You are on page 1of 2

መጋቢት 01/2011 ዓ.

የሉቄ አካባቢ ነዋሪዎች መረዳጃ ዕድር አመታዊ ሪፖርት የተከበራችሁ የዕድሩ አባላት

የአሁኑ ሥራ አመራር ኮሚቴ ሥራውን ከተረከበ ከየካቲት 2010 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ጥር 2011 ዓ.ም ድረስ
ያከናወናቸው ሥራዎችን ከዚህ ቀጥለን እናቀርባለን፡፡

የተከናወኑ ሥራዎች

 ሐዘን ለደረሰባቸው የዕድሩ አባላት በመመሪያው መሰረት አስፈላጊው ሁሉ እየተከናወነ ነው፡፡


 የዕድሩ ንብረት በጠቅላላው በጥንቃቄ እንዲያዝ እየተደተረገ ነው፡፤
 ለዕድሩ ቦታ ዓመታዊ ግብር መከፈል በሚገባበት ጊዜ ተከፍሏል፡፡
 የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ሰነድ አስፈላጊ በመሆኑ ከአዲስ አበባ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ፕሮጀክት
ጽ/ቤት በመቀበል ከካርታውና ሌሎች ሰንዶች ጋር ተያይዞ እንዲቀመጥ ተደርጓል፡፡
 ለአዲሶች ቤቶች አገልግሎት የሚውል የኤሌትሪክ ቆጣሪ ከመብራት ኃይል ተጠይቆ እንዲገባ ተደርጓል፡፡
አገተልግሎትም እየሰጠ ይገኛል፡፡
 ሁለት የብረት መዝጊያዎች ማላትም የአዳራጁና አንድ የመኖሪያ ቤት መዝጊያዎች ጥገና
ተደርጎላቸዋል፡፡
 ከዕድሩ አባላት የሚሰበሳበው ወርሃዊ ገቢና ከቤቶች ኪራይ የሚገባው ገንዘብ በወቅቱ በዕድሩ ባንኩ
አካውንት በየወሩ እየገባ ይገኛል፡፡
 ጠቅላላ ገቢን፣ ወጭንና ከወጭ ቀሪን በተመለከተ ከኦዲት ሪፖርት ማግኘት ይቻላል፡፡

የዕድሩን መተዳደሪያ ደንብ በተመለከተ

1. የዕድሩ ሕግና ደንብ ከተረቀቀና ሥራ ላይ መዋል ከጀመረ ቆይቷል፡፡ በመሆኑም አጠቃላይ ግመገማ
ለማድረግ አንድ ኮሚቴ ተቋቁሞ እንዲጠና ቢደረግና የሚሻሻለው እንዲሻሻል የሚለመጠውም
እንዲለወጥ ተደርጎ ወቅቱን የሚመጥን ተደርጎ ቢዘጋጅ
2. የቀደመው የሥራ አመራር ኮሚቴ በአንዳንድ ሕጎችና ዳንቦች ላይ ማሻሻያ በማድረግ ሥራ ላይ
አውሎአል እኛም ይህንኑ ስንተግብር ቆይተናል ግን አሁን ለጠቅላላው ጉባኤ ቀርቦ መፅደቅ
ስለሚኖርበት ከዚህ ቀጥሎ አቆርበንዋል፡፡

ሀ/ ለአባት እናት ልጅ ሲሞትና አስክሬን ከቤት ሲወጣ በር 5,000

ለ/ ለአባት እናት ልጅ ሲሞትና መርዶ ሲሆን ብር 2,500

ሐ/ የዕድሩ አባልና /የትዳር ጓደኛ ሲሞት ብር 10,000


መ/ ዕህት ወንድም ሲሞትና አስክሬን ከቤት ሲወጣ ብር 1,500

ሠ/ እህት ወንድም ሲሞትና መርዶ ሲሆን ብር 700

ረ/ ዕንግዳ ደራሽ /ሠራተኛ ሞቶ አስክሬን ከቤት ሲወጥ ብር 1,000 እንዲሁም የዕድሩ የዕድሩ አባል መሆን
ለሚፈልግ አዲስ ገቢ ብር 10,000 ናቸው፡፡

ልማትን በተመለከተ

ብዙ የሚሰራ ሥራ እንዳለ የታወቀ ቢሆንም እንኳ አቅም በፈቀደ መጠን የሚከተሉትን ሥራዎች መስራት
አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል፡፡

1. በወንዙ በኩል ለሚገኘው ቤት መሰረቱ በውሃ እየተሸረሸረ ስለሆነ ጥገና ያስፈልገዋል እንዲሁም
በዚያው በኩል ላለው የብሎኬት ግድግዳ በውጭ በኩል የግርፍ ሥራ ይሰራለት፡፡
2. በፊት ለፊት በኩል ያለው የቆርቆሮ አጥር እየፈረሰ ስለሆነ ከስር ያለውን የድንጋይ ግን በቢም አስሮ
በብሎኬት ቢገነባ በቋሚነት አካልግሎት ይሰጣል
3. ለግቢው በር ስፊ የብረት መዝጊያ ከተሸካሚ ብረቶች ጋር ተሰርቶ/ ተገዝቶ ይገጠምለት፡፡ በማለት
ሃሳብ ቀርቧል፡፡

You might also like