You are on page 1of 6

ይህን ያውቁ ኖሯል?

የከተሞች መስፋፋት ታይቶ በማይታወቅ ፍጥነት እያደገ በመምጣቱና የህዝብ ቁጥሩም በዛው ልክ እያሻቀበ በመምጣቱ
ከከተማ ነዋሪው ህዝብ የሚመነጨው የቆሻሻ መጠንም ከሚገመተው በላይ ሆኗል፡፡ ስለሆነም ይህን ተጽዕኖ ለመቋቋም
ቆሻሻን በተገቢው መንገድ ጥቅም ላይ በማዋልና የከተማ አረንጓዴ ቦታዎችን በማልማት ጎጂ ተጽኖዎችን መቋቋም
ይቻላል፡፡

የከተማ አረንጓዴ ቦታዎች ለሥነ-ምህዳር አገልግሎት አቅርቦት አስፈላጊ በመሆናቸው የከተማ ውበትን፣ የህብረተሰብ
ጤና እና ደህንነትን ለማሻሻል ትልቅ ሚና አላቸው፡፡

የከተማ መናፈሻዎችም ለነዋሪዎች ቅርበት ባላቸው አካባቢዎች ለምተው ለብዙዎች ተደራሽ እንዲሆኑ በማድረግ
በሰው ልጅ ጤና እና ደህንነት ላይ የሚደርሰውን ጉዳት ለመቀነስ ከፍተኛ ጥቅም አላቸው፡፡

ከመኖሪያ ቤቶች አጠገብ ወይም በዙሪያው ያሉ የግል ቦታዎች በተለያዩ የሣር ሜዳዎች፣ የጌጣጌጥ እና የአትክልት
ቦታዎች ቢሸፈኑ ለነዋሪዎች እፎይታን ከመስጠታቸው ባለፈ የአካባቢን ስነ-ምህዳር ለመቀየር ትልቅ አስተዋጽኦ
አላቸው፡፡

የከተማ ጓሮዎች የተለያዩ የባህልና የአካባቢ አገልግሎቶች እንዳሏቸው ይታወቃል። የአካባቢ አየር ማቀዝቀዣን
ያሻሽላሉ፤ ጎርፍን ለመቀነስ፣ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ለማድረግና ከጭንቀት እረፍትን ለማግኘት የሚያስችል አቅምን
ይፈጥራሉ፡፡ ስለሆነም በከተሞች አካባቢ ያለውን የብዝሃ ህይወት ለመጠበቅ የግል ጓሮዎች እና የከተማ መናፈሻዎች
ንጽህናቸው ተጠብቆ እና ለምተው ለብዙ ሰዎች ትልቅ ስሜታዊና ስነ-ልቦናዊ ፈውስ እንዲያመጡ ማድረግ የሁሉም
የከተማ ነዋሪ ተግባር ሊሆን ይገባል የሚለውን መልዕክታችንን እያስተላለፍን መረጃ ለመስጠት በሚኒስቴር መ /ቤታችን
በከተማ አመራር፣ ፋይናንስና አገልግሎት መሪ ስራ አስፈጻሚ፣ የከተሞች ጽዳትና የአረንጓዴ ልማት ማኔጅመንት ዴስክ
የተዘጋጀውን መረጃ ሰጪ ጽሁፍ እንድታነቡና ተግባራዊ ምላሽ እንድትሰጡ ጋብዘናችኋል፡፡

መልካም ንባብ!

በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የከተማ እና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር


Ministry of Urban & Infrastructure
በከተማ አመራር፣ ፋይናንስና አገልግሎት
መሪ ስራ አስፈጻሚ
የከተሞች ጽዳትና የአረንጓዴ ልማት ማኔጅመንት ዴስክ
ታህሳስ 2015 ዓ.ም

ስልክ / Tel. 011 554-1271


011-554-16-73/74/75
ድህረ-ገጽ/ website www mui.gov.et
E-mail klimat047@gmail.com
ፋክስ/Fax– 011-555-12-68
የፖ.ሳ.ቁ/ POBOX-24134/1000
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ

በከተሞች በመኖሪያ ቤት 20 ሜትር እና በተቋማት 50 ሜ ራዲየስ የጽዳት ሥራ ማስተግበሪያ ጋይድላይን

ክፍል አንድ
መነሻ ሀሳብ

በከተሞቻችን የሚከናወኑ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎች ያለህብረተሰብ እና ተቋማት ተሳትፎ


ውጤታማ መሆን አይችሉም፡፡ በተለይ በደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ ስራ ነዋሪዎችና ተቋማት በምንም
የማይተካ ሚና አላቸው፡፡ በመሆኑም ተቋማትንና ነዋሪዎችን በአጠቃላይ የከተማ ፅዳት ተግባራት እና በ 20/50
ሜትር ራዲየስ የፅዳት ስራ የነቃ ተሳትፎ እንዲያደርጉ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡ ነገር ግን በክትትልና ድጋፍ እና
በጥናት ስራዎቻችን ማረጋገጥ እንደተቻለው በከተሞቻችን በ 20/50 ሜትር ራዲየስ የፅዳት ስራ
የህብረተሰቡና የተቋማት ተሳትፎ በጣም ዝቅተኛ ደረጃ ላይ የሚገኝ ነው፡፡

