፃፀም ደረጃው ባለበት ነው፡፡ ምክንያቱም በነበረው ወቅታዊ ችግር መልስ
መስጠት አልተቻለም፡፡
በበጀት ዓመቱ 27‚000 ህዝብ በማሳተፍ በዓመቱ 5,974,406 ብር በህ/ሰብ ተሳትፎ ለማከናወን ታቅዶ ወ-12,415 ሴ-5,206 ድ-17,621 ሰዎችን በማሳተፍ
በገንዘብ 496,831 ፤ በጉልበት 614,623 እና በቁሳቁስ 341,331 በማሳተፍ በአጠቃላይ ብር 1,452,785 ብር (24.5%) ማድረስ ተችሏል፡፡ ህዝቡን በትም/ት
ፍይናንስ የበኩሉን አስተዋፆኦ እንዲያደርግ የሚደርገዉ ስራ ዝቅ ማለት በወቅታዊ ምክንያት የተፈጠረው አለመረጋጋት መሆኑን ለመረዳት ተችሏል፡፡
ክፍል 2
2.1. የ 2012 ዓ.ም አጠቃላይ ዕቅድ መነሻዎች፣ታሳቢዎችና የትኩረት አቅጣጫዎች
2.1 የመተማ ወረዳ ትም/ጽ/ቤት
2.2. ራዕይ፡-
ትምህርትና ስልጠናን በስፋት በማዳረስ ስብዕናው የተሟላ የስራ ባህልን ያሳደገ ብቁ ዜጋ ተፈጥሮ ማየት
2.3. ተልዕኮ፡-
የትምርት ሴክተር የልማት ሰራዊት በሁሉም የት/ተቋማት በመፍጠር በተቀናጀ እንቅስቃሴ የአጠቃላይ ትምህርት ጥራት
ፓኬጁን በውጤታማነት ማስፈፀም፣
ክፍል 3
3. የ 2012 ዓ.ም የአጠቃላይ ትምህርት ዕቅድ
ተግባር 1፡- በተደራጀ የትምህርት የልማት ሰራዊት የተማሪዎች ውጤት በሁሉም የትምህርት ዓይነት ሁሉም
ተማሪዎች 50℅ እና ከዚያ በላይ ማስመዝገብ፣
ተግባር 2፡- በሂደት ደረጃ የ 1 ለ 5 ዕቅድ ተዘጋጅቶ በሂደቱ አባላት የጋራ በማድረግ ወደ ተግባር ማስገባት፣
ተግባር 3፡-ሁሉም ትምህርት ቤቶች የተደራጀ የትምህርት ልማት ሰራዊትን ያካተተ ዕቅድ አዘጋጅተው ወደ ስራ
እንዲገቡ ማድረግ፣
ተግባር 4፡-በሁሉም ትምህርት ቤቶች የተማሪና የመምህራን የ 1 ለ 5 ና የልማት ቡድን አደረጃጀት ማደራጀት፤፣
ተግባር 5፡- ወመህ እና ቀትስቦ ት/ቤቶችን በባለቤትነት መንፈስ እንዲመሩ ግንዛቤ በመፍጠር፣ በተግባርና በየሃላፊነታቸው
የአቅም ማጎልበቻ አጫጭር ስልጠና በመስጠት በየወሩ እየተገናኙ ት/ቤቶችን እንዲመሩ ማድረግ፡፡
3.1.1. የትምህርት አመራር አሰራርና አደረጃጀት ማሻሻያ መርሃ-ግብር
ግብ አንድ ፡-
በት/ቤቶች አጠቃላይ የት/ት ጥራት ማስጠበቂያ ኘሮግራምና የምዕተ ዓመቱን ግብ አቀናጅቶ
የሚፈፅም የትምህርት አመራር ሀይል በየደረጃው መፍጠር፡፡
ተግባር 1፡- አዲስ ለተቀጠሩ የጉድኝት ሱፐርቫይዘሮች ውጤት ተኮር ውል መስጠትና እነሱም በተዋረድ ለር/መ/ራን
እንዲሰጡና የአፈፃፀም ውጤትንም መሙላት፣
ተግባር 2 ፡- የሚመጡ አዳዲስ መመሪያዎችን ወደ ት/ቤቶች በማውረድ ለሱፐርቫይዘሮች፣
ግብ ሁለት ፡-
ት/ቤቶች በብቁና ለደረጃው በሚመጥኑ፣ በአግባቡ በተመረጡና በሰለጠኑ ር/መ/ራንና
ሱፐርቫይዘሮች እንዲሁም በሌሎች ልዩ ልዩ አደረጃጀቶች እንዲመሩ ማድረግ፡፡
ተግባር 1፡- አንደኛ ደረጃ 1 ር/መ/ር እና 15 መ/ራን፤ ሁለተኛ ደረጃ 2 ር/መ/ር እና 10 መ/ራን እና 9 ድጋፍ ሰጭ ሰራተኞችን
ቅጥር እንዲፈፀም በማድረግ ት/ቤቶች የተፈለገውን ግብ እንዲመቱ ማድረግ፣
ተግባር 2፡- የረዥም ጊዜ የስራ ላይ ስልጠና ያልጀመሩትን ር/መ/ራንና ሱፐርቫይዘሮች ከዞን በሚሰጠው ኮታ መሰረት የክረምት
ትምህርት በማስጀመር ለሚመሩት ት/ቤት ደረጃቸውን ብቁ ማድረግ፣
ተግባር 3፡- ሁሉም ሱፐርቫይዘሮችና ር/መ/ራን ከዞን በሚመጣ በወረዳ ደረጃ በሚዘጋጅ የአጭር ጊዜ ልዩ ልዩ ስልጠና እንዲያገኙ
ማድረግ፣
3.1.2.
የመምህራን ልማት መርሃ-ግብር
ግብ ሶስት፡-
በክልሉ መ/ራን ትም/ኮሌጆች የሚሰጠውን የመጀመሪያ ደረጃ መምህራን ቅድመ ስራ
ለማሰልጠን በሚሰጠን ኮታ መሰረት መፈፀም፡፡
ተግባር 1፡- የዞኑ የት/ት ጉዳዮች ክትትል ዋና የስራ ሂደት በሚልከው የእጩ ሰልጣኝ መ/ራን ምልመላና መረጣ ኘሮግራም
በሚሰጠው ኮታ መሰረት ማስታወቂያ በማውጣት ጥሪ ተደርጐ በሚዘጋጀው ስታንዳርድ መሰረት በመመዝገብ
ለሚመለከታቸው አካላት መላክ፣
ተግባር 2፡- በኮሌጆች የቃልና የፅሁፍ ፈተና አልፈው የተሰጠውን ክልል አቀፍ መረጣ ላለፉ ሰልጣኞች እንዲገለፁና እንዲሁም
የተመደቡበትን ኮሌጅና የመመዝገቢያ ቀን ለሰልጣኞች በወቅቱ ማሳወቅ፣
ግብ አራት፡-
በወረዳው ከሚገኙ ት/ቤቶች በማስተማር ላይ ከተሰማሩት መ/ራን በት/ት ደረጃ ማሻሻያ ስልጠና ኘሮግራሞች
በማሳተፍ ተገቢውን አካዳሚያዊ እውቀት፣ሙያዊ ስነ-ምግባርና አወንታዊ አመለካከት ያላቸው መ/ራንን
ማፍራት፡፡
ተግባር 1፡- በመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤቶች በማስተማር ላይ ያሉ የዲፕሎማ መ/ራን ከዞን ትም/መምሪያ በሚሰጠን ኮታ መሰረት
በመመልመል በዲኘሎማ ደረጃ በሊኔየርና በክላስተር እንዲሁም በዲግሪ ኘሮግራም እንዲከታተሉ ማድረግ፣
ግብ አምስት፡-
መ/ራን በተግባር መሳሪያዎች ቋት የሙያ ማሻሻያ ኘሮግራም ስልጠና ሂደት በማሳተፍ አካዳሚያዊ
እውቀታቸውንና ሙያዊ ስነ-ምግባራቸውን በማሻሻል ሀላፊነታቸውን የሚወጡና በራሳቸው እንዲተማመኑ
ማስቻል፡፡
ተግባር 1፡- በኘሮግራሙ አተገባበር ላይ የነበሩ ችገሮችን በመፍታት መ/ራን የተግባር መሳሪያ ሙያ ማሻሻያ ኘሮግራም
ተግባራት በት/ቤትና በጉድኝት ማዕከላት በአግባቡ ፈፅመው የተማሪዎችን ውጤት የማሻሻል ስራ ተጠናክሮ እንዲቀጥል
ማድረግ፣
ተግባር 2፡- አዲስ ለሚቀጠሩና ለነባር መ/ራን በተመደቡበት ት/ቤት የሙያ ትውውቅ ኮርስና
