Professional Documents
Culture Documents
2013
2013
ቀን፡-09/04/2013
ከሚሴ
ከላይ በርዕሱ ለመግለፅ እንደተሞከረው አቶ እብራሂም አብዱረህማን የተባሉት ባለሀብት በኢንቨስትመንት ፍቃድ
ቁጥር፡- ከ/ከ/አስ/03/30149/20/2007 በቀን 24/05/2007 ዓ.ም በምግብ ዘይት ማቀነባበር ዘርፍ በመሰማራት በከሚሴ
ከተማ 02 ቀበሌ 2500 ካ.ሜ ቦታ ተረክበው በቀጥታ ወደ ስራ በመግባት ግንባታ በመገንባት በመንቀሳቀስ ላይ
መሆናቸው ይታወቃል፡፡
ስለሆነም ባለሀብቱ በምግብ ዘይት ማቀነባበር ወደ ስራ ገብተው እየተንቀሳቀሱ ሲሆን የሚገነቡት ፕሮጀክት በሲሚንቶ
የዋጋ ውድነትና እጥረት የተነሳ በቀጥታ ወደ ግንባታ ለመግባት ተቸግረው ስለነበር ባስቸኳይ ወደ መልሶ ግንባታ መግባት
እንዳለባቸው በተሰጣቸው አቅጣጫ መሰረት እና ለህብረተሰባችን ተገቢውን የስራ አጥነት ችግር ይቀርፉ ዘንድና
ግንባታውንም አጠናቀው ለህብረተሰባችን ተገቢ የሆነ አገልግሎት መስጠት ይችሉ ዘንድ የሲሚንቶ ግብአት እጥረት
ይፈታልኝ ሲሉ በቀን 08/04/2013 ዓ.ም ባመለከቱት ማመልከቻ ጠይቀውናል፡፡ በመሆኑም ፕሮጀክቱ ባሁኑ ሰአት
ከፍተኛ የሲሚንቶ እጥረት ስላጋጠመው የሲሚንቶ ግባአት እጥረት ይፈታለት ዘንድ ከአምባሰል ንግድ ስራወች ድርጅት
ከሚሴ ጣቢያ ትስስር እንዲደረግላቸው ስለሚፈልጉ በ(Spesfication and Bill of Quantities) መሰረት ማድረግና
በተፈቀደለት ኮታ መሰረት 400 ኩ/ል ሲሚንቶ ሽያጭ ትስስር እንዲፈፀምላቻ ስንል ወደ እናንተ የላክን መሆኑን በትህትና
አናሳውቃለን፡፡
ከሰላምታ ጋር
ግልባጭ