You are on page 1of 24

የመሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ

የኢንዱስትሪ ቀጠና (Zone) ልማት ኦፕሬሽናል ማንዋል


(ረቂቅ)

ህዳር 2005 ዓ.ም


ከ/ል/ኮ/ሚ
የፌደራል ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር
MINISTYR OF URBAN DEVELOPMENT AND CONSTRUCTION
የከተማ መሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ
URBAN Land Development and management

ማውጫ
ገጽ
መግቢያ……………………………………………………………………………………….. 1

ክፍል አንድ፡- የኢንዱስትሪ ቀጠና ልማት ቅንጅት እና ክትትል አካል ስለማቋቋም…………. 2


1. የቅንጅት እና ክትትል ኮሚቴው አመራር እና ጥንቅር…………………………………… 2
2. የቅንጅት እና ክትትል ኮሚቴው ተግባር እና ሀላፊነት…………………………………… 3
ክፍል ሁለት፡- ለኢንዱስትሪ ቀጠና የሚውል መሬት መካከል እና ማመልከት……………….3
1. ለኢንዱስትሪ ቀጠና የሚውል ቦታን ስለመከለል………………………………………….. 3
1.1. የመሰረተ ልማት ዝርጋታ ሁኔታ እና የፕላን መርበብ………………………………. 3
1.2. ተገቢ የቦታ ስፋት…………………………………………………………………….. 4
ክፍል ሶስት፡- የኢንድስትሪ ቀጠና ዝርዝር የአካባቢ ልማት ፕላን እና ዲዛይን ስለማዘጋጀት… 5
1. ዝርዝር የመሬት አጠቃቀም ፕላን ማዘጋጀት……………………………………………… 5
2. የኢንዱስትሪ ቀጠና ዝርዝረ የአካባቢ ልማት ፕላን ስለማፅደቅ……………………… ……. 6
3. የኢንዱስትሪ ቀጠና ልማት ዲዛይን ስለማዘጋጀት………………………………………….. 6
3.1. የግንባታ ዲዛይን ዝግጅት……………………………………………………………… 6
3.2. የመሰረተ ልማት ዲዛይን ዝግጅት……………………………………………………… 6
3.3. የአረንጓዴ እና ክፍት ቦታ ዲዛይን ዝግጅት……………………………………………. 7

ክፍል አራት፡- ለኢንዱስትሪ ቀጠና ከተከለለው ቦታ ላይ ተነሺን ማስተናገድ እና


ቦታን ነፃ ማድረግ…………………………………………………………………… 7

ክፍል አምስት፡- የኢንዱስትሪ ቀጠና መሰረተ ልማት ዝርጋታ እና ሽንሻኖ ስለማከናወን………. 7

1. የመሰረተ ልማት ዝርጋታ ስለማከናወን…………………………………………………….. 7


2. የሽንሻኖ እና ቅየሳ ስራ……………………………………………………………………… 8
3. የፓርሴል መለያ ቁጥር መስጠትና ቦታውን መመዝገብ……………………………………. 8
ክፍል ስድስት፡- ግንባታን ማከናወን እና ማከራየት፤ መሬትን በሊዝ አግባብ ማስተላለፍ……… 9
አባሪዎች………………………………………………………………………………………… 10
የኢንዱስትሪ ቀጠና (Zone) ልማት ኦፕሬሽናል ማንዋል

የፌደራል ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር


MINISTYR OF URBAN DEVELOPMENT AND CONSTRUCTION
የከተማ መሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ
URBAN Land Development and management

1. መግቢያ
ሀገራችንን ካለችበት ድህነት በማላቀቅ በ 2015 መካከለኛ ገቢ ካላቸዉ ሀገሮች ተርታ ለማሰለፍ ዘርፈ ብዙ የልማት
እንቅስቃሴዎች በመደረግ ላይ መሆኑ ይታወቃል፡፡ በተለይ ሀገራችንን የኢኮኖሚ ዕድገት እና ልማት ለማፋጠን ከግብርናዉ
ዘርፍ ቀጥሎ የኢንዱስትሪዉን ዘርፍ ማስፋፋት ትልቅ ትኩረት የተሰጠዉ ጉዳይ ነዉ፡፡ ለኢንዱስትሪዉ ዘርፍ ዉጤታማነት
ደግሞ የተደራጀ እና ዘመናዊ የኢንዱስትሪ ቀጣና መስፋፋት የማይተካ ሚና ይኖረዋል፡፡ በኢንዱስትሪ ሚኒስቴር 2004 ዓ.ም
በተዘጋጀዉ የኢንዱስትሪ ቀጣና ልማት ስትራቴጂ ጥናት ሰነድ ላይ እንደተመለከተዉ የኢንዱስትሪ ቀጣና ማለት
የኢንዱስትሪ ስብስብ (cluster of business) እና የተለያዩ ኢንዱስትሪዎች የሚቋቋሙበት እና ልማቱን ለማፋጠን ልዩ ልዩ
ማበረታቻዎች በሕግ አግባብ የሚሰጡበት የተከለለ አካባቢ ወይም ቦታ ሲሆን ይህ ቦታ ሁሉን አቀፍ የሆነ መሠረተ ልማት
አካቶ የተመሰረተ ነዉ፡፡ የኢንዱስትሪ ቀጣና የመንገድ፣ የውኃ፣ የኤሌክትሪክ ኃይል፣ የቴሌኮሙኒኬሽንና ሌሎች መሠረተ
ልማቶች የተገነቡበት ሆኖ የጋራ መገልገያዎች (common facilities)፣ መጋዘን (warehouse)፣ የብክለት ማጣሪያና
ማስወገጃ (effluent treatment) የያዘ ፣ የጥናትና ምርምር ማዕከል፣ የጋዝ ማደያ፣ ወዘተ እንዲሁም የተለያዩ ማኅበራዊ
አገልግሎቶች (መኖሪያ ቤቶች፣ የቢሮ ህንፃዎች፣ የሕክምና ማዕከል፣ ት/ቤት፣ መዋዕለ ህፃናት) ያሉበት የተረጋጋና
የተመቻቸ የሥራ አካባቢ በመፍጠር ሠራተኛው ምርታማ የሚሆንበት፣ ኢንዱስትሪዎቹም የእርስ በርስ ቁርኝት ያላቸውና
እርስ በርስ የሚመጋገቡ እንዲሆኑ ሁኔታዎች የተመቻቹበት ነው፡፡ ከዚህ አንጻር በክልሎች እና በከተሞች በኢንዱስትሪ
ቀጣናነት ተከልለዉ ወደተግባር የገቡትን ስንመለከት ተገቢዉን አገልግሎት መስጠት የማይችሉ እና የኢንዱስትሪ ቀጠና
ማሟላት የሚገባቸዉን መሰረታዊ አቅርቦቶች ሳይቀር የተጓደሉበት ሆኖ እናገኛለን፡፡ በመሆኑም ቀጣናዎቹ የታሰበዉን
ዉጤት ከማምጣት ይልቅ የልማት ሂደቱን በአግባቡ ለማፋጠን የሚያስችሉ አለመሆናቸዉን ለመገንዘብ ይቻላል፡፡ ለዚህ
እንደችግር የሚቀርበዉ የከተሞች የፋይናንስ አቅም ችግር እንደተጠበቀ ሆኖ ዘመናዊ ኢንዱስትሪ ቀጠና ማሟላት
በሚገባቸዉ ጉዳዮች እና በአሰራሩ ላይ ሰፊ የግንዛቤ ክፍተት እንዳለም ለመረዳት ተችሏል፡፡ በእድገት እና ትራንስፎርሜሽን
ዕቅዳችን ላይ በየከተሞች መልማት ያለባቸዉ ወደ 72 የሚጠጉ የኢንዱስትሪ ቀጣናዎች እንዳሉ ተመልክቷል፡፡

የኢንዱስትሪ ቀጠና (Zone) ልማት ኦፕሬሽናል ማንዋል


1
የፌደራል ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር
MINISTYR OF URBAN DEVELOPMENT AND CONSTRUCTION
የከተማ መሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ
URBAN Land Development and management