ተግባር 3፡- አዲስ ለሚከፈቱ ት/ቤቶች ለተግባር መሳሪያዎች ቋት ስልጠና አጋዥ የሚሆኑ የስልጠና ቁሳቁሶችን ለት/ቤቶች
አባዝቶ እንዲዳረሱ ማድረግ፣
ተግባር 4፡- ስልጠናው በአግባቡ እንዲካሔድ ክትትልና ሙያዊ ድጋፍ ተደርጐ ጠንካራና ደካማ
እንዲረጋገጡ ማድረግ፣
ተግባር 6፡- የኘሮግራሙ የሩብ አመት፣የ 6 ወርና ዓመታዊ የመረጃ አያያዝና ሪፖርት
ግብ ስድስት፡-
በወረዳው ውስጥ ያሉ መ/ራን የስልጠና ፍላጐታቸውንና ያሉባቸው የአቅም ክፍተት ተለይቶ ወቅታዊ አጫጭር
ስልጠና በመሰጠት ተጨማሪ አቅም መፍጠር፡፡
ተግባር 1፡- የስልጠና ፍላጐት ከልዩ ልዩ መረጃዎች መ/ራን ካለባቸው የአቅም ክፍተት
ተግባር 3፡- ስልጠናውን ለመስጠት ሞጁሎችን ማዘጋጀትና አጋዥ የሆኑ ግብዓቶችን ማሟላት፣
ተግባር 4፡- ስልጠናው ያመጣውን ለውጥ በመገምገም ደካማና ጠንካራ ጎኖችን በመለየት
ግብ ሰባት፡-
ተግባር 1፡- የመርሱ ዝውውርን ለመስራት ወቅቱን ጠብቆ የዝውውር መሙያ ቅፅ ለት/ቤቶች
ተግባር 2፡- ተሞልቶ የሚመጣውን የዝውውር መረጃ ማጠናከርና ወደ ዞን የሚላከውን በወቅቱ መላክ፣
ተግባር 3፡- ዝውውሩን በወቅቱ፣ግልፅ በሆነ መንገድና አግባብ ያለው ቅሬታ በማያስነሳ ሁኔታ መስራት፣
ተግባር 4፡- የትምህርት ደረጃቸውን የሚያሻሽሉና የቆይታ ጊዜያቸውን አሟልተው የደረጃ እድገት
ተግባር 6፡- መ/ራን፣ር/መ/ራንና ሱፐርቫዘሮች በሚሰጡት አስተያየት መሰረት የተገልጋይ ፍላጎትን እንዲሻሻል ማድረግ፣
ተግባር 7፡- አግባብነት ያላቸውን ቅሬታዎች በመቀበልና በመመርመር አፋጣኝ ምላሽ መስጠት፣
ግብ ስምንት
በሁሉም ደረጃ የሚገኙ መለስተኛና በመምህር ደረጃ ያሉ መምህራንን መመዘን፡፡
ተግባር 1፡- በሁሉም ደረጃ ያሉ፣በመለስተኛ ደረጃና በመምህር ደረጃ የሚገኙ መምህራንን መለየት፣
ተግባር 2፡- ለተለዩት መምህራን ምዘና የሚሰጥ መዛኝ መለየትና ለስልጠና መላክ፣
ተግባር 3፡- ለተለዩት የተመዛኝ መምህራን የሚያበቃ የምዘና መሳሪያዎችንና የበጀት ዝግጅት ማከናወን፣
ተግባር 5፡- በስታንዳርዱ መሠረት ምዘናውን ላለፉ መምህራን የሙያ ፈቃድ መስጠት፣የሚጠበቅ ውጤት ተማሪዎች
ብቃታቸው በተረጋገጠ መምህራን ይማራሉ፣መምህራን ለስራቸው ይተጋሉ፣ለሙያቸው ክብር ይሰጣሉ፣
ግብ ዘጠኝ የይዘትና የፔዳጎጅ ምዘና ለወሰዱ ጀማሪ መምህራን የተግባር ምዘና ይሰጣል፡፡
ተግባር 1፡-
የይዘትና የተግባር ምዘና የተመዘኑ መምህራንን የስምሪት መረጃ ማደራጀት፣
ተግባር 2፡- ለተመዛኞች በቂ ሊሆን የሚችል መዛኝ መለየትና ስልጠና እንዲወስዱ ማድረግ፣
ተግባር 3፡- ለተመዛኞች የተዘጋጀውን ሩብሪክስ ለተመዛኞች ቀድሞ ስልጠና እንዲወስዱ ማድረግ፣
ተግባር 6፡- በተቀመጠው ስታንዳርድ መሠረት ውጤት ላመጡ መምህራን የሙያ ፈቃድ እንዲያገኙ ማድረግ፣የሚጠበቅ
ውጤት፡-ተማሪዎች ብቃታቸው በተረጋገጠ መምህራን ይማራሉ፣መምህራን ለስራቸው ይተጋሉ ለሙያቸው ክብር ይሰጣሉ፣
ተግባር 1 ፡- በወረዳው ውስጥ በአጠቃላይ ትምህርት በተለይም በትምህርት ቤት መሻሻል ላይ ባለድርሻ ለሆኑት አካላት
ተካታታይ ስልጠና መስጠት፣
ተግባር 2 ፡- ከወረዳ እስከ ት/ቤት ድረስ አዲስ ተመድበው፣ተቀጥረው ወይም ተዛውረው ለሚመጡ
ር/መ/ራን፣ሱ/ቫይዘሮችንና መምህራን የፅንስ ሀሳብና ተግባር ተኮር ስልጠና መስጠት፣
ግብ አስራ አንድ
የወረዳው ት/ቤቶች የመማር-ማስተማር ሂደቱንና የሁሉንም ተማሪዎች ውጤት እያሻሻሉ የሚያስችል
ዓመታዊ የትምህርት ቤት መሻሻል ዕቅድን በአሳታፊነት ማዘጋጀትና ተግባራዊ ማድረግ፡፡
ተግባር 1 ፡- ሁሉም የወረዳው ት/ቤቶች በዕቅድ ዘመኑ ያጠናቀቁትን ዓመታዊ የት/ቤት መሻሻል እቅድ
አዘገጃጀት፣አተገባበርንና ውጤት ግምገማ በማድረግ የቀጣዩን የሦስተኛ ዓመት ዕቅድ በአሳታፊነት
አዘጋጅተው ማፅደቅ፣
ተግባር 2 ፡- የት/ቤት ማሻሻያ መርሀ-ግብር ሂደት በመሆኑ የትምህርት ተቋማት ካለፉት አንድ ዓመት የዕቅድ ዝግጅት
ሂደት፣አተገባበር፣ከተገኝው የግብ ስኬት ግምገማ፣ውጤትና ለግምገማው ከተፈጠረው የግንዛቤ ለውጥ
መነሻ በማድረግ የስትራቴጅክ እቅድ ዋና ዋና ግቦችና ተግባራትን ክለሳ ማድረግ፣
2..1 በወረዳና በቀበሌ የተካሄዱትን መድረኮችና በአገር አቀፍ ደረጃ በታቀደው የእድገትና ትራንስፎርሜሽን
ዕቅድ የ 2012 ዓ.ም ዓመታዊ እቅድን መከለስ
2..3 በእቅድ ትውውቅ ላይ የተገኙ ባለድርሻ አካላትን በየደረጃው በቃለ-ጉባኤ አስደግፎ መያዝ
2..4 በእቅድ ትውውቅ በባለድርሻ አካላት የተነሱ ዋናዋና ጉዳዮችንና እቅዱን ለመተግበር የሚያጋጥሙ
ችግሮችና ለችግሮች የተሰጠ መፍትሄ የተፈጠረ መነሳሳትን ቀምሮ መያዝ
ተግባር 3 ፡- የት/ቤት ዓመታዊ የት/ቤት መሻሻል ዕቅድ በአራቱ አብይ ርዕስ ጉዳዮች በአስራ ሁለት ንዑሳን ርዕስ
ጉዳዮችና ሁሉንም ስታንዳርዶች መሰረት በማድረግና የግምገማ ትግበራውንና ሪፖርቱም ይህን አግባብ
የተከተለ ማድረግ፣
3.1 በት/ቤት ማሻሻያ አብይ ርዕስ ጉዳዮችንና ስታንዳርዶችን መምህራን በንቃትና በውጤታማነት ስለመሳተፋቸው
በየወሩ ግምገማ ማካሄድ
ተግባር 4 ፡- ዓመታዊ ዕቅድን ከአዲስ ት/ቤት ማሻሻያ ዕቅድ ግብ ጋር በማያያዝ ማለትም የመምህራንን ግብ
ከተማሪዎች ግብ ጋር ማስተሳሰር፣
ተግባር 5 ፡-በተጣለው የተማሪዎች ማሻሻያ ግብ ላይ የት/ቤቱ መምህራን፣ሰራተኞች፣ተማሪዎች፣ልዩ ልዩ አደረጃጀቶችና
ወላጆች በልዩ ልዩ መድረኮች ላይ ግልፅነት እንዲኖራቸው ማድረግና በአተገባበሩ ላይ የራሳቸውን ሚና
እንዲጫወቱ ማድረግ፣
