You are on page 1of 4

የተፈጥሮ ሃብት ልማት፤ጥበቃ እና አጠቃቀም የግንቦት ወር 2015 ዓ.

ም ቼክ- ሊስት

1. በአፈርና ውሃ ጥበቃ

 የስነ- አካላዊ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራዎችን በፕሮግራሞች፤በግል እና በሳምንት አንድ ቀን በቡድን


ማስቀጠል፤

 የተፋሰስ ተጠቃሚዎች ማህበራትን ወደ መሰረታዊ ህብረት ስራ ማህበራት ማሸጋገር


(40%)፤የስራውን አፈጻጸም የግብርና እና የህ/ስ/ማ ጽ/ቤቶች በየሳምንቱ በጋራ እየገመገሙ
እንዲመሩት ማድረግ፤

 ሞዴል ተፋሰሶችን በፓኬጁ መሰረት መለየታቸውን በማረጋገጥ የተሰሩ ስራዎችን እና የተገኙ


ውጤቶችን መቀመር፤ ስራውን የሚከታተል ከአፈርና ውሃ ጥበቃ፤ከደን ልማት፤ ከአት/ፍራፍሬ፤
ከእንስሳት ሃብት ልማት እና ከሰብል ልማት የተውጣጣ የባለሙያዎች ቡድን ከዞን እስከ ወረዳ
ማደራጀት እና ወደ ስራ ማስገባት፤

ሞዴል ተፋሰሶች የሚከተሉትን መስፈርቶች ሊያሟሉ ይገባል

 በአጠቃላይ በተፋሰሱ መሰራት ካለበት የስነ-አካላዊ አፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ ሽፋን ከ 80% በላይ
ያጠናቀቁ፤

 ወደ ተፋሰስ ተጠቃሚዎች ህ/ስ/ማ የተሸጋገሩ፤ጽ/ቤት እና አስፈላጊ ቁሳቁስ የተሟላላቸው ከእቅድ


ዝግጅት ጀምሮ ኃላፊነታቸውን በመወጣት ላይ የሚገኙ፤

 100% ከልቅ ግጦሽ ነጻ ማድረግ፤

 የውሃ አማራጭ ያላቸው፤

 በተለያዩ የገቢ ማስገኛ ስራዎች የገቡ፤

 የስራ እድል የተፈጠረባቸው/የሚፈጠርባቸው፤

 የአፈር ለምነት ማሻሻያ ስራዎች (መደበኛ ኮምፖስት፤ቨርሚ ኮምፖስት፤ባዮ ሳለሪ) በጥራት


እየተከናወነባቸው ያሉ፤

 የለሙ ተፋሰሶችን ለመሬቱ ባለይዞታዎች ርክክብ በማድረግ 100% ከልቅ ግጦሽ ነጻ ማድረግ
መተዳደሪያ ደንቡን ተግባራዊ ማድረግ፤
 ከሚመለከታቸው ጽ/ቤቶች እና የስራ ቡድኖች ጋር በመቀናጀት የለሙ ተፋሰሶችን በተለያዩ የገቢ
ማስገኛ ስራዎች ማለትም በደን ልማት፤በእንስሳት ማድለብ እና ርባታ፤በንብ ማነብ እና በፍራፍሬ
ልማት ወደ ስራ በማስገባት ለተፋሰሱ ተጠቃሚዎች የገቢ ማንጭ እንዲሆኑ ማስቻል፤

2. በደንና አግሮፎረስትሪ
 ለተከላ ብቁ ጠንካራ እና ጤነኛ ችግኝ ለማድረስ ለተፈሉ ችግኞች አስፈላጊውን እንክብካቤ አጠናክሮ
ማስቀጠል (ማዛመት፤አረም ማረም፤ማሳሳት….)፤

1
 የተፈላ ችግኝ መረጃ በዝርያ ለዞን መላክ፤
 በፕላስቲክ ለሚፈላ ችግኝ ትኩረት መስጠት (በወረዳውም ሆነ በቀበሌ መጋዘን አንድ ጥቅል ፖሊቲን
መክረም የለበትም)፤