ከዚህ አንጻር ከተሞች በኢንዱስትሪ ቀጠና ልማት ረገድ ያለባቸዉን ችግር እንዴት መቅረፍ እንዳለባቸዉ እና ዝርዝር
አሰራሩን ለማስጨበጥ የሚያስችል ይህ የኦፕሬሽናል ማኑዋል ተዘጋጅቷል፡፡
ክፍል አንድ፡- የኢንዱስትሪ ቀጠና ልማት ቅንጅት እና ክትትል አካል ስለማቋቋም

1. የቅንጅት እና ክትትል ኮሚቴዉ አመራር እና ጥንቅር


የኢንዱስትሪ ቀጠና ልማት በባህሪዉ የበርካታ አካላትን ተሳትፎ የሚጠይቅ በመሆኑ የእነዚህን አካላት
ተሳትፎ እና ተገቢ የስራ ድርሻ የሚያቀናጅ እና የሚያስተባብር ተገቢዉን ክትትል የሚያደርግ የኢንዱስትሪ
ቀጠና ልማት ቅንጅት እና ክትትል ኮሚቴ መቋቋም የሚገባዉ ይሆናል፡፡ ኮሚቴዉ በከተማ አስተዳደሩ
ወይም በክልሉ ከፍተኛ የፖለቲካ አመራር የሚመራ ይሆናል፡፡ በክልል እና በከተማ አስተዳደር የኮሚቴዉ
አባላት ጥንቅር በመሰረታዊነት የሚከተሉትን የሚያካትት ይሆናል፡-

 የንግድ እና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ


 የከተማ ልማት እና ኮንስትራክሽን ቢሮ
 የፋይናንስ እና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ
 የመሬት ልማት እና ማኔጅመንት ቢሮ
 የገቢዎች እና ጉምሩክ ተቋም
 የፕላን ኢንስቲትዩት/ኮሚሽን/
 የመብራት ኃይል ተወካይ
 የቴሌኮሙኒኬሽን ተወካይ
 የዉሀ እና ፍሳሽ ተወካይ
 የአካባቢ ጥበቃ ቢሮ
 ሌሎች ተገቢ የሆኑ አካላት

የኢንዱስትሪ ቀጠና (Zone) ልማት ኦፕሬሽናል ማንዋል


2
የፌደራል ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር
MINISTYR OF URBAN DEVELOPMENT AND CONSTRUCTION
የከተማ መሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ
URBAN Land Development and management

2. የቅንጅት እና ክትትል ኮሚቴዉ ተግባር እና ሀላፊነት፡-

የኮሚቴዉ ተግባር እና ኃላፊነት በመሰረታዊነት የሚከተሉትን ያካትታል፡-


 የኢንዱስትሪ ቀጠናዉን ዕቅድ መገምገም
 የኢንዱስትሪ ቀጠናዉን የዕቅድ አፈጻጸም መርሐ ግብር እና በጀት አግባብ በመወሰን አፈጻጸሙን
መከታተል
 የኢንዱስትሪ ቀጠናዉ ልማቱን አፈጻጸም በመደበኛ መርሐ ግብር መገምገም እና አቅጣጫ
መስጠት
 በአፈጻጸም ሂደት ለሚያጋጥሙ ችግሮች ተገቢዉን መፍትሄ መስጠት እና አፈጻጸሙን መከታተል

ክፍል ሁለት፡- ለኢንዱስትሪ ቀጠና የሚዉል መሬት መከለል እና ማመልከት


1. ለኢንዱስትሪ ቀጠና የሚዉል ቦታን ስለመከለል

ከተሞች ለኢንዱስትሪ ቀጠና የሚዉል ቦታን ለመከለል ተገቢዉን ጥናት እና ጥንቃቄ ማድረግ የሚኖርባቸዉ
ይሆናል፡፡ ለኢንዱስትሪ ቀጠና ዝግጅት የሚዉለዉን መሬት ለመከለል መዋቅራዊ ፕላኑ ያስቀመጣቸዉ
ታሳቢዎች እንደተጠበቁ ሆኖ የሚከተሉት ዋና ዋና ጉዳዮች መሰረታዊ ናቸዉ፡፡

1.1. የመሰረተ ልማት ዝርጋታ ሁኔታ እና የፕላን መርበብ


የኢንዱስትሪ ቀጠና በርካታ የጥሬ ዕቃ ፣ የወጪ እና ገቢ ምርቶች በስፋት እና በብዛት የሚመላለሱበት
መሆኑ ይታወቃል፡፡ ይህ ሂደት በዋነኛነት ሀገራዊ የትራንስፖርት አዉታርን መሰረት ያደረገ ነዉ፡፡
ሀገራችን የትራንስፖርት ዘርፉን ለማሳደግ በያዘችዉ ሰፊ ዕቅድ ክልልን ከክልል - ከተማን ከከተማ
እንዲሁም ሀገሪቱን ከዉጭዉ ዓለም ጋር ለማስተሳሰር የሚያግዙ የመንገድ፤የባቡር እና የአየር
ትራንስፖርት የዘረጋች እና በዕቅድ ዘመኑም ለመዘርጋት በሂደት ላይ ያሉ አዉታሮች በርካታ ናቸዉ፡፡

የኢንዱስትሪ ቀጠና (Zone) ልማት ኦፕሬሽናል ማንዋል


3
የፌደራል ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር
MINISTYR OF URBAN DEVELOPMENT AND CONSTRUCTION
የከተማ መሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ
URBAN Land Development and management

በመሆኑም ለኢንዱስትሪ ቀጠና የሚዉሉ ቦታዎችን በመከለል ረገድ ለነዚህ አዉታሮች በቀላሉ ተደራሽ
የሆነ ቦታ መምረጥ ተገቢ ይሆናል፡፡ የኢንዱስትሪ ቀጠና በምርት ሂደት እና በአጠቃላይ እንቅስቃሴዉ
ግብአት እና ጠቀሜታ የሚዉል ከፍተኛ የዉሃ ፍጆታን የሚጠይቅ በመሆኑ እና ይህም ፍጆታ በአማካይ
በቀን ለአንድ መለስተኛ ከተማ ከሚቀርበዉ ጋር ተመጣጣኝ በመሆኑ በጥልቅ ጉድጓድ ቁፋሮ የታገዘ
የዉሃ አቅርቦት ሊኖር የሚገባ ይሆናል፡፡ በመሆኑም ለኢንዱስትሪ ቀጠና የሚዉለዉ መሬት ክለላ
በአካባቢዉ ይህንን አቅርቦት ለማግኘት በሚያስችል መልኩ ጥናት በማከናወን መረጋገጥ የሚኖርበት
ይሆናል፡፡

የኢንዱስትሪ ቀጠና በተፈጥሮዉ ከፍተኛ የኃይል አቅርቦት የሚጠይቅ እንደመሆኑ ክለላዉ


የሚከናወንበት ከተማ እና ቦታ ይህን ከፍተኛ የሆነ የኃይል አቅርቦት ለመጥለፍ እና ለመጠቀም
የሚያስችል የኃይል መርበብ እና ቴክኒካል ታሳቢዎችን ያሟላ ሊሆን ይገባል፡፡
የኢንዱስትሪ ቀጠና ዉስጥ የሚንቀሳቀሱ ኢንዱስትሪዎች እና ደጋፊ አገልግሎቶች የኢንቨስትመንት
ተግባሩን ለማቀላጠፍ ሰፊ የሆነ የኮሙኒኬሽን አገልግሎትን የሚጠቀሙ መሆናቸዉ ይታወቃል፡፡
በመሆኑም የኢንዱስትሪ ቀጣናዉ የሚከለልበት ከተማ ለዚህ አገልግሎት ተደራሽ መሆኑ በቅድሚያ
መረጋገጥ ይኖርበታል፡፡

1.2. ተገቢ የቦታ ስፋት


ለኢንዱስትሪ ቀጠና የሚከለለዉ ቦታ በርካታ እንቅስቃሴዎች የሚከናወኑበት እና ተመጋጋቢ እና
ተያያዥ ኢንዱስትሪዎችን በብዛት ለማስፈር እንዲሁም የቀጣናዉን ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ከፍ
ለማድረግ እንዲቻል ዝቅተኛዉ 10 ሄ/ር ሆኖ በቀጣይ ለማስፋፋት የሚያስችል አማራጭ ያለዉ
መሆን ይገባዋል፡፡

የኢንዱስትሪ ቀጠና (Zone) ልማት ኦፕሬሽናል ማንዋል


4
የፌደራል ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር
MINISTYR OF URBAN DEVELOPMENT AND CONSTRUCTION
የከተማ መሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ
URBAN Land Development and management