5.1 በተጣለው የተማሪዎች ግብ ላይ የት/ቤቱ ማህበረሰብና ወላጆች፣እንዲሁም ልዩ ልዩ አደረጃጀቶች ግልጽ
እንዲሆኑ ማድረግ
ተግባር 7፡- በት/ቤት ደረጃ በየወሩ፣በጉድኝት ደረጃ 3 (በየሩብ አመቱ) በወረዳ ደረጃ 2 ጊዜ በትምህርት ሴሚስተር
መጨረሻ ላይ በትምህርት ቤቱ ማሻሻያ ውጤት ላይ ያለበትን ሁኔታ አጀንዳ አድርጎ መወያየት፣
7.1 በየደረጃው በተቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ መከናወኑን ማረጋገጥና በየጊዜው በግብረ-መልስ ማሳወቅ
ግብ አስራሁለት
ተግባር 1 ፡- 50/90 የት/ቤት ኮሌጅ ግንኙነት ውስጥ በሆነ መንገድ በት/ቤት ማሻሻያ መርሀ- ግብር እንዲሆን ማድረግ፣
1.1 የት/ቤት ማሻሻያ መርሀ-ግብር በውጤታማነት ለመፈፀም ተገቢውን ክትትልና ድጋፍ ማድረግ
ተግባር 2 ፡- በት/ቤት ውስጥ ያሉ መምህራንና ሰራተኞች በዘመኑ በት/ቤት ማሻሻል ኮሚቴ በአባልነት ይህንም ከአራቱ አብይ
ርዕስ ጉዳዮች በአንደኛ ንቁ ተሳትፎ የማድረግ ተቋማዊ ባህል መፍጠር፣
ተግባር 3 ፡- በወረዳችን ያለፉት ዓመታት የትምህርት ቅበላ የሶስት ዓመት ት/ቤት ማሻሻል የውጤት ጥናት በመስራት
ለማሻሻያ ግብዓትነት መጠቀም፣
ተግባር 4 ፡-የት/ቤት ማሻሻያ ዕቅድ ውጤትን ማደረጃጀትና በተገቢው መንገድ ጥቅም ላይ ማዋል፣
ተግባር 1 ፡- ሁሉም የወረዳው ት/ቤቶች ህብረተሰቡ ወንድ 21000 ሴት 6000 ሰዎችን በማሳተፍ የተለያዩ ግብዓቶችን
ለሟሟላት በገንዘብ 2,820,290 ፣በጉልበት 1,742,146 እና በቁሳቁስ 1,411,970 ድምር 5,974,406 የተቋሙን
የመደበኛና የካፒታል በጀት 80% እንዲሸፍን ማድረግ፣
ተግባር 2 ፡- ወላጆች በዓመት ውስጥ በየ 2 ወሩ ለ 5 ጊዜ በመገኘት በት/ቤት ዕቅድ አፈፃፀምና በተማሪዎች ውጤት ላይ
እንዲወያዩና የድርሻቸውን እንዲወጡ ማድረግ፣ ሴት ልጆችን ወደ ት /ቤት የሚልኩና ዉጤታማ የሚያደርጉ
ወላጆችን ማበረታታት፤
ተግባር 3 ፡- ከቀበሌ እስከ ወረዳ ያሉት የህዝብ ም/ቤቶችና የወረዳው አስተዳደር አካላት በዕቅድ ዘመኑ በፓኬጅ አተገባበር
ሪፖርት ቀርቦለት እንዲመክርና የድርሻውን እንዲወጣ ማድረግ፣
ተግባር 3 ፡- ከቀበሌ እስከ ወረዳ ያሉ ህዝባዊ ማህበራትና አደረጃጀቶች በየደረጃው ባሉ ተቋማት በፓኬጅ አተገባበር ሪፖርት
እንዲያመጡና ሚናቸውን እንዲጫወቱ ማድረግ፣
ግብ አስራ አራት በክፍል ውስጥ መማር-ማስተማር ሂደቱን በአዲስ የትምህርት ቤት ማሻሻል ማዕቀፍ
መሰረት እያሻሻሉ በመሄድ የተማሪዎችን ውጤት ማሻሻል፡፡
ተግባር 1 ፡- በወረዳው ውስጥ ያሉት ሁሉም የመጀመሪያ ሳይክል /1-4/ የክፍል ውስጥ አደረጃጀት ከነባር ዘዴ ወጥተው
አዲሱን ተማሪ ተኮር አማራጮች በሙሉ እንዲተገበሩ ማድረግ ፣
1.1 የተማሪ ተኮር የክፍል ውስጥ አደረጃጄቶችን በሁሉም የመጀመሪያ ሳይክል /ከ 1-4/ ት/ቤቶች ተግባራዊ ማድረግ፣
ተግባር 2 ፡- በወረዳው የሚገኙ የአንደኛ ክፍል አዲስ ገቢ ተማሪዎችን በአዲስ የክላስተር ክረምት ባጠናቀቁ መምህራን
እንዲማሩ ማድረግ፣
2.1 የክላስተር ክረምት ስልጠና የጀመሩ መምህራንን ለይቶ መያዝ
2፣2 ስልጠና ያጠናቀቁ የክለስተር ሰልጣኝ መምህራንን ከ 1 ኛ ክፍል ጀምሮ ወደላይ መመደብ
ተግባር 3፡- በወረዳው የሚገኙ የ 1 ኛ ክፍል ሴክሽኖች ውስጥ የክላስተር ቋንቋ ስልጠና የወሰዱ መምህራን እንዲመደቡ
በማድረግ በመንፈቅ ዓመቱ መጨረሻ የተማሪዎች የቋንቋ ክህሎት የሚጠብቀው ፕሮፋይል ላይ
እንዲደርስ ማድረግ፣
3.1 በመንፈቅ ዓመቱ መጨረሻ የተማሪዎች የቋንቋ ከህሎት የሚጠበቀው ፕሮፋይል ላይ እንዲደርስ
ከመምህራን ጋር ስምምነት ላይ ማድረስ፣
ተግባር 4 ፡-ተማሪዎች በየ ሩብ ዓመቱ መጨረሻ በተጣለው ግብ የተከናወኑ ተግባራትንና
በተገኘው ውጤት ላይ ውይይት ማድረግ፣
ተግባር 5 ፡- ተማሪዎች በዓመቱ ውስጥ በሙሉቀን የሚማሩት 1,075,30 ሰዓት በፈረቃ የሚማሩበት
ደግሞ 820 ሰዓታት ትምህርት ያገኙ መሆኑን ማረጋገጥ በበቂ ምክንያት ለሚቀሩ መምህራን የተተኪ መምህራንን
ስርዓት ዘርግቶ ተግባራዊ ማድርግ፣
5.1 ከት/ቤቱ ማህብረሰብ ጋር በመነጋገርና በመተማመን የሙሉቀን ትምህርት መጀመር
5.2 የክፍለ ጊዜ ብክነት እንዳይፈጠር የተተኪ መምህራንን ስርዓት መዘርጋትና ተግባራዊ ማድረግ፣
ተግባር 6፡- በአጠቃላይ በወረዳው ውስጥ የሚገኙ ሙሉ ሳይክል ትምህርት ቤቶች የቤተ-ሙከራ አጠቃቀም በአግባቡ
ተቃኝቶና ተጠንቶ የሳይንስ ትምህርት ቤቶች የቤተ-ሙከራ አጠቃቀም በአግባቡ ተቃኝቶና ተጠንቶ
የሳይንስ ትምህርት በተሸለ መልኩ ለመስጠት የሚያስችል ስልት ቀይሶ ተግባራዊ ማድረግ
6.2 የሳይንስ ቤተ-ሙከራ / በሶስቱም ሳይንሶች / በሁሉም ሙሉ ሳይክል ት/ቤቶች በአግባቡ የሚጠቀሙበትን ስልት ቀይሶ
መንቀሳቀስ፣
ተግባር 7፡- ለመጀመሪያ ደረጃ 2 ኛ ሳይክል የቤተ-ሙከራ ስታንዳርድና አደረጃጀት ማንዋል በአሳታፊነት
አግባብ በማዘጋጀት ተገቢውን ትውውቅ በማድረግ ትምህርት ቤቶችን ማደራጀት፣
ተግባር 8፡- በወረዳው በሁሉም የመጀመሪያ ደረጃ መጀመሪያ ሳይክልና ንባብን የሚያሻሽሉ ስነ- ዘዴዎችን በመጠቀም ሁሉም
ህፃናት እንዲያነቡ ማድረግ፣
8.1 በትምህርት ዘመኑ መጀመሪያ ላይ ማንበብና መፃፍ ባለመቻላቸው ድጋፍ ለማድረግ የተለዩ ተማሪዎችን መረጃ
በአግባቡ መያዝና ለውጡን እየተከታተሉ ሪፖርት ማድረግ