ክፍል ሁለት

የ 20/50 ሜትር ራዲየስ ፅዳት ፅንሰ ሀሳብ/ምንነት

የ 20/50 ሜትር ራዲየስ የፅዳት ስራ ማለት በከተሞች በደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ ስርዓት ውስጥ
የሚካተት ተግባር ሆኖ ሁሉም መኖሪያ ቤቶች ግቢያቸውንና አካባቢያቸውን እስከ 20 ሜትር ራዲየስ ድረስ፣
ተቋማት ደግሞ ግቢያቸውንና አካባቢያቸውን እስከ 50 ሜትር ራዲየስ ድረስ ፅዱና ውብ የሚያደርጉበት
የአሰራር ስልት ነው፡፡

ስራው በአጠቃላይ በአገር አቀፍ ደረጃ በከተሞቻችን ያለውን የደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ ችግር
ለመቅረፍ ያስችል ዘንድ የተፈጠረ የስትራቴጂክ እቅዶች ማስፈፀሚያ ስልት ሲሆን ሁሉም ነዋሪዎች እና
ተቋማት ግቢያቸውንና አካባቢያቸውን ፅዱና ውብ ካደረጉ ከተሞች በሙሉ ከቆሻሻ የፀዱ፣ ውብ ገፅታ
ያላቸው፣ ለሥራ፣ ለኑሮ፣ ለቱሪዝምና ለኢንቭስትመንት ምቹ ያደርጋቸዋል ከሚል እሳቤ የተነሳ ሀሳብ ነው፡፡

የ 20/50 ሜትር የአካባቢ ፅዳት ስራ የሚደገፍበት የህግ ማዕቀፍ

የከተሞቻችን ነዋሪዎች የውስጥ ግቢያቸውን ከማጽዳት በተጨማሪ ከግቢያቸው ውጪ እስከ 20 ሜትር


ራዲየስ ድረስ፣ ተቋማት ደግሞ እስከ 50 ሜትር አካባቢ ፅዱና ውብ እንዲያደረጉ እና ግዴታቸውን እንዲወጡ
የሚያስችል በአገር አቀፍ ደረጃ የተዘጋጁ የህግ ማዕቀፎችና አሰራሮች አሉ፡፡ በዋናነት የኢትዮጵያ ህገ-
መንግስት፣ የደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ አዋጅ (513/2007)፣ የከተማ ልማት ፖሊሲ እና የከተሞች የደረቅ
ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ ስትራቴጂ ተጠቃሽ ናቸው፡፡ በተጨማሪም ከተሞች እንደየራሳቸው ተጨባጭ ሁኔታ
ያዘጋጁት ለ 20/50 ሜትር ራዲየስ የአካባቢ ፅዳት ትግበራ የሚያግዝ ደንብ፣ መመሪያና የአሰራር ስርዓት
አላቸው፡፡
የማዘጋጃ ቤታዊ ደረቅ ቆሻሻ መልሶ ዑደት ማድረግ/ Recycling

ክፍል አንድ፡ መነሻ ሀሳብ

መግቢያ መልሶ ዑደት የሚደረግ ደረቅ ቆሻሻን በአግባቡ ሳይለይ በሚወገድ ደረቅ ቆሻሻ የሚፈጠረውን ጉዳት
ለመቀነስ ይጠቅማል፡፡

አብዛኛዎቹ የኢትዮጵያ ከተሞች ደረቅ ቆሻሻ በአግባቡ በማስተዳደር፣ በመያዝ እና እንደ ጥሬ እቃ በመጠቀም
ለመልሶ ዑደት በተቀናጀ ሁኔታ እየሰሩ አይደለም፡፡

መልሶ-ዑደት ማድረግ የደረቅ ቆሻሻ መጠን የመቀነስ አቅም አማራጭ በመሆኑ ከ 80-90 በመቶ ከጠቅላላው
የቆሻሻ ይዞታ ይቀንሳል፡፡ መልሰው ዑደት የማይሆኑት ቆሻሻዎች ብቻ ወደ ማስወገጃ ቦታ ይወገዳሉ፡፡

ደረቅ ቆሻሻን መልሶ ዑደት ማድረግ ማለት የአገልግሎት ጊዜውን ጨርሶ አይጠቅመንም ብለን
የምናስወግደውን ቆሻሻ መልሶ በማደስ ወደ ሌላ አዲስ ምርት የመቀየር እና የማምረት ሂደት ነው፡፡

መልሶ ዑደት የማድረግ ጥቅም


(Benefits of recycling)

መልሶ ዑደት ማድረግ የሚለቀቅ የግሪን ሀውስ ጋዝ መጠንን በመቀነስ የዓለም ሙቀት መጨመርን ለመከላከል
መልሶ ዑደት ማድረግ የስራ እድል ከመፍጠሩም በላይ ጠቀሜታ አለው፡፡ በአሜሪካ ያገለገሉ፣ የማይፈለጉ እና
ጊዜ ያለፈባቸው ወይም ያረጁ እቃዎችን በመጠቀም እያንዳንዱን ለመልሶ ዑደት ማድረግ የቀልዝ ስራን
ጨምሮ ይሰራሉ፡፡

መልሶ ኡደት የሚሆን ደረቅ ቆሻሻ ዓይነት

የምግብ ትርፍራፊ፣ ልብስ፣ ወረቀት፣ ብርጭቆ፣ ፕላስቲክ፣ ቦርሳ እና ሻንጣ፣ ብረታ ብረት፤ ወረቀት፣ የታሸጉ
እቃዎች፣ ቆርቆሮ፣ ጠርሙስ ወዘተ.

መልሶ ዑደት የሚሆን የደረቅ ቆሻሻ ዓይነት

መሰብሰብ

መለየት
ወደ አዲስ ምርት
መቀየር
የዕቃውን መለያ ማስወገድ፣
በውኃ ለቅለቅ በማድረግ ማጠብና መቆራረጥ
ማድረቅ

በማንሳፈፍ መለየት

You might also like