ክፍል ሶስት፡- የኢንዱስትሪ ቀጠና ዝርዝር የአካባቢ ልማት ፕላን እና ዲዛይን ስለማዘጋጀት
1. ዝርዝር የመሬት አጠቃቀም ፕላን ማዘጋጀት

የኢንዱስትሪ ቀጠና ዝርዝር የልማት ፕላን ዝግጅት ትልቅ አቅምን እና ብቃትን የሚጠይቅ በመሆኑ በክልል
ከተሞች ይህንን ለማዘጋጀት የሚችል አቅም በሂደት እስከሚገነባ ድረስ በክልል የፕላን ተቋማት ወይም ብቁ
በሆኑ የግል አማካሪዎች ወይም ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት አማካይነት ፕላኑን ማስጠናት እንደአማራጭ
ሊታሰብ የሚገባዉ ይሆናል፡፡ የኢንዱስትሪ ቀጠና የፕላን ዝግጅት ታሳቢዎች በቀጠናዉ በመሰረታዊነት
እንዲመረት ከተፈለገዉ ምርት እና የኢንዱስትሪ ትስስር አግባብ የሚነሳ ይሆናል፡፡ በዚህ ረገድ ቀጠናዉ
ለጨርቃ ጨርቅ ወይም ለብረታ ብረት ወይም ለሌሎች ምርቶች በስፔሽያላይዜሽን ወይም በቅይጥ
የሚመረትበት መሆኑ የሚወሰን ይሆናል፡፡ የኢንዱስትሪ ቀጠናዉ ከማምረቻ ኢንዱስትሪዎች በተጨማሪ
የተለያዩ አገልግሎቶችን ማለትም የንግድ ሥራና የሙያ አገልግሎቶች በማካተት ምርቱን ከግብይቱ፣
ኢንዱስትሪውን ከአገልግሎቱ ሰጪው ዘርፍ በማቆራኘት ሁለንተናዊ ልማትን በሚያስገኝ መልኩ የሚዘጋጅ
በመሆኑ የኢንዱስትሪ ቀጠናዎች የገበያ ማዕከሎችን፣ መኖሪያ ቤቶችን፣ መዝናኛ ሥፍራዎችን፣
ሆስፒታሎችንና ትምህርት ቤቶችን የጉምሩክ አገልግሎቶችን፤ የነዳጅ ማደያዎችን፤ የኃይል አቅርቦት ሰብ
ስቴሽኖችን፤ የዉሃ አቅርቦት ማሰራጫ እና ማጠራቀሚያ ስትራክቸሮችን፤ ልዩ ልዩ የአገልግሎት መስጫ
ተቋማትን፤ ከፍተኛ የማከማቻ መጋዘኖችን እና ጋራዦችን ወዘተ ታሳቢ ሊያደርግ ይገባል፡፡ ቀጠናዉ በርካታ
እና ትላልቅ ተሸከርካሪዎች የሚመላለሱበት በመሆኑ ደረጃዉን እና ስፋቱን የጠበቀ የዉስጥ ለዉስጥ መንገድ
እና በቂ መቆሚያ ቦታ እንዲኖረዉ ይጠበቃል፡፡ ቀጠናዉ ተገቢዉ የአካባቢ ደህንነት መጠበቂያ አረንጓዴ
ቦታዎችን፤ የፍሳሽ እና ቆሻሻ፤ የብክለት ማከሚያ እና ማስወገጃ ስትራክቸሮችን ታሳቢ የሚያደርግ ይሆናል፡፡
የኢንዱስትሪ ቀጠና ዝርዝር ፕላን የሽንሻኖ ፕላንን ያካተተ ሆኖ የሽንሻኖዉ ታሳቢዎች በቦታዉ ላይ
ሊተገበር በታቀደዉ የኢንዱስትሪ ዓይነት እና የአገልግሎት ደረጃ እና ይዘት የሚወሰን ይሆናል፡፡

የኢንዱስትሪ ቀጠና (Zone) ልማት ኦፕሬሽናል ማንዋል


5
የፌደራል ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር
MINISTYR OF URBAN DEVELOPMENT AND CONSTRUCTION
የከተማ መሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ
URBAN Land Development and management

በአጠቃላይ የኢንዱስትሪ ቀጠናዉ ዝርዝር የልማት ፕላን ከላይ የተመለከቱትን ታሳቢዎች መሰረት በማድረግ
የሚዘጋጅ እና ሁሉም ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ቀርቦ መዳበር የሚገባዉ ይሆናል፡፡
2. የኢንዱስትሪ ቀጠና ዝርዝር የአካባቢ ልማት ፕላን ስለማጽደቅ
የኢንዱስትሪ ቀጠና ዝርዝር የልማት ፕላን ሁሉም ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ቀርቦ እና ታይቶ
በክልል ወይም በከተማዉ ካቢኔ በኩል የሚጸድቅ ይሆናል፡፡ ፕላኑ አግባብ ላለዉ አካል ቀርቦ ከጸደቀ
በኋላ ህጋዊነቱ የተረጋገጠ ሲሆን ከፕላኑ ጋር የሚጣረስ ተግባር መፈጸም ወይም በፕላኑ መሰረት
አለመፈጸም በህግ አግባብ የሚያስጠይቅ ይሆናል፡፡

3. የኢንዱስትሪ ቀጠና ልማት ዲዛይን ስለማዘጋጀት

የኢንዱስትሪ ቀጠና ልማት ዲዛይን ዝግጅት ዝርዝር የአካባቢ ልማት ፕላኑን ተከትሎ የሚዘጋጅ ይሆናል፡፡
የኢንዱስትሪ ቀጠና ዲዛይን በአማካሪ ተቋም ወይም በራስ ሃይል ወይም በመሰረተ ልማት ዘርጊ ተቋሙ
ወይም በግንባታ ፈጻሚዉ አካል የሚከናወን ሆኖ ዲዛይኑ የሚከተሉትን በዋነኛነት የሚይዝ ይሆናል፡፡

3.1. የግንባታ ዲዛይን ዝግጅት፡-


በኢንዱስትሪ ቀጠናዉ የሰራተኞች የኪራይ መኖሪያ ቤቶች፤ የመዝናኛ ህንጻዎች፤ የትምህርት
እና የጤና ማዕከላት፤ የአገልግሎት መስጫ ተቋማት፤ በኪራይ አግባብ ለአልሚዉ በኪራይ
የሚቀርቡ የማምረቻ ሼዶችን ወዘተ ግንባታዎች ዲዛይን ስታንዳርዱን በጠበቀ መንገድ
መዘጋጀት ይኖርበታል፡፡ የተዘጋጀው ዲዛይን ተገቢዉን ማሟላቱን በማረጋገጥ የሚጸድቅ
ይሆናል፡፡
3.2. የመሰረተ ልማት ዲዛይን ዝግጅት
ዝርዝር የአካባቢ ልማት ፕላኑን እና የሽንሻኖ ፕላኑን መሰረት በማድረግ በኢንዱስትሪ ቀጠናዉ
የሚዘረጋዉ የመሰረተ ልማት ዲዛይን በዘርጊ ተቋሙ ወይም ልማቱን በሚያከናዉነዉ ተቋም
አማካይነት መዘጋጀት ይኖርበታል፡፡
የኢንዱስትሪ ቀጠና (Zone) ልማት ኦፕሬሽናል ማንዋል
6
የፌደራል ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር
MINISTYR OF URBAN DEVELOPMENT AND CONSTRUCTION
የከተማ መሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ
URBAN Land Development and management

በዚሁ መሰረት የኢንዱስትሪ ቀጠናዉ የዉስጥ ለዉስጥ መንገድ፤ የፍሳሽ መዉረጃ እና


ማስወገጃ፤ የዉሃ መስመር እና ተያያዥ ስትራክቸሮች፤ የመብራት መስመር እና ተያያዥ
ስትራክቸሮች ፤ የቴሌፎን መስመር የብክለት መከላከያ እና ማከሚያ ስትራክቸር በአግባቡ
መዘጋጀት እና መጽደቅ የሚኖርበት ይሆናል፡፡