ተግባር 9፡- በሁሉም የትምህርት ደረጃዎች የሳይንስና የሂሳብ ትምህርት አሰጣጥን በማሻሻል የተማሪውን ውጤት
ማሻሻል፣
9.1 የሳይንስና የሂሳብ ትምህርት አሰጣጥን ለማሻሻልና የተማሪዎችን ውጤት ለማሳደግ ከመምህራን ጋር በመወያየትና
ስምምነት በመድረስ እንዲሁም ልዩ ልዩ እቅድ አዘጋጅቶ ተግባራዊ ማድረግ
ተግባር 10፡- የመማር-ማስተማሩን ስራ ለማጠናከር የሚያስችል ጥናታዊ ፅሁፎችንና የፅንስ ሀሳብ ፅሁፎችን
እያንዳንዱን የትምህርት አይነት ሊያጠናከር በሚችል መልኩ ዝግጅት ማድረግና ማጠንከር
1.1 የመማር-ማስተማርን ስራ ለማጠናከር ጥናታዊና የፅንሰ ሀሳብ ፅሁፎችን ማዘጋጀትና ተግባራዊ ማድረግ
1.2 በጥናታዊ ፅሁፎች ውይይት /ሲፖዚየም / በት/ቤት ደረጃ፣በጉድኝትና በወረዳ ደረጃ ማካሄድ
1.3 በተማሪዎች ውጤትና የሳይንስ ሂሳብ ትምህርት ላይ የተገኙ ተጨባጭ ለውጦች
ተግባር 11 ፡- የሳይንስ መምህራን መድረክ በትምህርት ቤትና በወረዳ ደረጃ ማዘጋጄትና እንዲዘጋጁ
በማድረግ ተማሪዎች በሳይንስ ትምህርት ውጤታማ የሚሆኑበትን አግባብ መሞከር፣
ግብ አስራ አምስት
በየደረጃው ለሚገኙ የትምህርት ተቋማት በአዲሱ ክልላዊ ስታንዳርድ ወሳኝ የሆኑ ግብዓቶችን በማሟላት
ምቹና ማራኪ በማድረግ የትምህርት ጥራትን በማስጠበቅ የተማሪዎችን ውጤት ማሻሻል፡፡
ተግባር 1፡- ሁሉም ተቋማት የመማር-ማስተማር ዘዴዎችንና የተማሪዎችን አያያዝ እንዲሁም የትምህርት
ቤቶች አካባቢ ተማሪዎችን የሚማርኩ፣የሚያበረታቱና ከስጋት ነፃ እንዲሆኑ ማድረግ፣
ተግባር 3 ፡- ተጨማሪ ክፍሎችን በመገንባት የተማሪ ክፍል ጥምርታን 1-4 1፡50 ና 5-8 1 ለ 45 ማድረስ፣
ተግባር 6 ፡- ትምህርት ቤቶች ቤተ-ሙከራ (ከ 5—8)፣አይሲቲ ማዕከል(ከ 9—10)ና በ 10 (ከ 5—8) ት/ቤቶች ፣የመጠጥ
ውሀ፣የሁለቱም ፆታ መፀዳጃ ቤት፣የትም/ማበልፀጊያ ማዕከላት(በሁሉም)፣የስፖርት ሜዳዎች(በሁሉም) 100% ያላቸው
እንዲሆኑ ማድረግ
ተግባር 7፡- ሁሉም ተማሪዎች 100% ደረጃቸውን በጠበቁ የተማሪዎች መቀመጫ ወንበርና ዴስክ መቀመጥና መማር
መቻላቸውን ማረጋገጥ፣
ግብ አስራ ስድስት
ደረጃቸውን የጠበቁ የትም/ት ተቋማት ግንባታን ጥያቄ ከየቀበሌዎች በቀረበው
መሠረት ተለይቶ አመች ሁኔታ መፍጠር፡፡
ተግባር 1፡- የትም/ት ተቋማትን ለመገንባት የተዘጋጀውን የህንፃ ዲዛይንና የስራ ዝርዝር በባለሙያዎች ቡድን እንዲታይና
እንዲረጋገጥ ክትትል ማድረግ፣
ተግባር 2፡- የተሰጠውን ማረጋገጫ መሠረት በማድረግ በስራ ሂደቱ የበላይነት በማፅደቅ የግዥ ዘዴውን በመለየት ግዥ
እንዲፈፀም የጨረታውን ሰነድና ማስታወቂያ በማዘጋጀት የጨረታ ማስታወቂያ ማውጣት፣የጨረታ ሰነድ አባዝቶ ለመሸጥ
በሰነዱ ለሚቀርቡ ጥያቄዎች ማብራሪያ ለመስጠት ማመቻቸት፣(ከወረዳው ገ/ፕ/ልማት ትብብር ጽ/ቤት ጋር)
ተግባር 3፡- የጨረታ ሰነድ ማዘጋጀትና ማሸግ፣እንዲሁም በወቅቱ በተያዘለት ፕሮግራም ሳጥኑን በመክፈት የተጫራጨቾችን
ዋጋ በንባብ ማሰማትና የጨረታ ማስከበሪያ በመረከብ የጨረታ መክፈቻ ቃለ-ጉባኤ በማዘጋጀት የቴክኒክ ግምገማ
ማከናወን፣የጨረታውን ውጤት ማሳወቅና ሰነድ በማዘጋጀት እንዲፈፀም የውል ማስከበሪያ በመረከብ ስራን የመፈፀም ብቃት
መፍጠር፣(ከወረዳው ገ/ፕ/ልማት ትብብር ጽ/ቤት ጋር)
ተግባር 5፡- የሚገነቡት ተቋማት ስርጭት ፍትሀዊ እንዲሆኑ የተቋማቱ ግንባታ በወቅቱ ተጠናቆ ለተፈለገው የትም/ት መስጫ
አገልግሎት እንዲውል ማድረግ፣
ግብ አስራ ስምንት
በወረዳችን በሚገኙ ሁሉም ት/ቤቶች ደረጃቸውንና ጥራታቸውን የጠበቁ የት/ት መሳሪያዎችን ማቅረብ
ተግባር 1፡- የት/ት መሳሪያዎችን አቅርቦት አስመልክቶ ረቂቅ ስታንዳርድና የመረጃ መሰብሰቢያ
ተግባር 2፡- በተዘጋጀው ረቂቅ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት በማድረግ የተፈጥሮ ሳይንስ፣
ተግባር 3፡- በማንኛውም መንገድ ማለትም በግዥ ወይም በዕርዳታ የሚገኙ የት/ት
ግብ አስራ ዘጠኝ
በወረዳችን ባሉ የት/ት ተቋማት ወቅቱን የጠበቀ የት/ት መሳሪያዎች ጥገናና ዕድሳት ጥያቄ ወቅታዊ
ምላሽ እንዲያገኝ ማድረግ፡፡
ተግባር 2፡- በየት/ት ተቋማቱ የት/ት መሳሪያዎችን ጥገና ፍላጎት በማሰባሰብ በተቋሙ መጠገን
የሚችልና የማይችለውን በመለየት በትም/ት ልማት ሰራዊት /ልማት ቡድን/ በማስጠገን አገልግሎት ላይ እንዲውል ማስቻል፣
ግብ ሀያ
የክፍል፣የጉድኝነትና የወረዳ እንዲሁም የሀገር አቀፍ ፈተናዎች ትንተና ለተማሪዎች ውጤት ማሻሻያነት
በግብዓትነት የመጠቀም የአሰራር ስርዓት ተጠናክሮ ተግባር ላይ እንዲውል ማድረግ፡፡
ተግባር 1፡- በትምህርት ዘመኑ ከመጀመሪያ ደረጃ 1 ኛ ሳይክልና 1 ኛ ደረጃ 2 ኛ ሳይክል እና ከዚያም ዝቅተኛ
የተማሪዎች ውጤት ማሻሻያ በ 10 ጥሬ ማርክ መነሻ ማሻሻል፣
ተግባር 2፡- ሁሉም ት/ቤቶች በ 2011 ዓ.ም የፈተና ውጤታቸው በመተንተን ችግር ያሉባቸው የትምህርት
አይነቶች ልዩ ዕቅድ አዘጋጅቶ መተግበር መምህራን የሚያስተምሩት የትምህርት አይነት ዓመታዊ
የተማሪዎችን ውጤት ማሻሻል ግብ አቅደው እንዲንቀሳቀሱ ማድረግ፣
ተግባር 3፡- ት/ቤቶች በትምህርት መሻሻያ ዕቅዳቸው መሰረት የ 2011 ዓ.ም የተማሪዎች ውጤት ትንተና በመነሳት ዓመታዊ የተማሪዎች ውጤት የማሻሻያ ግብ
ላይ የጋራ ስምምነት ማድረግ፣በግቡ ስኬትና መንስኤዎች ላይ ወርሀዊ ውይይት ማድረግ፣
3.1 የፈተና ውጤቶችን በመተንተንና ችግር ላለባቸው የት/አይነቶች ልዩ እቅድ አዘጋጅቶ ተግባራዊ ማድረግ