 ለስነ-ህይወታዊ ስራዎች ትኩረት መስጠት፤

 የአግሮፎረስትሪ ፓኬጆችን ከሪፖርት ባለፈ ሙያዊ የጥራት ደረጃቸውን ተከትሎ በመስራት ረገድ ሰፊ
ክፍተት የሚታይ በመሆኑ ከወዲሁ በየፓኬጁ የተለየውን መሬትና ተጠቃሚ ትክክለኛነት በማረጋገጥ
መሬት ማስነካት (የ GPS ኮርዲኔት፤የተጠቃሚዎች ዝርዝር ፤ስልጠና መስጠት)፤

 የስነ-አካላዊ አፈርና ውሃ ጥበቃ ስራዎችን በስነ- ህይወታዊ ዘዴ ለመሸፈን የድርጊት መርሃ-ግብር


(Action Plan) በአስቸኳይ በማዘጋጀት አስፈላጊውን የቅድመ-ዝግጅት ስራ ማጠናቀቅ፤

 አሁን ያለውን የዝናብ ሁኔታ በመጠቀም በቀጥታ ዘር እና በሳር ግንጣይ የስነ-አካላዊ ስራዎችን
በእጽዋት ማጠናከር፤

 የሳር ሰርጥ እቅድን ማከናወን፤

 የችግኝ ጣቢያ የ GPS ኮርዲኔት

 የጥራት ደረጃውን የጠበቀ የችግኝ ጉድጓድ ዝግጅት ከተከላ ወቅት አንድ ወር ቀደም ብሎ ማጠናቀቅ፤

 የሁለተኛ ዙር የጽድቀት መመዘኛ መስራት፤

 ለአረንጓዴ አሻራ ልማት ወረዳዊ እና የቀበሌ ማስጀመሪያ ቦታ መረጃ በተላከው ፎርማት መሰረት
እስከ ግንቦት 10/2015 ዓ.ም ለዞን መላክ፤

3. ፕሮግራሞችን እና ፕሮጀክቶችን በተመለከተ


 በዞናችን የተፋሰስ ልማቱን በገንዘብም ሆነ በማቴርያል በማገዝ ጉልህ አስተዋጽኦ በማድረግ ላይ
ከሚገኙት ፕሮግራሞች መካከል (RPSNP, CALM P4R, SLMP, PASIDP) ዋነኞቹ ናቸው፡፡
በነዚህ ፕሮግራሞች የታቀፉ ተፋሰሶች ከእቅድ ዝግጅት ጀምሮ እስከ ውጤት የሚደረግላቸው ክትትል
እና ድጋፍ በሚፈለገው ደረጃ ላይ አይደለም አፈጻጸማቸውም ከመደበኛው ተፋሰሶች ብዙም የተለየ
ሆኖ አይታይም፡፡ በመሆኑም የቴክኒክ ኮሚቴዎችን በማጠናከር እና ጥብቅ ክትትል እና ድጋፍ በማድረግ
እና እየገመገሙ በመምራት ለመደበኛ ተፋሰሶች ሞዴል ሆነው ምርጥ ተሞክሮ የሚቀመርባቸው እና
ልምድ የሚወሰድባቸው ተፋሰሶች ማድረግ፤
 የወረዳ ቴክኒክ ኮሚቴ አባላት የፕሮግራሞችን አፈጻጸም በመስክ ድጋፍና ክትትል በማድረግ እና በቃለ
ጉባኤ በተደገፈ ግምገማ በጥብቅ መምራት የግምገማውን ውጤት በቡድን መሪዎች አማካኝነት ለዞን
ሪፖርት ማድረግ፤
 የአየር ንብረት ማስተካከል በዘላቂ መሬት አያያዝ ፕሮግራም (CALM P4R) የተፋሰስ ተጠቃሚዎች
ህ/ስ/ማ/ አባላትን ቁጥር ከተቅላላ ተጠቃሚው ከ 60% በላይ ማሳደግ፤