3.3. የአረንጓዴ እና ክፍት ቦታ ዲዛይን ዝግጅት


በኢንዱስትሪ ቀጠናዉ የሚለሙ አረንጓዴ ቦታዎች እና በክፍትነት እንዲቆዩ የሚከለሉ
ቦታዎች ዲዛይን ተዘጋጅቶላቸው ተገቢውን ዉበት እና ደረጃ ሊይዙ ይገባል፡፡ የዲዛይን
ዝግጅቱ እንደተጨባጭ ሁኔታዉ በአልሚዉ ተቋም ወይም በአማካሪ ድርጅት አማካይነት
እንዲዘጋጅ ማድረግ ይቻላል፡፡ ይሁንና ዲዛይኑ በተገቢው ጥራትና ደረጃ በወቅቱ እንዲዘጋጅ
ተገቢውን ክትትልና ድጋፍ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡ በሌላ በኩል የዲዛይን ርክክብ ሲፈጸም
ተገቢውን ጥራት ጠብቆ ስለመሰራቱ መረጋገጥ አለበት፡፡
ክፍል አራት፡- ለኢንዱስትሪ ቀጠና ከተከለለዉ ቦታ ላይ ተነሺን ማስተናገድ እና ቦታን ነጻ ማድረግ
በመሬት ልማት እና ዝግጅት ኦፕሬሽናል ማንዋል ነዋሪን ስለማስተናገድ እና ቦታን ነጻ ማድረግ
ኢንዱስትሪ ዞንን ጨምሮ ለሁሉም ልማቶች ተመሳሳይ በመሆኑ በመሬት ልማት እና ዝግጅት
ኦፕሬሽናል ማንዋሉ መሰረት የሚፈጸም ይሆናል፡፡

ክፍል አምስት፡- የኢንዱስትሪ ቀጠና መሰረተ ልማት ዝርጋታ እና ሽንሻኖ ስለማከናወን


1. የመሰረተ ልማት ዝርጋታ ስለማከናወን
በተዘጋጀዉ እና በጸደቀዉ ዲዛይን መሰረት ከላይ የተመለከቱትን መሰረተ ልማቶች ተገቢዉን ጥያቄ በማቅረብ/
ለምሳሌ፤ ለመብራት፤ ለቴሌኮሙኒኬሽን፤ ለዉሃ ፤ ለፍሳሽ መስመር፤/ በተቋማቱ አማካይነት፤ መንገድ፤
የብክለት ማስወገጃ እና ማከሚያ ስትራክቸሮችን በግል

የኢንዱስትሪ ቀጠና (Zone) ልማት ኦፕሬሽናል ማንዋል


7
የፌደራል ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር
MINISTYR OF URBAN DEVELOPMENT AND CONSTRUCTION
የከተማ መሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ
URBAN Land Development and management
ኮንትራክተሮች አማካይነት የሚዘረጋ ይሆናል፡፡የኢንዱስትሪ ቀጠናዉን በባለቤትነት የሚመራዉ ተቋም
ዝርጋታዉን ከሚያከናዉን አካል ጋር በፋይናንስ ህግ መሰረት ዉል መፈጸም እና ስራዉን ማስጀመር ተገቢ
ይሆናል፡፡ የመሰረተ ልማት ዝርጋታ ሂደቱን በአግባቡ መከታተል እና ተገቢዉ መሟላቱን በማረጋገጥ ርክክብ
የሚፈጸም ይሆናል፡፡

2. የሽንሻኖ እና ቅየሳ ስራ

የሽንሻኖ ፕላኑን መሰረት በማድረግ የኢንዱስትሪ ቀጠናዉ በሚገባ ተቀይሶ በስታንዳርዱ መሰረት የሚሸነሸን
ይሆናል፡፡ ስታንዳርድ የኢንዱስትሪ ቀጠና ሽንሻኖ በእዝል 3 ተመልክቷል፡፡ በፕላኑ መሰረት ልኬት ተከናዉኖ
በተሸነሸነዉ ቦታ ላይ የወሰን ድንጋይ መትከል ተገቢ ይሆናል፡፡ ለዚህ ስራ ደግሞ አንዱ ግብዓት የወሰን
ድንጋይ ወይም ችካል ሲሆን ይህም የቅየሳ ስራ ከመከናወኑ በፊት አስቀድሞ መዘጋጀት ይኖርበታል፡፡
የሚተከለውም የወሰን ድንጋይ አራት ማእዘን ያለው ሆኖ የተለየና ጎላ ብሎ የሚታይ አተካከሉ በቀላሉ ሊነቀል
በማይችል መልኩ እንደ አፈሩ ፀባይ በጥልቀት መተከል የሚገባው ሲሆን በተጨማሪም ፕሎቶቹን በቀላሉ
ለመለየት እንዲቻል የወሰን ድንጋዩ ኮድ እና ኮኦርድኔት ቁጥር ሊሰጠው ይገባል፡፡ በሽን ሸናው መሰረት የወሰን
ድንጋይ ከተተከለ በኋላ ቦታው በአግባቡ ስለመሸንሸኑ የሚያስረዳ የመስክ ሪፖርትና የርክክብ ፎርማት
ተዘጋጅቶና ተፈርሞ ለሚመለከተው አካል መቅረብ አለበት፡፡

3. የፓርሴል መለያ ቁጥር መስጠትና ቦታውን መመዝገብ

በቦታው ላይ በዝርዝር የሽንሻኖ ፕላኑ መሰረት የወሰን ድንጋይ ከተተከለ በኋላ ዝርዝር የሽንሻኖ ፕላኑ ላይ
ለእያንዳንዱ ፓርሴል መለያ ቁጥር በመስጠት በመሬት ባንክ እንዲመዘገብ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡ እያንዳንዱ
ፓርሴል የሚሰጠው መለያ ቁጥር ከሌላው የተለየ እና የራሱ ብቻ የሆነ (Unique) መሆን አለበት፡፡ ይህ ቁጥር
በተለይ በቀጣይ በየከተሞቹ ለሚዘረጋው የመሬት እና መሬት ነክ ቋሚ ንብረት ምዝገባ የሚያገለግል ስለሚሆን
ተገቢውን የኮድ አሰጣጥ ፎርማት ተከትሎና አንዱን ፓርሴል ከሌላው ፓርሴል/ፕሎት ለመለየት በሚያስችል
መልኩ መከናወን አለበት፡፡

የኢንዱስትሪ ቀጠና (Zone) ልማት ኦፕሬሽናል ማንዋል


8
የፌደራል ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር
MINISTYR OF URBAN DEVELOPMENT AND CONSTRUCTION
የከተማ መሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ
URBAN Land Development and management

የመለያ ቁጥር አሰጣጡ ወጥነት እንዲኖረው ለማድረግ ከተሞች እስካሁን እየሰሩበት የነበረውን የኮድ አሰጣጥ
መፈተሽና ከላይ ለተገለጸው የቋሚ ንብረት ምዝገባ አገልግሎት ጭምር የሚጠቅም የፓርሴል መለያ ቁጥር
አሰጣጥ ስርዓት የሚዘረጋበትን መንገድ መቀየስ አለባቸው፡፡
ክፍል ስድስት፡- ግንባታን ማከናወን እና ማከራየት፤ መሬትን በሊዝ አግባብ ማስተላለፍ

በኢንዱስትሪ ቀጠናዉ ዉስጥ በአልሚዉ በኩል ከሚገነቡ ተቋማት እና ህንጻዎች በስተቀር በክልሉ ወይም
በከተማዉ አስተዳደር ለአገልግሎት መስጫነት ወይም በኪራይ አግባብ አገልግሎት የሚሰጡ ግንባታዎች
በዲዛይኑ መሰረት መዘጋጀት እና መጠናቀቅ የሚኖርባቸዉ ይሆናል፡፡ በተለይ በኢንዱስትሪ ቀጠናዉ መሰረታዊ
አገልግሎት የሚሰጡ እንደመኖሪያ ቤት፤ ት/ቤት፤ የጤና ተቋማት፤ መዝናኛ ማዕከላት፤ የነዳጅ ማደያ
የመሳሰሉት አቅርቦቶችን በግል አልሚ በኩል የሚቀርብበትን አግባብ ማመቻቸትም እንደአማራጭ የሚታይ
ይሆናል፡፡ ለማምረቻ ማዕከላት የሚሆኑ ሼዶችን እና መጋዘኖችን እና ጋራዦችንም እንደተጨባጭ ሁኔታዉ
በግል አልሚ አማካይነት እንዲለማ እና ለቀጠናዉ አገልግሎት እንዲሰጥ ማድረግ ተመራጭ ሊሆን ይችላል፡፡
ግንባታዉ በክልሉ ወይም በከተማዉ የሚከናወን ሲሆን የኪራይ ዋጋዉን በመወሰን አልሚዉ እንዲገለገልበት
ማድረግ ተገቢ ይሆናል፡፡