3.2 ት/ቤቱ በጣለው የተማሪዎች ውጤት ማሻሻያ ግብ ለተማሪዎችንም ማወያየትና ተማሪዎችም የራሳቸውን ግብ እንዲጥሉ ማድረግ
3.3 ስለውጤቱ መሻሻል ተከታታይነት ያለው ወርሀዊ ውይይት ማካሄድ
ተግባር 4 ፡- የ 4 ኛ፣የ 8 ኛና 10 ኛ ክፍል ውጤት ትንተና በማድረግ ከተገኘው ውጤት አንፃር ለውጤታማነቱ
የእቅድ መነሻ ሀሳብ እንዲሆን ማስቻል፣
4.1 የ 8 ኛ ክፍልና የ 10 ኛ ክፍል የፈተና ውጤት ትንተና በማካሄድ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ማድረግ
ተግባር 5 ፡- የ 4 ኛ ከፍል የንባብ ብቃት መለኪያ በጉድኝት ደረጃ ማዘጋጀትና ፈተና ማካሄድ፣
ተግባር 1፡- ትምህርቱ ከት/ቤቶች ግቢ ውጭ ለህብረተሰቡ የሚሰጥበትን ስልት ቀይሶ ተግባራዊ ማድረግ፣
ትምህርቱን ወደውጭ ለማውጣት የሚያስችል ስልት በመቀየስና ዕቅድ በማዘጋጀት ተግባራዊ ማድረግ
በት/ቤት ደረጃ ተግባራዊ የሆኑና ተግባራዊ ያልሆኑ እሴቶችን ለይቶ መያዝና ተግባራዊ ያልተደረጉ
እሴቶችን ተግባራዊ ማድረግ
ተግባር 2 ፡- ከት/ቤት ውጭ ያሉ ልዩ ልዩ ባለሙያዎችን በት/ቤት ተገኝተው ትምህርትን የማጠናከር ተግባር እንዲያበረክቱ
ማድረግ፣
ተግባር 3 ፡- ትምህርቱ በሁሉም የወረዳው ት/ቤቶች (ከ 5—10 ኛ) ክፍል ውስጥ በተሻሻለው አዲስ ስርዓተ ትምህርትና
በሰለጠኑ መምህራን መሰጠቱን ማረጋገጥ፣
ተግባር 4 ፡- ከ 1 ኛ-4 ኛ ክፍል ለሚያስተምሩ መምህራን ተገቢና ተከታታይ ስልጠና መስጠት፣ ትምህርቱን የሚያስተምሩ
መምህራን ከአካባቢ ሳይንስ ት/ት በተለይም ደግሞ የስነ-ምግባር እሴቶችንችን ለይተው ምን ያህል
እንሚያስረዱ በየወሩ በክፍልና በሳይክል ደረጃ እንዲወያዩ ማድረግ፣
ግብ ሀያ ሁለት
ትምህርቱን በይበልጥ ለማስረፅ ሌሎች ተጓዳኝ ተግባራትን አጠናክሮ ተማሪዎች ላይ በመስራት
የትምህርት አሰጣጥን በማጠንከርና በበቂ ሁኔታ ተግባራዊ ማድረግ፡፡
ተግባር 2፡- የት/ቤቱን ተማሪዎችና መምህራን በእሴቶች አካባቢያዊ አተገባበር ችግር ዙሪያ የተደራጀ ልዩ ልዩ መድረኮችን ፈጥሮ ውይይት
በማድረግ ግንዘቤ መፍጠር፣
ተግባር 3 ፡- ልዩ ልዩ አደረጃጀቶች በመመሪያዉ መሰረት ከየድርሻው በተጨማሪ የጋራ ፎረም በመፍጠር በዓመቱ በአጠቃላይ በት/ቤታቸው
ልዩ ልዩ ጉዳዮች ላይ አራት ጊዜ መክረው ለችግሮች መፍትሄ ማስቀመጥ፣
ተግባር 4፡- የስነ-ምግባር መኮነኖች ክበብ በየት/ቤቱ በመመሪያው መሰረት ተቋቁሞ ውጤታማ ስራ እንዲሰራ ማድረግ፣
ተግባር 5፡- የተማሪዎች ካውንስል ፓርላማ ም/ቤት የምርጫ ሂደቶችን ተከትሎ እንዲመረጡ በማድረግ ተግባራዊ ልምምድ ማድረግ፣
ግብ ሀያ ሶስት
የተጠናከሩ የክፍል ውስጥ የክበባትና የአደረጃጀት ስርዓቶች ተከታታይነት ባለው መልኩ መዘርጋትና ተግባር ላይ
በማዋል የተማሪዎችን ዲሲሰፕሊን ማሻሻል፡፡
ተግባር 1፡- በየሴክሽኑና ት/ቤት ደረጃ አሳታፊ በሆነ መንገድ የተማሪዎች መተዳደሪያ ደንብ በወቅቱ ወጥቶ ተግባራዊ ማድረግ፣
ተግባር 2፡- የልዩ ልዩ የተማሪዎች አደረጃጀቶችን ባረጋገጠ መልኩ የአለቆች ህብረት፣የጎበዝ ተማሪዎች ህብረት፣የተማሪዎች ካውንስል፣የሴት
ተማሪዎች አማካሪ ኮሚቴ ወ.ዘ.ተ በወቅቱ በአግባቡ ማደራጀት፣
ተግባር 3፡- የት/ቤቱ ተማሪዎች ከሀገሪቱ ራዕይ በመነሳት የወደ ፊት ራዕያቸውን እንዲለዩ መዝግቦ በራዕያቸው ላይ የተደራጀ ውይይት
እንዲያደርጉና የባለሙያ ተጨማሪ ማብራሪያ እንዲያገኙ ማድረግ፣
ግብ ሀያ አምስት
ተማሪዎች በትምህርት ቤትና ከትምህርት ቤት ውጭ በንድፈ ሀሰብ የቀሰሟቸውን እሴቶች የተላበሱ መሆኑን የሚያረግጡባቸው
ተግባራዊ ስራዎች በማከናወን ተጨባጭ ውጤታማ ለውጥ ማሳየት፡፡
ተግባር 1፡- እሴቶች ት/ቤት ባሉበት ደረጃና አካባቢያዊ ሁኔታ ከህ/ሰብ ባህል፤ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ጉዳዮች አንፃር ወዘተ በመነሳት
ተማሪዎች ሊሳተፉባቸው የሚችሉ ስራዎችን ተግባራት ለይቶ ማቀድ፤ የአሰራርና ስምሪት አፈፃፀም ስርዓት መዘርጋት፤ ባደረጉት ተግባራዊ
እንቅስቃሴ ግምገማና ውይይት እንዲያደርጉ ማድረግ፣
ተግባር 2፡- ተማሪዎች በተግባር የተሳተፉባቸውን ስራዎች እንደየስሜታቸው በመለየት ተሞክሮ እንዲለዋወጡ፣ ከውጤቱም ምን እንደተገኘ
በጋራ እንዲመከሩ ማድረግ፣ በግልና በቤተሰብ የዕለት ተዕለት ኑሮ መተግበር የሚገባቸውን ለይተው ወደ ተግባር እንዲገቡ
የማነሳሳት ስራ መስራት፣
ተግባር 3፡- የሀገሪቱን ራዕይና እሴቶች ከት/ቤቶች ግቢ ውስጥ በጉልህ ቦታ ተፅፈው የት/ቤቱ ማህበረሰብ ሲወጡና ሲገቡ እያዩ የበለጠ
እንዳይረሷቸው ማድረግ፣
ተግባር 4፡- የስነ-ዜጋና ስነ-ምግባር መምህራን በዘመኑ ውስጥ አራት ጊዜ /በየሩብ ዓመቱ /በመገኘት በ 2010 ዓ.ም ትምህርት ዘመን መጨረሻ
ያደርጉትን ምክክር ውሳኔ መነሻ በማድረግ ልምድ በመለዋወጥ ትምህርቱን ማጠናከር፣
ተግባር 5፡- የመምህራን ህብረትን አጠናክሮ በማቋቋም በትምህርት ይዘቶች፣በክበብ እንቅስቃሴዎች ከት/ቤት ውጭ እሴቶን ከማስረፅ አኳያ
በተማሪዎች ዲሲፒሊን ችግሮች አጠቃላይ በመማር-ማስተማሩ በሚያጋጥሙ ችግሮች ዙሪያ ተከታታይ ምክክር ማድረግ፣
ተግባር 6፡- በየደረጃው ያሉ ተማሪዎች በክፍል ውስጥ በንድፈ ሀሳብ ደረጃ የቀስሟቸውን እሴቶች ከት/ቤት ውጭ በማህበረሰብ ውስጥ ተግባራዊ
በሚደረግባቸው ዘርፈ ብዙ ተግባራት ውስጥ ማሰማራት፣