2
 የልማታዊ ሴፍቲኔት ቀሪውን 50% የማህበረሰብ ስራዎችን በኖርም እና በጥራት ሁሉንም
የፕሮግራሙን ተጠቃሚዎች በማሳተፍ ማጠናቀቅ፤

 የልማታዊ ሴፍቲኔት የኮንትራት ባለሙያዎች በአብዛኛው ኃላፊነታቸውን በአግባቡ እየተወጡ


ባለመሆኑ እና አንዳንዶቹም በግል ስራ ላይ መሰማራታቸውን መረጃ የደረሰን በመሆኑ በውጤት ተኮር
ስራ ሰፍሮ በመስጠት ወደ ስራ ማስገባት፤

 በወረዳው ውስጥ በመንቀሳቀስ ላይ የሚገኙ በተፈጥሮ ሃብት ልማት ስራ ላይ የሚንቀሳቀሱ


መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች የሚያከናውኗቸውን ስራዎች በመከታተል እና መረጃ በመያዝ ለዞን
መላክ፤

4.የ 2016 ዓ.ም የመደበኛ እና የፕሮግራሞች አሳታፊና የተቀናጀ እቅድ ማዘጋጀት

 የተጠቃሚዉን ተሳትፎ በማሳደግ ከወዲሁ የባለቤትነት ስሜት ሊፈጥር እንዲችል ታስቦበትና እና


አሳታፊ ተደርጎ እቅዱ ሊዘጋጅ ወይም የተፋሰስ ክለሳ ስራዉ ሊሰራ ይገባዋል፡፡
 በአስር ዓመት መሪ እቅዱ ላይ የተቀመጡ ስትራቴጅክ ግቦችን ታሳቢ ማድረግ፤
 ባለፉት አመታት የተገኙ ጥንካሬዎች፣ ምርጥ ተሞክሮዎችና አሰራሮችን ታሳቢ ማድረግ፣
 በ 2015 ዓ.ም የተደራጀውን የሚሰራ ኃይል በ 10 በመቶ እንደሚጨምር ታሳቢ ማደረግ፣
 የሚታቀደው በ 2015 ዓም ከተሰራው ስራ በ 15% ተጨምሮ እንዲታቀድ ማደረግ በተለይም ነባር
ስራዎች ላይ
 ሁሉም ወረዳ የፊዚካል ስራዎች እቅድ ከ 23 ቀን በላይ የሚያሰራ እቅድ ማቀድ፣
 የደን ሽፋናችንን ለማሳደግ የዚህን ዓመት የደን ልማት ሽፋን አፈጻጸማችንን በ 1 በመቶ በመጨመር
እንዲታቀድ ማድረግ፤
 የተከላ ቦታ በ 2015 ከተከናወነው በደን ልማት 7% በጥምር ደን እርሻ 10% በመጨመር ማቀድ፤
 የመደበኛ እስከ ሰኔ 10/2015
 የፕሮግራሞች እስከ ሚያዚያ 30/2015

5.መረጃ እና ሪፖርት በተመለከተ

 እስካሁን ባለን ልምድ ከዞን ካልተጠየቀ በስተቀር በየሳምንቱ በስልክ፤በኢሜል እና በቴሌግራም መረጃ
የመስጠት ልምዱ ደካማ ነው፡፡ በመሆኑም በዚህ ዓመት ከዚህ ችግር በመውጣት በእጃችሁ
የሚገኘውን መረጃ በተላከው የሳምንታዊ ሪፖርት ቅጽ መሰረት በየሳምንቱ ለዞን እንዲደርስ
ማድረግ፤

 የሪፖርት ተዓማኒነት ችግርን ለመቅረፍ መረጃ በየተፋሰሱ እንዲያዝ ማድረግ በመስክ ለክቶ
ማረጋገጥ፤

3
 በአካባቢ ላይ እና የህ/ሰቡን የኑሮ ሁኔታ በማሻሻል ለውጥ ያመጡ ተፋሰሶችን ምርጥ ተሞክሮ
መቀመር፤

You might also like