ከግንባታ ዉጪ የሆኑ የተሸነሸኑት የኢንዱስትሪ ቀጠና ቦታዎች በሊዝ አዋጁ አግባብ የሚተላለፉ ይሆናል፡፡
የይዞታ አስተዳደሩም ይህንኑ ህግ መሰረት ያደረገ ይሆናል፡፡ ዝርዝር አሰራሩ በሊዝ ኦፕሬሽናል ማንዋል ላይ
ተመልክቷል፡

የኢንዱስትሪ ቀጠና (Zone) ልማት ኦፕሬሽናል ማንዋል


9
የፌደራል ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር
MINISTYR OF URBAN DEVELOPMENT AND CONSTRUCTION
የከተማ መሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ
URBAN Land Development and management

አባሪዎች

አባሪ 1 ፡- የኢንዱስትሪ ቦታ የሊዝ ባለይዞታነት ማቋቋሚያ ውል

ቀን፡ --------------------

የ-------------------- ከተማ ከተማ አስተዳደር

የኢንዱስትሪ ቦታ የሊዝ ባለይዞታነት ማቋቋሚያ ውል


የከተማ ቦታ በሊዝ እንዲያዝ በወጣው አዋጅ ቁጥር 721/2004 እና በ------------- ብሄራዊ ክልላዊ መንግሥት ም/ቤት
የሊዝ ባለይዞታነት ማስተዳደሪያ ደንብ ቁጥር ------------------ መሠረት የተጻፈ የሊዝ ውል፡፡

በ……….……… ከተማ ማዘጋጃ ቤት (ከዚህ በኋላ ውል ሰጪ) እና በሊዝ ባለይዞታነት መብት ባለቤት
አቶ/ወ/ሮ/ድርጅት ……………………………. (ከዚህ በኋላ ውል ተቀባይ) መካከል የጋራ መግባባትና ጥቅምን
መሠረት ያደረገ የውል ስምምነት ተፈጽሟል፡፡

አንቀጽ 1 የውል ሰጪና የውል ተቀባይ አድራሻ

ውል ሰጪ፡

ከተማ ……………..ክ/ከተማ………………. ፖ.ሣ.ቁ. ………….. ስልክ ቁጥር ……….

ውል ተቀባይ፡

ከተማ ………………ክ/ከተማ…………. ፖ.ሣ.ቁ. ……………… ስልክ ቁጥር ……………


ወረዳ ……………. ቀበሌ ……………… የቤት ቁጥር ……………

አንቀጽ 2 ውል ስለማቋቋም
ይህ ውል በውል ሰጪና በውል ተቀባይ ነፃ ፍላጐት፤ ውል ሰጪ በዚህ ውል የተጠቀሰውን የከተማ ቦታ ለኢንዱስትሪ
አገልግሎት ይዞታ በውሉ ለተወሰነው ጊዜ ለውል ተቀባይ በሊዝ ባለይዞታነት

የኢንዱስትሪ ቀጠና (Zone) ልማት ኦፕሬሽናል ማንዋል


10
የፌደራል ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር
MINISTYR OF URBAN DEVELOPMENT AND CONSTRUCTION
የከተማ መሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ
URBAN Land Development and management

ሊያስተላልፍና ውል ተቀባይም ከውል ሰጪ የተረከበውን ቦታ ይዞታ በዚሁ ውል በተመለከተው የጊዜ ገደብ ውስጥ
ለተፈቀደው አገልግሎት ዓይነት ብቻ በዚህ ውል የተጠቀሰውን ዋጋ ከፍሎ በመውሰድ ሊገለገሉበት ፈቅደውና ወደው
ያቋቋሙት ውል ነው፡፡

አንቀጽ 3 የቦታው ዝርዝር ሁኔታ

3.1 በሊዝ የሚያዘው ቦታ አድራሻ፡-

በ…………………….ዞን መስተዳድር በ……………………ክ/ከተማ በ………………ወረዳ


በ……………………ከተማ በ……………………ቀበሌ የሚገኝ ለኢንዱስትሪ የሚያገለግል ቦታ ነው፡፡

3.2 በሊዝ የሚያዘው ቦታ አዋሳኞች፡-


በሰሜን……………….. በደቡብ……………….. በምሥራቅ……………. በምዕራብ…………….

3.3 የቦታው X እና Y አቅራቢያ ኮኦርዲኔቶች ………………………….

3.4 በሊዝ የሚያዘው ቦታ በ ……………………… ቁጥር የተመዘገበ ለኢንዱስትሪ አገልግሎት የሚዉል ቦታ ነው፡፡

3.5 በሊዝ የሚያዘው ቦታ ለ ………………….. አገልግሎት ብቻ ይውላል፡፡

3.6 በሊዝ የሚያዘው ቦታ ጠቅላላ ስፋት ……………………… ሜትር ካሬ ነው፡፡

3.7 የሕንፃው ከፍታ ባለ ……………… ፎቅ ነው፡፡

3.8 ከፍተኛ የግንባታው ወለል/ግቢ ስፋት ንፅፅር መቶኛ ……………(……%) ነው፡፡

3.9 በሊዝ የሚያዘው ቦታ …………………የቦታ ደረጃና ……….. ንዑስ የቦታ ደረጃ ያለው ነው፡፡

የኢንዱስትሪ ቀጠና (Zone) ልማት ኦፕሬሽናል ማንዋል


11

የፌደራል ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር


MINISTYR OF URBAN DEVELOPMENT AND CONSTRUCTION
የከተማ መሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ
URBAN Land Development and management

አንቀጽ 4 ስለ ሊዝ ዋጋ መጠንና አከፋፈል

4.1 በሊዝ የሚያዘው ቦታ ጠቅላላ ዋጋ በብር ……………../በፊደል ……………………. ብር/ ነው፡፡

4.2 ውል ተቀባይ እንዲከፍሉ የተስማሙበት የቅድሚያ ክፍያ በካርኒ ቁጥር ………………………… . በተመዘገበ
ሰነድ በብር ………………/በፊደል፡ …………………………………..……./ብር ተከፍሏል፡፡

4.3 ውል ተቀባይ የቦታውን ጠቅላላ የሊዝ ዋጋ ክፍያ ሊከፍሉ በተስማሙበት የክፍያ ዘመን ውስጥ ለማጠናቀቅ
ግዴታ ገብተዋል፡፡

4.4 በዚህ ሰነድ አንቀጽ 7.5 የተጠቀሰው እንደተጠበቀ ሆኖ ውል የተገባበት የአንድ ሜትር ካሬ የሊዝ ዋጋ በብር
………. / በፊደል ………………………………….. ብር/ ለውል ዘመኑ ሁሉ የፀና ይሆናል፡፡

4.5 ውሉ ሲታደስ የሊዝ ዋጋው በሚታደስበት ወቅት ባለው ዋጋ ይሆናል፡፡

አንቀጽ 5 የችሮታ ጊዜ
5.1 ውል ተቀባይ በሊዝ አዋጅ 721/2004 አንቀጽ 15 እና በክልሉ/ከተማ አስተዳደሩ ደንብ ቁጥር….. አንቀጽ………
መሠረት ለ…… ዓመት የሚቆይ የክፍያ/የግንባታ/ ሌላ የችሮታ ጊዜ ተፈቅዶላቸዋል፡፡
አንቀጽ 6 የውል ዘመን

6.1 ውል ተቀባይ የተስማማበት ወይም በሊዝ አዋጁ አንቀጽ 18 ንኡስ አንቀጽ 1 (ለ/2) እና (ሐ/2) በአዲስ አበባ
ከተማ 70 ዓመት እና በሌሎች ከተሞች 80. ዓመት የውል ዘመኑ ጣሪያ ይሆናል፡፡