ተግባር 7፡- በወረዳው የትምህርት ተቋማት ውስጥ እሴቶችን በይበልጥ ለማስረፅ የሚያስችሉ ተጓዳኝ ተግባራትን በተጠናከረ መልኩ ተግባር
ላይ ማዋል፣
ተግባር 8፡- የህፃናት ፓርላማ ስርዓትን በሁሉም የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት ተግባራዊ ማድረግና እሴቶችን በተሻለ መልኩ ማስረፅ፣
ተግባር 9፡- የስነ-ዜጋና ስነ-ምግባር ትምህርት ባለፉት ዓመታት ያመጣውን ለውጥ ዳሰሳ በማካሄድ ለቀጣይ ማሻሻያነት እንደ ግብዓት
መጠቀም፣
3.1.5. የስርዓተ-ትምሀርት ማሻሻያ መርሃ-ግብር
ግብ ሀያ ስድስት
የስርዓተ ትምህርቱን ትግበራ ለመደገፍ መካተት የሚገባቸውን ወሳኝ ተጓዳኝ ተግባራት በየትምህርት ቤቱ
ማስፈፀም፡፡
ተግባር 1፡- ከት/ቤት መሻሻል ማዕቀፍ ውስጥ ትኩረት የተሰጣቸው ሁለገብ ጉዳዮች አካባቢ እንክብካቤ፣ስርዓተ ፆታ፣ኤች አይ ቪ
ኤድስ፣ሀይጅንና ሳንቴሽንን ማስተግበሪያ አቅጣጫ ቀይሶ ተግባራዊ ማድረግ፣
ተግባር 2፡- በየደረጃው ያለ የትምህርት ዘርፍም ሆነ ህብረተሰብና የትምህርት ባለድርሻዎች ስርዓተ ትምህርቱ የሚገመገምበት፣ግብረ -መልስ
የሚሰጥበት ቋሚ ስርዓት መዘርጋትና ተግባራዊ ማድርግ፣
ተግባር 3 ፡- ተጨማሪ የንባብና የፅህፈት ክህሎት ማስተማሪያ የተማሪዎች ተግባር ተኮር ፣የቤተ-ሙከራ ማንዋሎች ተባዝተው ለአዲስና
ለሌሎች ት/ቤቶች ማሰራጨት እንዲሁም በየደረጃው ባሉ በሁሉም ጉዳዮች (any matter) አማካኝነት የሱፐር
ቪዢን ድጋፍ ማድረግ፣
ተግባር 4 ፡- በክፍል ውስጥ እስከ ወረዳ ያሉ ልዩ ልዩ የተማሪዎች አደረጃጀትና የአሰራር ስርዓቶችን በተጠናከረ
የተቀናጀና ተከታታይነት ባለው መልኩ አደራጅቶና የአሰራር ስረዓቶችን በማጠናከር ወደ ስራ በማስገባት
የወረዳውን ተማሪዎች ስነ-ምግባር ማሻሻል፣
ተግባር 5 ተማሪወች ባለድሜ ጋብቻ እና ሌሎች ፆታዊና ፆታዊ ባልሆኑ ምክንያቶች ት/ታዉን እንዳያቋርጡ
ክትትልና ድጋፍ ማድረግ፤
ተግባር 6 ረዳት የሌላቸዉ ተማሪወች ከት/ቤት ልዩ ልዩ መዋጮወች/ክፍያወች ነፃ እንዲሆኑ ማድረግ፤
ተግባር 7 ሴት ተማሪወች በት/ታቸዉ እንዲጎብዙ ክትትል ማድረግና የተሻለ ዉጤት ያመጡትን ደግሞ ለይቶ
ማበረታት
ግብ ሃያ ሰባት
በሀገር አቀፍ ደረጃ የወጣውን የስርዓተ ትምህርት መነሻ በማድረግ ክልላዊ ስትራቴዎች
ተዘጋጅተው በዝግጅትና ትግበራ ሂደት በስኬታማነት መፈፀም፡፡
ተግባር 1፡- ለት/ቤቶች መፅሀፍት ስርጭት ብዛት በአይነትና በክፍል ደረጃ ለይቶ ማቀድ፣
ተግባር 2 ፡- በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚዘጋጁትን የተለያዩ የክፍል ደረጃዎች ትም/ት መምሪያ ማስተማሪያ ማሳወቅ፣
ተግባር 3፡- በሀገር አቀፍ ደረጃ ተዘጋጅተውና ታትመው የሚሰራጩትን የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት የመማሪያ
ማስተማሪያ መፅሀፍትን ለሁሉም የመንግስት ት/ቤት ተማሪዎች በነፃ መታደላቸውን ማረጋገጥ፣
ተግባር 4፡- ተግባር-ተኮር የጎልማሶች መሰረታዊ ትምህርት ስርዓት ትምህርት ማተሪያሎች / መርሀ ትምህርት
የአመቻቾች ማንዋልና የተሳታፊዎችን የተግባር መልመጃዎች መፅሐፍ ማሰራጨት፣
ተግባር 5፡- የቅድመ-መደበኛ ትምህርት የማስተማሪያ መፅሐፍት/ደረጃ አንድ፣ሁለትና ሶስት/ማሰራጨት፣
ግብ ሃያ ስምንት
የክልሉን የአጠቃላይ ትምህርት አፈፃፀም በቀጣይነት እያሻሻሉ ለመሄድ እንዲቻል የትምህርት
ጥናትና ምርምር ባህልን አጠናክሮ ተግባራዊ ማድረግ፡፡
ተግባር 1፡- መምህራን በት/ቤት ደረጃ በሰለጠኑበት የሙያ ማሻሻያ ስልጠና መሰረት በተለያዩ ችግሮች ላይ ተግባራዊ
ጥናትና ምርምር እንዲያካሂዱ ማድረግ ውጤቱን በትምህርት ቤት ጉባኤ ቀርቦ የፓናል ውይይት
ማካሄድ፣ምርጦችን እስከ ክልል ማቅረብና መፍትሔዎችን ለችግር መፍቻነት መጠቀም፣
ተግባር 2፡- አዲስ የተሸሻለውን ስርዓተ ትምህርት ትግበራ አሳታፊ በሆነ ሂደት መገምገምና የማሻሻያ ግብዓቶችን
ማሰባሰብ፣
ተግባር 3፡- ከተቋማት እስከ ወረዳ ባሉ የትምህርት ባለሙያዎች በሴቶች ትምህርት ተሳትፎ ዙሪያ የጉድኝት ማዕከላት
በትምህርት ስራ ያለውን አስተዋፅኦ በስርዓተ ትምህርት ትግበራ ዙሪያ በትምህርት ውስጣዊ ብቃት
ዙሪያ በሳይንስና ሂሳብ አሰጣጥ ዙሪያና በተከታታይ ምዘናና ተማሪ ተኮር የማስተማር ስነ-ዘዴ ዙሪያ
ጥናትና ምርምር እንዲያደርጉ ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠር፣
ግብ ሃያ ዘጠኝ
ተግባር 1፡- የመጀመሪ ደረጃ ትምህርት ማጠናከሪያ ትምህርት፣የመጀመሪያ ትምህርት ማጠናከሪያ ፈተና፣የተማሪዎች
ምዝገባ፣የፈተና ህትመት ስርጭት፣የፈተና አስተዳደርና ውጤትን ማሳወቅ፣
1.1. በ 2012 ዓ.ም በትም/ቤቶች የተፈታኞች ብዛትን መለየትና ከወዲሁ ቅድመ ዝግጅት ማድረግና በጀት
መያዙን ማረጋገጥ
ተግባር 2፡- የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ትምህርት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ፈተና የተማሪዎች
ምዘገባ የፈተና ህትመት፣ስርጭት የፈተና አስተዳደርና ውጤትን ማሳወቅ
1.1. በ 2012 የትም/ቤቶች የተፈታኞች ብዛት መለየትና ከወዲሁ ቅድመ ዝግጅት ማድረግ
ተግባር 3፡- በተከታታይ ምዘና ላይ ባጋጠሙ ችግሮች ላይ ክትትል በማድረግና አፈፃፀሙን በማየት ቀጣይ የመፍትሔ
አቅጣጫ ማስቀመጥ፣
2.1. ክትትል ማድረግና አፈፃፀሙን በማየትና የመፍትሔ አቅጣጫ አስቀምጠው ተግባራዊ ማድረግ፣
ተግባር 4፡- የቀለም ትምህርትና የስፖርት ውድድር የሚካሄድበትን አግባብ ማስቀመጥና መተግበር፣
ተግባር 5፡- በክልል አቀፍ ፈተናዎች አስተዳደር ላይ የተከሰቱ ችግሮች ተለይተው በ 201 ዓ.ም እንዳይከሰት
ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ውይይት ማካሄድ፣
ተግባር 6፡- የትምህርት ማስረጃ ማረጋገጫ ለሚጠይቁ ተገልጋዮች ተገቢውን አገልግሎት መስጠት፣
.በድጋሜ ካርድ የተሰጣቸውን ተገልጋዮች ብዛት ለይቶ መያዝ
3.1.6. የኢንፎርሜሽን ኮምዩኒኬሽን ቴክኖሎጅ አገልግሎትን የማስፋፋት መርሃ-ግብር
ግብ ሰላሳ
የኢንፎርሜሽን ኮሚኒኬሽን ቴክኖሎጂ አገልግሎት የማስፋፋት ፕሮግራምን ተቋማዊ የሆነ
አሰራር ስርዓት እንዲኖር ማድረግ፡፡
ተግባር 1፡- በወረዳው ውስጥ የሚገኙ 1 ኛ ደረጃ ሙሉ ሳይክልና በ 2 ኛ ደረጃ ት/ቤቶች ዋና ዋና ግብዓቶች
እንዲሟሉና እንዲደራጁ በማድረግ የመማር-ማስተማርና ስልጠና ሂደቱን በተጠናከረ መልኩ መደገፍ፣
ግብ ሰላሳ አንድ
አዲስ በተሸሻለው መደበኛና መደበኛ ያልሆውን ትምህርት በመደገፍ የትምህርት ጥራትን
ማስጠበቅ፡፡
ተግባር 1፡- የሬዲዮ ስርጭት ለማይደርስባቸው ት/ቤቶች ሚሞሪ አስጭነዉ ት/ቤቶች እንዲጠቀሙ ማድረግ፣
ተግባር 2፡- የት/ቤት ሚኒ-ሚዲያ ክበባትን ለማጠናከር ለ 124 መምህራንና ተማሪዎች በሚኒ-ሚዲያ አጠቃቀም ላይ
ስልጠና መስጠት፣
ተግባር 3፡- የሬዲዮ ፕሮግራም የጊዜ ሰሌዳ ተዘጋጅቶ ለመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤቶች በወቅቱ እንዲደርስ ማድረግ፣
በ 2 ኛ ደረጃ የሁለተኛ ሳይክል ት/ቤቶች (11—12 ኛ) የሚማሩ ተማሪዎችን የትምህርት ሽፋንን ወ-143 ሴ-146 ድ-289
በመዋእለ ህፃናት የት/ት ፕሮግራም የትምህርት ሽፋንን ወ 250 ሴ 246 ድ 496 ማድረስ
በ ኦ ክፍል የት/ት ፕሮግራም ተሳትፎን ወ 2,779 ሴ-2,761 ድ-5,540 ማድረስ
በአንደኛ ደረጃ በልዩ ፍላጎት ትምህርት ወ 59 ሴ 50 ድ 109 ተማሪዎችን ማስተናገድ
ተግባር ሁለት
በየደረጃው የሚሰጠውን የትምህርት አቅርቦትና ተሳትፎ ለማሳደግ የሚያስፈልጉ ወሳኝ ግብዓቶች እንዲሟሉ ማድረግ፡፡
ለዚህም የሚከተሉት ዋና ዋና ተግባራት ይከናወናሉ፡፡
84 ተጨማሪ መማሪያ ክፍሎችን እና 15 ቢሮወችን መገንባት፤ 180 መማሪያ ክፍሎች እና 21 ቢሮወችን ጥገና ስራ
ማካሄድ
በዚሁ የት/ት ዘመን በሁሉም የክፍል ደረጃዎችና የትምህርት አይነቶች የመማሪያ መፃህፍትን ለሁሉም ተማሪዎች
በነፍስ ወከፍ ማዳረስ
በወረዳው ለተማሪዎች በቀመር የሚመደበውን የ 2012 ዓ.ም መደበኛ በጀት ክትትል በማድረግ ተገቢ የማሻሻያ ሀሳብ
በማቅረብ ግብረ-መልስ ለሚመለከታቸው አካላት መስጠት
ከህብረተሰቡ፣ከረድዔት ሰጭ ድርጅቶችና ከአካባቢው ተወላጆች ወዘተ ሀብትን በማሰባሰብ ወደ አንድ ቋት
ማስገባትና ይህን ከተለያዩ ምንጮች የተገኘን ሀብት ፍትሃዊ በሆነ መልኩ ድልድል መፈፀም
ተግባር ሶስት
በወረዳው የአካቶ ት/ት ባሉት ት/ቤቶች በሚማሩ ተማሪዎች ጥናት በማካሄድ ፕሮጀክት በማዘጋጀት የሃብት
ማፈላለግ ማመንጨት ተግባር መፈፀም፣
ግብ ሁለት
መሠረታዊ የጎልማሶች ትምህርትን በወረዳው ባሉ ቀበሌዎች ማጠናከር፡፡
ተግባር አንድ
መሠረታዊ የጎልማሶች ትምህርት ፕሮግራም በሁሉም የወረዳው ቀበሌዎች በመጀመር የጎልማሳውን አቅም
ማጠንከር፣
በ 135 ጣቢያወችና በ 135 አመቻቾች ወ 1241 ሴ 1004 ድ 2245 አዲስና ወ 807 ሴ 558 ድ 1365 ነባር በጠቅላላው ወ
2048 ሴ 1562 ድ 3610 ጎልማሶችን ማሰልጠን
ተግባር ሁለት
ወረዳዊ የተቀናጀ ተግባር-ተኮር የጎልማሶች ትምህርት ስትራቴጂ ተዘጋጅቶ ፕሮግራሙን በሁሉም ቀበሌዎች
ተጠናክሮ መስጠት መጀመር፣
ተግባር ሶስት
ወረዳዊ የህዝብ ንቅናቄ ሰነድ በማዘጋጀትና ከወረዳ እስከ ቀበሌ በማስተዋወቅ ግንዛቤ
መፍጠር፣
ተግባር አራት
ማንበብ፣መፃፍና ማስላት የማይችሉ ወጣቶችና ጎልማሶችን መረጃ በየደረጃው አጠናቅሮ
መያዝና ለሚመለከተው ክፍል ማሳወቅ፣
ግብ ሶስት
የትምህርት ፍትሀዊነትን ማስጠበቅ፡፡
ተግባር አንድ፡-
o ስርዓተ-ፆታን በትምህርት ስራ ውስጥ ማካተት
በየደረጃው በሚገኙ የትምህርት ፕሮግራሞች የስነ-ፆታዊ ክፍተትን/Gender Disparity/ የሚያጠቡ ተግባራትን መፈፀም፡፡
ለዚህም ለ 2012 ዓ.ም የሴቶችን የት/ት ተሳትፎ ለማጎልበት 19,712 ለማድረስ ዕቅድ ተይዟል፡፡
ህ/ሰቡ ስለሴት ልጅ ያለውን አስተሳሰብ ስለ ሴቶች ትምህርት አስፈላጊነትና ችግሮች የግንዛቤ ማጎልበቻ በተለያዩ
መድረኮች መፍጠር
በት/ቤት ዙሪያ የሚገኙ አደረጃጀቶችን በመጠቀም ያለ እድሜ ጋብቻንና ጠለፋን ለማስቀረት ጥረት ማድረግ
በትምህርታቸው ጥሩ ውጤት ላመጡ ሴት ተማሪዎች ማበረታቻ ማለትም የገንዘብና የማቴሪያል ድጋፍ
የሚያገኙበትን ሁኔታ መፍጠር
በየት/ቤቶች የሴት ተማሪዎች የተጨማሪ ትምህርት ድጋፍ ማድረግ
ተግባር ሁለት
በከተሞችና በገጠር መካከል ያለውን የትምህርት አቅርቦት ልዩነት/urban-Rural inequity/ ለማጥበብ በገጠርና
በኋላቀር አካባቢዎች የትምህርት ተቋማት በተጠናና በተጠናከረ ሁኔታ ማስፋፋት፣
ተግባር ሶስት