6.1 በዚህ ውል መሠረት የሊዝ ዘመኑ የሚጀምረው ከ…….ቀን ……..ዓ.ም. ጀምሮ እስከ …….ቀን ……….ዓ.ም.
ድረስ ይሆናል፡፡

6.1 በአዋጁ አንቀጽ 19 ንኡስ አንቀጽ 2 መሠረት የሊዝ ውል ዘመኑ ከማብቃቱ ከ 10 እስከ 2 ዓመታት ውስጥ ውል
ተቀባዩ የውል ዘመኑ እንዲታደስለት ማመልከት ይችላል፡፡

የኢንዱስትሪ ቀጠና (Zone) ልማት ኦፕሬሽናል ማንዋል


12
የፌደራል ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር
MINISTYR OF URBAN DEVELOPMENT AND CONSTRUCTION
የከተማ መሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ
URBAN Land Development and management

አንቀጽ 7 የውል ተቀባዩ መብቶች

7.1 በሊዝ የያዘውን ቦታ በሊዝ ዘመኑ ውስጥ ያለገደብ ለማስተላለፍ፣ በዋስትና ለማስያዝ ወይም የከፈለውን የሊዝ
ዋጋ በካፒታል አስተዋጽኦ መልክ የመጠቀም መብቶች ይኖሩታል፡፡

7.2 በሊዝ አዋጁ አንቀጽ 25 ንኡስ አንቀጽ 1(ለ) መሠረት ውሉ ሲቋረጥ በዚሁ አዋጅ አንቀጽ 25 ንኡስ አንቀጽ 4
መሠረት ተገቢውን ካሣ ያገኛል፡፡

አንቀጽ 8 የውል ሰጪው ግዴታዎች

8.1 ውል ሰጪ የውል ተቀባይን መብቶች የማክበር ግዴታ አለበት፡፡

8.2 ይህ ውል እንደተፈረመ ውል ሰጪ ለውል ተቀባይ የሊዝ ይዞታ የምስክር ወረቀት ወዲያውኑ የመስጠት ግዴታ
አለበት፡፡

8.3 ውል ሰጪ ውል ተቀባይ ለሚሠራው ልማት የግንባታ ፈቃድ መስጠት አለበት፡፡

8.4 ውል ሰጪ ውል ተቀባይ በውሉ መሠረት እየሠራ መሆኑን መከታተልና ከውል ውጭ የሆነ ጉዳይ ሲያጋጥም
በወቅቱ እንዲታረም የማድረግ ግዴታ አለበት፡፡ በውል ሰጪ የክትትል ማነስ ውል ተቀባይ ከውል ውጭ ሠርቶ
ከተገኘ ወይም ይህ ጉዳይ ውል መቋረጥ ካስከተለ ውል ሰጪ በኃላፊነት ይጠየቃል፡፡

አንቀጽ 9 በሊዝ ስለተያዘው የከተማ ቦታ አጠቃቀም

9.1 በሊዝ አዋጁ አንቀጽ 21(1) መሠረት ውል ተቀባይ ቦታውን ለተፈቀደለት አገልግሎት ብቻ የማዋል ግዴታ
አለበት፡፡
9.2 በሊዝ ደንቡ አንቀጽ ……… መሠረት ውል ተቀባይ በ……… ወራት የጊዜ ገደብ ውስጥ ግንባታ የመጀመር
ግዴታ አለበት፡፡

9.3 በሊዝ አዋጁ አንቀጽ 21(2) መሠረት የከተማ አስተዳደሩ በጽሑፍ ካልፈቀደ በስተቀር ውል ተቀባይ የቦታውን
አጠቃቀም/አገልግሎት መቀየር አይችልም፡፡

የኢንዱስትሪ ቀጠና (Zone) ልማት ኦፕሬሽናል ማንዋል


13
የፌደራል ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር
MINISTYR OF URBAN DEVELOPMENT AND CONSTRUCTION
የከተማ መሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ
URBAN Land Development and management

9.4 ውል ተቀባይ የተፈቀደለትን ኘላን መቀየር ቢፈልግ የተቀየረውን ኘላን አቅርቦ ማፀደቅና የበፊቱን መመለስ
ይኖርበታል፡፡

9.5 የከተማ ቦታ አጠቃቀም ሲቀየር የሊዝ ዘመኑ እንደ አገልግሎት ዓይነቱ የሚቀየር ሲሆን ዋጋው ከፍ ያለ ከሆነ ውል
ተቀባዩ ልዩነቱን የመክፈል ግዴታ አለበት፡፡

አንቀጽ 10 የመሬት አጠቃቀም

10.1 ውል ሰጪ ውል ተቀባይ በገባው ግዴታ መሠረት በመሬቱ መጠቀሙን መቆጣጠር አለበት፡፡

10.2 የውል ተቀባይ የልማት እንቅስቃሴና የመሬት አጠቃቀሙ ሥራ ላይ ባለው ሕግና ተመሳሳይ የመሬት
አጠቃቀምን በሚመለከቱ መመሪያዎች ይገዛል፡፡

10.3 ውል ተቀባይ ባቀረበውና በጸደቀለት የሕንጻ ፕላን መሠረት ግንባታ መጀመር ይኖርበታል፡፡

10.4 የመሬት ውስጥ ሃብት፣ የተቀበሩ የመሠረተ ልማትና የአገልግሎት አውታሮች የመሬት የመጠቀም መብት ጋር
አይገናኙም፡፡

10.5 ውል ተቀባይ የከተማው አስተዳደር/ማዘጋጃ ቤቱ ከልሎ ካስረከበው ድንበር/ወሰን ውጪ በራሱ ፍላጎት


መለወጥ/ማስፋት አይችልም፡፡ የድንበር አጥር/ምልክት ሲፈርስ መልሶ ለመሥራት ውል ተቀባይ አግባብ ላለው
አካል በጽሁፍ በማመልከት ፈቃድ መጠየቅ ይጠበቅበታል፡፡

10.6 በይዞታው ውስጥ አካባቢን ሊበክል የሚችል መርዛማ ነገሮችን ማከማቸት አይችልም፡፡

10.7 ግንባታዎች በተፈቀደላቸው የጊዜ ገደብ ውስጥ መጀመራቸውን ውል ሰጪው በመቆጣጠር ውሉ እንዲቀጥል
ወይም በሊዝ አዋጁ አንቀጽ 25 (1/ሀ እና ሐ) መሠረት እንዲቋረጥ ያደርጋል፡፡

10.8 ማንኛውም ግንባታ በተፈቀደለት አገልግሎት መሠረት ግልጋሎት መስጠቱን ውል ሰጪው ይቆጣጠራል፣
የኢንዱስትሪ ቀጠና (Zone) ልማት ኦፕሬሽናል ማንዋል
14

የፌደራል ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር


MINISTYR OF URBAN DEVELOPMENT AND CONSTRUCTION
የከተማ መሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ
URBAN Land Development and management

አንቀጽ 11 ውል የሚቋረጥባቸው ምክንያቶች


11.1 ውል እንዲፈርስ ሁለቱም ወገኖች ሲስማሙ፡፡

11.2 ውል ተቀባይ ግዴታውን ካልተወጣ፡፡

11.3 በሊዝ አዋጁ አንቀጽ 21/1 በተዘረዘሩት ምክንያቶች፡፡

አንቀጽ 12 የውል መቋረጥ ውጤት

12.1 ውል የተቋረጠው በዚህ ውል አንቀጽ 11/11.3 እና በሊዝ አዋጁ አንቀጽ 21/1 ሀ እና ሐ መሠረት የሆነ እንደሆነ
ውል ተቀባዩ ያሰፈረውን ንብረት በ 6 ወር ጊዜ ውስጥ በማንሳት ቦታውን ለውል ሰጪ የማስረከብ ግዴታ አለበት፡፡

12.2 ውል የተቋረጠው በሊዝ ደንቡ አንቀጽ……/……. መሠረት ከሆነ በአዋጁ አንቀጽ 21/3 መሠረት ውል ተቀባዩ
ተገቢውን የካሳ ክፍያ ያገኛል፡፡

12.3 ውሉ የተቋረጠው በሊዝ ደንቡ አንቀጽ …./…….. ከሆነ በደንቡ አንቀጽ …./…... መሠረት ተገቢው ወጪና
መቀጫ ተቀንሶ የሊዝ ክፍያው ለውል ተቀባይ ተመላሽ ይሆናል፡፡