ዝቅተኛ የተማሪ ተሳትፎ ባላቸው ቀበሌዎች ልዩ ትኩረት በመስጠት የትምህርት ተሳትፎን የሚያጎለብቱ የተለያዩ
ተግባራትን መፈፀም፣
የሳተላይት ትምህርት ቤቶችን በማስፋፋት መክፈትና የት/ት ዕድል ያላገኙትን ዕንዲያገኙ ማድረግ
እንደ አከባቢው ተጨባጭ ሁኔታ ማህበረሰብ አቀፍ አፀደ-ህፃናት ተቋም ማቋቋም
ግብ አራት
የትምህርት ብቃትን ማሻሻል፡፡
ተግባር አንድ
በ 2012 ዓ.ም በጀት ዓመት በመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤቶች የመማሪያ ሴክሽን ተማሪ ጥምርታ በስታንዳርዱ መሠረት
ማድረግ፣
ተግባር ሁለት
በየደረጃው የሚገኙ የትምህርት ተቋማት የተማሪዎችን መድገምና ማቋረጥ ምጣኔን የሚያሻሽሉ ተግባራትን
በውጤታማነት መፈፀም፣
የመድገም ምጣኔን 2% በታች ማድረስ
የማቋረጥ ምጣኔን ከ 2% በታች ማድረስ
የእርከኑን ማጠናቀቂያ ምጣኔ ማሻሻል
ግብ አምስት
በወረዳችን በሚገኙ በሁሉም ት/ቤቶች ደረጃቸውንና ጥራታቸውን የጠበቁ
የትም/መሳሪያዎች ማቅረብ፡፡
ተግባር አንድ
የትም/መሳሪያዎች አቅርቦትን አስመልክቶ ረቂቅ ስታንዳርድና የመረጃ መሠብሠቢያ ፎርማት በማዘጋጀት መረጃውን
በመሰብሰብ፣በማጠናከርና የመነሻ ሀሳብ በማዘጋጀት በሀሳቡ ላይ በስራ ሂደቱ ውይይት በማድረግ ማፅደቅና ስታንዳርድ
ማዘጋጀት፣
ተግባር ሁለት
በተዘጋጀው ረቂቅ ከባለ ድርሻ አካላት ጋር ውይይት በማድረግ የተፈጥሮ ሳይንስ፣የሂሳብ፣የህብረተሰብ ሳይንስ፣የሰ.ማ.ጎ
የትም/መሳሪያዎችን በየዓይነቱ በየትም/ት ሳብጀክቱ የስራ ዝርዝር አዘጋጅቶ ወደ ስራ መግባት፣
ተግባር ሶስት
በማንኛውም መንገድ ማለትም በግዥ ወይም በዕርዳታ የሚገኙ የትም/መሳሪያዎችን በፍትሀዊነት በወቅቱ በየተቋማቱ
እንዲደርስ ማድረግ፣
3.2.2. የ
ንዑስ ተግባር፡- ሲቪል ሰርቪስ ማሻሻያ ፕሮግራም (5%)
ግብ አንድ የሲቪል ሰርቪስ ማሻሻያ ፕሮግራምን በትምህርት ተቋማት አጠናክሮ ተግባራዊ
ማድረግ፡፡
ዓላማ፡- የሲቪል ሰርቪስ ማሻሻያ ፕሮግራምን በመተግበር ውጤታማ አሰራሮችን መፍጠር ነው፡፡
የሚከናወኑ ተግባራት
- ተቋማት ራዕይና ተልዕኳቸውን በግልፅ እንዲያሳውቁ ማድረግ
- የአግልግሎት አሰጣጥን በት/ት ተቋማት ማሻሻል
- አቅጣጫ ጠቋሚ እንዲኖር ማድረግ
- ሰራተኞች የደረት ባጅ መጠቀምና መምህራን ጋዎን እንዲለብሱ ማስተባበር
- የማስተነጋጃ ሰዓት ለይቶ ማስቀመጥ
- ለአግልግሎቱ ሰዓት መጥኖ በማስቀመጥ አግልጋሎት መስጠት
- የውጭ አስተዳደርን በተመለከተ ት/ቤቶች የፋይናንስ አሰራራቸውን በባንክ አካውንት እንዲጠቀሙ ማድረግ
- ትም/ቤቶች የግዢ ስርዓት፣ደንብና መመርያውን ተከትለው እንዲገዙ ማድረግ
- የውጤት ተኮር እቅድ ሁሉም ት/ቤቶች እንዲያዘጋጁ ማድረግ
- ውል የወሰዱና ያልወሰዱ መምህራን እና ሰራተኞችን መረጃ በተገቢው ሁኔታ በመያዝ እንዲያሟሉ ማድረግ
- የ 6 ወር የስራ አፈፃፀም በወቅቱ ተሞልቶ እንዲቀርብ ማድረግ
- የቅሬታ ማስተናገጃ ስርዓትን ማሻሻልና ቅሬታን በፅሁፍ ተቀብሎ ምላሽ በደብዳቤ መስጠት
- የስራ መከታተያ ቸክሊስት አዘጋጅቶ ወደ ተግባር መግባት
- ከአጋር መ/ቤቶች ጋር ተቀናጅቶ መስራት
ግብ ሁለት
ዓላማ ፡-በየዕለቱ የዕቅድ አፈፃፀምን በመገምገም ችግሮችን ፈጥኖ ለማስተካከል እንዲቻል ነው፡፡
የሚከናወኑ ተግባራት
- አስተዳደሩ በየሳምንቱ ስራዎችን ይገመግማል
- ሱፐርቫይዘርና የትምህርት ባለሙያዎች በየ 15 ቀኑ ይገመገማሉ
- ር/መምህራን፣ሱፐርቫይዘርና ጽ/ቤቱ በየሩብ ዓመቱ ይገማገማል
- የጉድኝት ማዕከላት በየወሩ እየተገናኙ ግምገማ ያካሂዳሉ
- የተማሪ ቁጥር መረጃ ት/ቤቶች በየሳምንቱ ለወረዳ ይልካሉ፤ወረዳ ለዞን በማጠናከር ያስተላልፋል
- የየሩብ አመቱና ወርሃዊ ሪፖርቶች ከስራ ግምገማዎች በመነሳት ይዘጋጃሉ
ክፍል 4
4. ዕቅዱን ለመፈፀም ያሉ መልካም አጋጣሚዎች፣ስጋቶች፣መፍትሄዎችና የምንከተላቸው አቅጣጫዎች፣
ወሳኝ የሆኑ የሀምሌና የነሀሴ ወር የቅድመ ዝግጅት ተግባራት በወቅቱና በአግባቡ መፈፀም
መምህራን በወቅቱ በትምህርት ቤት ተገኝተው የቅድመ ዝግጅት ተግባራትን አከናውነው ትምህርት በወቅቱ እንዲጀመር
ማድረግ ፣ከክረምት ኮርስ ተመላሾች በወቅቱ በትምህርት ቤት እንዲገኙ ማድረግ፣
የ 8 ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ውጤትን ለተማሪዎች ወዲያውኑ እንደደረሰ ወደ ትምህርት ቤቶች ማድረስ፣
የትምህርት ቤቶች አከፋፈት በወቅቱ የቀበሌው አመራርና ወላጆች በተገኙበት በደመቀ ስነ-ስርዓት እንዲፈፀም ማድረግ
በስነ-ስርዓቱ ላይ የትምህርት ቤቱን ዕቅድና ከወላጆች የሚጠበቀውን ተሳትፎ በማስተዋወቅና ሌሎችንም ወሳኝ ተግባራት
በማከናወን መፈፀም፣
ህብረተሰቡ የጊዜ ሰሌዳውን ጠብቆ በየ ወሩ በመወያየት በተማሪዎች ውጤትና ዲሲፕሊን መሻሻል እንዲያመጣና
ተቋሙንም በፋይናንስ የማገዝ ስራ እንዲሰራ መግባባት፣
ትርጉም ያለው ከተቆጣጣሪነት መረጃ ከመልቀምና ከማቀባበል ያለፈ የሱፐርቪዥን ድጋፍ መስጠት፣
ስራዎችን በቼክሊስት ቆጥሮ ለየስራ ሂደቱና በየደረጃው ላሉ ተቋማት ማስረከብ፣
ወቅታዊ፣ታማኝና ተከታታይነት ያለው የሪፖርትና ግብረ-መልስን ስርዓት አጠናክሮ ተግባራዊ ማድረግ፡፡ከሁሉም በላይ
ደግሞ ከሪፖርት ጥንቅር በኋላ ለበታችኛው አካል የሚሰጠው ግብረ-መልስ በራሱ አስተማሪ የስልጠናና ማስተካከያ
መሳሪያ መሆኑን በመረዳት በአግባቡ መተግበር፡፡
ክፍል 5
5. የዕቅዱ አተገባበር፣የግንኙነትና የሪፖርት አደራረግ ስርዓት