12.4 ውሉ የተቋረጠው በሊዝ ደንቡ አንቀጽ …./…. የሆነ እንደሆነና ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት መቋረጡ
ከተረጋገጠ ውል ተቀባዩ መቀጫ አይኖርበትም፡፡

አንቀጽ 13 የውሉ ህጋዊ ውጤት

ይህ ውል በሁለቱም ተዋዋይ ወገኖች ከተፈረመ በኋላ ለ ………….. ዓመት የፀና ይሆናል፡፡

እኔ ……………………………… ስለ ……………… ከተማ ማዘጋጃ ቤት እና እኔ


…………………………….. ሊዝ ተቀባይ የውሉን ጠቅላላ ይዘት በአግባቡ መርምረን በመገንዘብ በውሉ መሠረት
መብታችንን ስናስከብር ግዴታችንን ለመፈፀም በፈቃዳችን ተስማምተን በፊርማችን አጽድቀናል፡፡
………………………….. ……………………….
የውል ሰጪ ፊርማ የውል ተቀባይ ፊርማ
የኢንዱስትሪ ቀጠና (Zone) ልማት ኦፕሬሽናል ማንዋል
15
የፌደራል ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር
MINISTYR OF URBAN DEVELOPMENT AND CONSTRUCTION
የከተማ መሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ
URBAN Land Development and management

አባሪ-2 ፡ የሊዝ ይዞታ ምስክር ወረቀት


የ………………………………. ከተማ አስተዳደር
የኢንዱስትሪ አገልግሎት የሚዉል ቦታ የሊዝ ይዞታ ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት
የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የከተማ ቦታን በሊዝ ስለመያዝ ባወጣው አዋጅ ቁጥር 721/2004
እንዲሁም የ…………. ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ምክር ቤት የከተማን ቦታ በሊዝ ለማስተዳደር ባወጣው ደንብ
ቁጥር ---/------- ዓ.ም. አንቀጽ …. መሠረት በ …… ቁጥር የተመዘገበውና በዚህ ገጽ መጠኑ በግልጽ የተመለከተውን
የከተማ ቦታ አቶ/ወ/ሮ/ድርጅት…………..….. በሊዝ ለመያዝ በውል ቁጥር …………. በመዋዋላቸው ይህ የሊዝ
ይዞታ ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት ተሰጥቷቸዋል፡፡

የቦታው አቀማመጥ የፊት ገጽ

የካርታ ቁጥር ………………


የተሰጠበት ቀን

ሰ ሚዛን ……………
……………..

[የካርታ ቦታ]

የኢንዱስትሪ ቀጠና (Zone) ልማት ኦፕሬሽናል ማንዋል


16
የፌደራል ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር
MINISTYR OF URBAN DEVELOPMENT AND CONSTRUCTION
የከተማ መሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ
URBAN Land Development and management
ቦታው የሚገኝበት የቦታው የቦታ ስፋት የሚሰጠው የሊዝ ዘመን የቦታው የሊዝ
ወረዳ ቀበሌ ደረጃ አገልግሎት ጠቅላላ ዋጋ

…………………….. …………………..… ……………………..


የማ/ቤቱ ኃላፊ የ……………………. የ…………………….
………… ኃላፊ …………… ኃላፊ

የሊዝ ባለይዞታ መብቶችና ግዴታዎች


1. የሊዝ መብቶች
በሊዝ አዋጁ መሰረት ማንኛውም ቦታ በሊዝ የወሰደ ሰው የሚከተሉት መብቶች ይኖሩታል፡-
ሀ. በሊዝ የመጠቀም መብትን ለሌላ ወገን ማስተላለፍ ይችላል፤
ለ. የሊዝ ቦታን በዋስትና ማስያዝ ይችላል፡- ይኸውም በመሬት የመጠቀም መብት በዋስትና ሲያዝ መሬቱ ላይ
የተገነባው ሕንጻና ከሕንጻው ጋር የተያያዙ መገልገያዎች አብረው ይያዛሉ፡፡ እንዲሁም በሌላ አኳኋን ካልተወሰነ
በስተቀር ሕንጻውና መገልገያዎቹ በዋስትና ሲያዙ በመሬት የመጠቀም መብቱም አብሮ ይያዛል፡፡
ሐ. ለሊዝ የከፈለውን ዋጋ እንደካፒታል አስተዋጽኦ ማስመዝገብ/መጠቀም ይችላል፡፡
2. ግዴታዎች
ሀ. ማንኛውም የኢንዱስትሪ አገልግሎት የሚዉል ቦታ በሊዝ የተፈቀደለት ሰው በሊዝ አዋጅ 721/2004፣ ክልሉ/ከተማ
መስተዳድር በሚወጣ የሊዝ ደንብና መመሪያዎች ያሉ ግዴታዎችን መወጣት ይገባዋል፡፡

ለ. ማንኛውም የሊዝ ባለመብት ከመዘጋጃ ቤት ጋር ለፈረመው የሊዝ ውል ተገዥ ይሆናል፡፡


3. የሊዝ ባለይዞታነት መብትን ሊያሳጡ የሚችሉ ምክንያቶች
ሀ. ባለይዞታው በሊዝ አዋጁ አንቀጽ 21 ን/አንቀጽ 1 መሰረት ቦታውን በተዋዋሉበት የጊዜ ገደብ ውስጥ ጥቅም ላይ
ካላዋለ፤
ለ. ቦታው ለሕዝብ ጥቅም ተብሎ ለሌላ ሥራ /አገልግሎት እንዲውል ሲወሰን፣ ወይም
ሐ. የሊዝ ይዞታ ዘመኑ በአዋጁ መሠረት ካልታደሰ የሊዝ ይዞታ ሊቋረጥ ይችላል፡፡

የኢንዱስትሪ ቀጠና (Zone) ልማት ኦፕሬሽናል ማንዋል


17
የፌደራል ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር
MINISTYR OF URBAN DEVELOPMENT AND CONSTRUCTION
የከተማ መሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ
URBAN Land Development and management

አባሪ-3 ፡ በኢንዱስትሪ ቀጠና ውስጥ የሚከናወን ሽንሻኖ ስታንዳርድ


1. ኢንዱስትሪና ወርክሾፕ
ጠ/የወለል ስፋት የሚያስፈልገው የቦታ ስፋት (ሜ/ካሬ)
የህንፃው ህንፃው የህንፃው
ተ.ቁ.
አገልግሎት የሚያርፍበት የወለል ከፍታ
ደረጃ 1 ደረጃ 2 ደረጃ 3 ደረጃ 4 ደረጃ 5
ስፋት
1 C1,C2, 2 ዐዐ G+0 _ _ _ 200- 400-
D1,D2, 2 ዐዐ 500 660
D3,D4,
2 C1,C2, 4 ዐዐ G+1 _ 200- 270- 400- 660
D1,D2, 2 ዐዐ 330 400 500
D3,D4,
3 C1,C2, 10 ዐዐ G+4 330 330 400 500 660
D1,D2, 2 ዐዐ
D3,D4,
4 C1,C2, 15 ዐዐ G+2 500- 750- 1000 1250 1650
D1,D2, 500 825 825
D3,D4,
5 C1,C2, 2500 G+4 825 825- 1000- 1250 1650
D1,D2, 500 1000 1650
D3,D4,
6 C1,C2, 700 G+0 _ _ _ 700- 1400-
D1,D2, 700 1750 2320
D3,D4,

የኢንዱስትሪ ቀጠና (Zone) ልማት ኦፕሬሽናል ማንዋል


18
የፌደራል ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር
MINISTYR OF URBAN DEVELOPMENT AND CONSTRUCTION
የከተማ መሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ
URBAN Land Development and management

7 C1,C2, 21 ዐዐ G+2 700- 1400 1750- 2100-


D1,D2, 7 ዐዐ 1650 2100 2320
D3,D4,
8 C1,C2, 35 ዐዐ G+4 1650 1650 1400 1750- 2320
D1,D2, 7 ዐዐ 3500
D3,D4,
9 C1,C2, 10 ዐዐ G+0 _ _ 660- 1000- 3320
D1,D2, 10 ዐዐ 1650 2500
D3,D4,
1ዐ C1,C2, 50 ዐዐ G+4 1650 1650 2000 2500 3320
D1,D2, 10 ዐዐ
D3,D4,

መፍቻ
C1፡ ለኤግዚብሽን አዳራሽ
C2 ፡ ለሙዚየም
D1፡ ለትላልቅ ኢንዱስትሪ
D2፡ ለመካከለኛ ኢንዱስትሪ
D3፡ ለትናንሽ ኢንዱስትሪ
D4 ፡ በግንባታ ግዜ ለሚሠሩ ጊዜያዊ መጋዘኖች
ማብራሪያ፡ ሠንጠረዡ እንደሚያሳየው በ G+0 ሌቭል ለኢንዱስትሪና ወርክሾፕ የሚውል ቦታ እስከ ደረጃ
አራት እንደማይዘጋጅና በ G+1 ሌቭልም ቢሆን በደረጃ አንድ እንደማይዘጋጅ ያሳያል፡፡

የኢንዱስትሪ ቀጠና (Zone) ልማት ኦፕሬሽናል ማንዋል


19
የፌደራል ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር
MINISTYR OF URBAN DEVELOPMENT AND CONSTRUCTION
የከተማ መሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ
URBAN Land Development and management

2. ለቢሮዎችና ለንግድ ማዕከላት

ጠ/የወለል ስፋት የሚያስፈልገው የቦታ ስፋት (ሜ/ካሬ)


የህንፃው ህንፃው የህንፃው
ተ.ቁ.
አገልግሎት የሚያርፍበት ከፍታ ደረጃ 1 ደረጃ 2 ደረጃ 3 ደረጃ 4 ደረጃ 5
የወለል ስፋት
G1,B1, 1 ዐዐ
1 G+0 _ _ _ 100-250 200-325
B2,B3,
1 ዐዐ
G1,B1, 200
2 G+0 _ _ _ 200-500 400-651
B2,B3,, 2 ዐዐ
G1,B1, 300 600-
3 G+0 _ _ _ 300-750
B2,B3,, 3 ዐዐ 1000

G1,B1, 400 400- 800-


4 G+0 _ _ _
B2,B3,, 400 1000 1325

G1,B1, 500 500- 1000-


5 G+0 _ _ _
B2,B3,, 500 1250 1650

G1,B1, 300
6 G+2 120-125 150-162 200 250 325
B2,B3,, 100
G1,B1, 10 ዐዐ
7 G+4 250 325 325 500 500
B2,B3,, 2 ዐዐ
G1,B1, 21 ዐዐ
8 G+6 375 500 600 750 1000
B2,B3,, 3 ዐዐ
G1,B1, 36 ዐዐ
9 G+8 500 651 800 1000 1325
B2,B3,, 4 ዐዐ
G1,B1,
1ዐ 55 ዐዐ G+10 625 625 1000 1250 1250
B2,B3,,

የኢንዱስትሪ ቀጠና (Zone) ልማት ኦፕሬሽናል ማንዋል


20

የፌደራል ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር


MINISTYR OF URBAN DEVELOPMENT AND CONSTRUCTION
የከተማ መሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ
URBAN Land Development and management

መፍቻ
G1፡ ለቢሮዎች
B1፡ ለትንንሽ ንግድ ማዕከላት
B2፡ ለመካከለኛ ንግድ ማዕከላት
B3፡ ለትልልቅ ንግድ ማዕከላት
ማብራሪያ፡ ሠንጠረዡ እንደሚያሳየው በ G+0 ሌቭል ለኢንዱስትሪና ወርክሾፕ የሚውል ቦታ እስከ ደረጃ ሦስት
እንደማይዘጋጅ ያሳያል፡፡
3. ለመጋዘኖችና ለጋራዥ አገልግሎት
ጠ/የወለል ስፋት
የሚያስፈልገው የቦታ ስፋት (ሜ/ካሬ)
የህንፃው ህንፃው የህንፃው
ተ.ቁ.
አገልግሎት የሚያርፍበት ከፍታ ደረጃ
ደረጃ 1 ደረጃ 2 ደረጃ 3 ደረጃ 5
የወለል ስፋት 4
1 J1, J2, J3, J4, 1 ዐዐ G+0 _ _ _ 100-250 330
1 ዐዐ
2 J1, J2, J3, J4, 200 G+0 _ _ _ 200-500 651
2 ዐዐ
3 J1, J2, J3, J4, 500 G+0 _ _ _ 500- 1650
5 ዐዐ 1250
4 J1, J2, J3, J4, 700 G+0 _ _ _ 700- 2320
700 1750
5 J1, J2, J3, J4, 1000 G+0 _ _ _ 1000- 3320
1000 2500

የኢንዱስትሪ ቀጠና (Zone) ልማት ኦፕሬሽናል ማንዋል


21
የፌደራል ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር
MINISTYR OF URBAN DEVELOPMENT AND CONSTRUCTION
የከተማ መሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ
URBAN Land Development and management

6 J1, J2, J3, J4, 300 G+2 _ 100-162 150-200 250 325
300
7 J1, J2, J3, J4, 100 G+4 250-285 285 400 500 651
2 ዐዐ
8 J1, J2, J3, J4, 35 ዐዐ G+6 700 700 1000 1250 1250
5 ዐዐ
9 J1, J2, J3, J4, 63 ዐዐ G+8 1000 1150 1150 1750 2280
7 ዐዐ
1ዐ J1, J2, J3, J4, 11000 G+10 1425 1425 2000 2500 2500
1000

መፍቻ
J1, J2, J3፡ ለመጋዘኖች
J4፡ ለጋራዥ አገልግሎት

ማብራሪያ፡ ሠንጠረዡ እንደሚያሳየው በ G+0 ሌቭል ለመጋዘኖችና ጋራዥ አገልግሎት የሚውል ቦታ እስከ ደረጃ
ሦስት እንደማይዘጋጅ ያሳያል፡፡

የኢንዱስትሪ ቀጠና (Zone) ልማት ኦፕሬሽናል ማንዋል


22

የፌደራል ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር


MINISTYR OF URBAN DEVELOPMENT AND CONSTRUCTION
የከተማ መሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ
URBAN Land Development and management

4. ለሱቆችና ለሸቀጣ ሸቀጥ መጋዘን፤


ጠ/የወለል ስፋት
የሚያስፈልገው የቦታ ስፋት (ሜ/ካሬ)
የህንፃው ህንፃው የህንፃው
ተ.ቁ.
አገልግሎት የሚያርፍበት ከፍታ
ደረጃ 1 ደረጃ 2 ደረጃ 3 ደረጃ 4 ደረጃ 5
የወለል ስፋት
50
1 F2 G+0 __ __ __ __ 50-160
50
100
2 F2 G+0 __ __ __ __ 100-325
100
3 F2 600 G+2 __ __ 200-400 300-500 600-651
200
1000
4 F2 G+4 200-250 250-325 325-400 400 651
200
1000
5 F1 F3 G+3 __ 250-416 325-500 500-625 825
250
300 300-
6 F1 F3 G+0 __ __ __ __
300 1000
500 500-
7 F1 F3 G+0 __ __ __ __
500 1650
3500
8 F1 F3 G+6 625 825 1000 1250 1650
500
1000 1000-
9 F1 F3 G+0 __ __ __ __
1000 3320
9000
10 F1 F3 G+8 1250 1650 2000 2500 3320
1000

የኢንዱስትሪ ቀጠና (Zone) ልማት ኦፕሬሽናል ማንዋል


23

የፌደራል ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር


MINISTYR OF URBAN DEVELOPMENT AND CONSTRUCTION
የከተማ መሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ
URBAN Land Development and management

መፍቻ
F1፡ ለትልልቅ ሱቆች
F2፡ ለትንንሽ ሱቆች
F3 ፡ ለሸቀጣ ሸቀጥ መጋዘን
ማብራሪያ፡ ሠንጠረዡ እንደሚያሳየው ከ G+2 በታች ለሆኑ ትናንሽ ሱቆች ግንባታ የሚውል ቦታ በደረጃ አንድና ሁለት
እንደማይዘጋጅ ያሳያል፡፡ በተመሳሳይም በ G+0 ሌቭል ለትናንሽ ሱቆች መስሪያ ተብሎ እስከ ቦታ ደረጃ
አራት አይዘጋጅም፣
የኢንዱስትሪ ቀጠና (Zone) ልማት ኦፕሬሽናል ማንዋል
24

You might also like